cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

እውነት የሆነ የሕይወት ቃል / A true word of life

“በመጀመሪያው ቃል ነበረ፥ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፥ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ።” — ዮሐንስ 1፥1 በመጀመሪያ የነበረውን እውነት የሆነውን የሕይወትን ቃል እንሰብካለን።

Mostrar más
El país no está especificadoEl idioma no está especificadoLa categoría no está especificada
Publicaciones publicitarias
130
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
Sin datos30 días

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

https://www.youtube.com/watch?v=bFB9N4swRMs 🔥🙏SUBSCRIBE AND SHARE !!!🙏🔥
Mostrar todo...
ድንቅ ትምህርት "IMPARTATION እጅ ማስጫን ሳይሆን እጅ ማስታጠብ ነው። " Amazing Gospel teaching by Apostle Kaleab Tadess!

አዳሲስ ቪዲዮዎችንና ተከታታይ መልዕክቶች ወዲያው እንዲደርስዎ ከታች ያለዉን ሊንክ በመጫን ሰብስክራይብ ያድርጉ Facebook- [

https://www.facebook.com/mightiestemple

] [

https://www...

ክርስቲያኖችን ሰለ እሳት ከማስረዳት ይልቅ በእሳት ትንሽ ማቃጠል ስለ እሳት ሀይልና አቅም ማሳውቅ ይቻላል፡፡ሰለ መንፈስ ቅዱስ በchapter ከፋፍለህ ብትማር ከዘፍጥረትና ከዘፀአት ከማርቆስና ከቆሮንቶስ ብታጠናው ሰለ እርሱ ታውቃለህ እንጂ እርሱን ማውቅ አትችልም፡፡መንፈስ ቅዱስን ማውቅ የሚቻለው በእርሱ በመነካት ብቻ ነው፡፡ ዮሐንስ 14 ¹⁵-¹⁶ ብትወዱኝ ትእዛዜን ጠብቁ። እኔም አብን እለምናለሁ ለዘላለምም ከእናንተ ጋር እንዲኖር ሌላ አጽናኝ ይሰጣችኋል፤ ¹⁷ እርሱም ዓለም የማያየውና የማያውቀው ስለ ሆነ ሊቀበለው የማይቻለው የእውነት መንፈስ ነው፤ ነገር ግን ከእናንተ ዘንድ ስለሚኖር በውሥጣችሁም ስለሚሆን እናንተ ታውቃላችሁ። የእግዚአብሔር ሰው ቃልአብ ታደሰ.
Mostrar todo...
1ኛ ቆሮንቶስ 13 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ በሰዎችና በመላእክት ልሳን ብናገር፣ ፍቅር ግን ከሌለኝ እንደሚ ጮኽ ናስ ወይም እንደሚንሿሿ ጸናጽል ነኝ። ² የትንቢት ስጦታ ቢኖረኝ፣ ምስጢርን ሁሉና ዕውቀትን ሁሉ ባውቅ፣ ተራራንም ከቦታው የሚነቅል እምነት ቢኖረኝ፣ ፍቅር ግን ከሌለኝ ከንቱ ነኝ። ³ ያለኝን ሁሉ ለድኾች ብሰጥ፣ ሰውነቴንም እንዲቃጠል ለእሳት ብዳርግ፣ ፍቅር ግን ከሌለኝ ምንም አይጠቅመኝም። ⁴ ፍቅር ታጋሽ ነው፤ ደግሞም ቸር ነው። ፍቅር አይመቀኝም፤ አይመካም፤ አይታ በይም፤ ⁵ ተገቢ ያልሆነ ነገር አያደርግም፤ ራስ ወዳድ አይደለም፤ አይበሳጭም፣ በደልን አይቈጥርም። ⁶ ፍቅር ከእውነት ጋር እንጂ በዐመፅ ደስ አይሰኝም። ⁷ ፍቅር ሁል ጊዜ ይታገሣል፤ ሁል ጊዜ ያምናል፤ ሁል ጊዜ ተስፋ ያደርጋል፤ ሁል ጊዜ ጸንቶ ይቆማል።
Mostrar todo...
እርሱ ለእኛ መዳን ወዶ እና ፈቅዶ ነፍሱን ሰጠ፡፡ ሞትንም ድል አድርጎ ተነሳ፡፡ ክብርና ምስጋና ውዳሴም ለታረደው በግ ለዘለዓለም ይሁንለት
Mostrar todo...
የሞተልን እርሱ ተነስቷል!!!
Mostrar todo...
አንዳንድ ጊዜ የእግዚአብሔር ሀሳብና ፈቃድ ሚስጢር ነው። በሕይወታችን ውስጥ እርሱ የከብርበት ዘንድ ለእኛ የማይገቡን እና የማንጠብቃቸው ነገሮች ይገጥሙናል። ያኔ ሁሉን ቻይ የሆነውን የእግዚአብሔርን እጅ እናያለን! ========================= “ኢየሱስ ይህን በሰማ ጊዜ፣ “ይህ ሕመም የእግዚአብሔር ልጅ በእርሱ ይከብር ዘንድ ለእግዚአብሔር ክብር ነው እንጂ ለሞት የሚያደርስ አይደለም” አለ።” — ዮሐንስ 11፥4 (አዲሱ መ.ት)
Mostrar todo...
ኢየሱስ ክርስቶስ ለዘለዓለም ጌታ ነው!!! የሚያምን ብቻ አሜን ይበል
Mostrar todo...
እግዚአብሔር ትልቅ ነው።እርሱን አውቀነው አንጨርሰውም ሰዎችና ሁኔታዎች ገድበው በሚስሉልን ምስል ሳይሆን ቃሉ በሚተርክልን ልክ እንመነው... እግዚአብሔርን ማንም ጥግ ድረስ ሊያብራራው አይችልም... እርሱ ከምንምና ከማንም በላይ ነው። በሰዎችም ዕውቀት አይለካም። እግዚአብሔርን መመልከቻ መነፅራችን በሰዎች ልክ ሳይሆኑ ቃሉ በሚገልፅልን ልክ ይሁን። ያኔ ሁሌ በእርሱ እንገረማለን ውስጣችን ሀሴት ያደርጋል ምን ያህል ሀያል እንደሆነም እንገነዘባለን። ክብርና ምስጋና ሀያል ለሆነው አባታችን ይሁን!!!
Mostrar todo...
# በምንሰማውና በምናየው ነገር ከምንረበሽ ይልቅ ሁሉን ነገር መለወጥና በምንም ነገር ውስጥ መንገድን በሚያበጀው እግዚአብሔር ፊት በንስሃ እንውደቅ። # እግዚአብሔር በምንም ሁኔታ አይለወጥም! መለወጥ የእርሱ ባህሪው አይደለም ይልቅ እንዳንጠፋ ነገሮችን ወደ መልካም ነገር መለወጥ ይችልበታል። # በእኛ ማንነት ውስጥ ክርስቶስ ይታይ። እኛ ውስጥ ያለው ብርሃን በጨለማ ላይ ይብራ... ሰዎች መልካም ስራዎቻችንን በማየት የሰማይ አባታችንን ያክብሩት። ቤተሰብ ይሁኑ 👇👇👇👇👇 @jesuswasword @jesuswasword @jesuswasword
Mostrar todo...