es
Feedback
Addis Ababa City Manager Office

Addis Ababa City Manager Office

Ir al canal en Telegram
1 474
Suscriptores
Sin datos24 horas
-37 días
-2130 días
Archivo de publicaciones
የአዲስ አበባ ከተማ ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ለተጠሪ ተቋማት የኮሙዩኒኬሽን መዋቅርና ለተቋሙ ባለሙያዎች በማዘጋጃ ቤታዊ ሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን ስትራቴጂ እና በማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ጋይድላይን ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ዛሬ ጥቅምት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ሰጥቷል። በም/ቢሮ ኃላፊ ደረጃ የጽ/ቤቱ የኮሙዩኒኬሽን ዘርፍ ሃላፊ ወ/ሮ ሃይማኖት ዘለቀ የስልጠናውን ዓላማ አስመልክተው እንደተናገሩት በማዘጋጃ ቤታዊ ዘርፍ የሚሰጡ አገልግሎቶችን አስመልክቶ ለመዲናዋ ነዋሪዎች ትክክለኛ፣ ተአማኒና ወቅታዊ መረጃዎችን በማድረስ አሳታፊ፣ ግልጽነት እና የተጠያቂነት የሰፈነበት የአሰራር ስርአትን በማጠናከር ረገድ የሚዲያ እና ኮሙዩኒኬሽን ዘርፉ የሚጫወተው ሚና የጎላ መሆኑን አስረድተዋል። አያይዘውም በማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት የሚከናወኑ ስራዎችና የሚሰጡ አገልግሎቶች ለከተማችን ነዋሪዎች ወሳኝና አንገብጋቢ እንደ መሆናቸው በሂደቱም የህብረተሰቡን ተሳትፎ ይበልጥ የሚያጎለብቱ አጀንዳዎች በመቅረጽና መረጃዎችንም በሁሉም የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ፕላትፎርሞች በማድረስ ረገድ የሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን አመራርና ባለሙያው ሚና የጎላ በመሆኑ ይህንን በአግባቡ መወጣት ያስፈልጋል ሲሉም ተናግረዋል። የግንዛቤ ማስበጫ መድረኩን አስመልክቶም ተሳታፊ ኮሙዩኒኬተሮች በበኩላቸው እንደተናገሩት የወሰዱት ስልጠና ወቅታዊና በየእለቱ ለሚያከናወኑት የመረጃ ልውውጥ ስራ ተጨማሪ አቅም የሚፈጥርላቸው እንደሆነ ጠቅሰው ከዚህ በተጨማሪም ስልጠናው በተናጠል የሚኖሩ የመረጃ ልውውጦችን የሚያሻሽልና በተቀናጀና ተናባቢ በሆነ መንገድና ውጤታማ የኮሙዩኒኬሽን ተልዕኮዎችን ለመወጣት እንደሚያስችላቸው ተናግረዋል። በግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናው የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ፣ የጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ፣ የሲቪል ምዝገባና ነዋሪዎች አገልግሎት ኤጀንሲ ፣ የመብራት አገልልግሎት አስተዳደር ባለስልጣን እንደዚሁም ከከተማው ስራ አስከያጅ ጽ/ቤት ልዩ ልዩ ስራ ክፍሎች የተወጣጡ አመራርና ባለሞያዎች ተሳትፈዋል:: ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

ወደ "ፍካት" በሚል ርእስ በአዲስ አበባ ከተማ ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤትና በአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ጋር በመተባበር በ90 ቀናት የልዩ ንቅናቄ እቅድ የተከነናወኑ የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት የተሟሉላቸውና በሁሉም መስክ አብነታዊ አፈጻጸም የተመዘገበባቸው የተቀናጀ የሞዴል ብ… See more

በጎርጎራ ጣናነሽ የተሰኘችዉን ጀልባ ሥራ አስጀምረናል። በጣና ውሃ ላይ እየቀዘፈች ባሕር ዳር ከተማን ከጎርጎራ ኤኮ ሎጅ ማገናኘት ጀምራለች። ከ180 ተጓዦች በላይ የማጓጓዝ አቅም ያላት ጣናነሽ ለጉብኝት፣ ለመዝናናት እና አስደማሚውን የጣና ሀይቅ የተፈጥሮ… See more

የሚሰጡ አገልግሎቶችን ለማዘመንና ብቁ የሆኑ ባለሙያዎችን ለመፍጠር የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች ወሳኝ ሚና እንዳላቸው በቢሮ ሀላፊ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ስራ አስኪያጅና የጥናት ልማት ትግበራ ዘርፍ ሀላፊ ወ/ሮ ይመኙሻል ታደሰ ገለፁ። በአዲስ አበባ ከተማ ስራ አስኪያጅ ፅ/ቤት በሜኒስትሪሚንግ አስተባባሪነት ሲሰጥ የነበረዉ የህዝብ መሀል የንግግር ክህሎትን ማሳደግና በሙስና ፅንሰ ሀሳብ ላይ ሲሰጥ የነበረዉ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ተጠናቋል። ለፅ/ቤቱ ሰራተኞች የተሰጠዉ ስልጠና በቀጣይ በስራ እንቅስቃሴ ላይ ለሚኖራቸው ተግባራትን በተቀላጠፈ መልኩ ለመፈፀም ሚናው የጎላ እንደሆነ ወ/ሮ ይመኙሻል ተናግረዉ ከስልጠናው ያገኙትን እዉቀት ወደ ተግባር መቀየር ያስፈልጋል ሲሉም አክለዋል። አክለውም ስልጠናውን ለፅ/ቤቱ ሰራተኞች በዚህ ልክ መስጠት አስፈላጊ መሆኑ ገልፀው በተለይም የሚሰጡ አገልግሎቶች ላይ አንዳንድ የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራርና የመልካም አስተዳደር ችግርን ከመቅረፍ አንፃር ስልጠናዉን ወደ ተግባር በመቀየር ወደ ስራ መግባት ያስፈልጋል ሲሉም ወ/ሮ ይመኙሻል ታደሠ አሳስበዋል። በመጨረሻም ስልጠናው በዚህ መልክ መስጠቱ የግንዛቤ አቅምን ከማስፋት ባለፈ በቀጣይ የስራ ሂደት ላይ የራሱ የሆነ አቅም የሚፈጥር ነዉ ሲሉ በስልጠናዉ ላይ ሰልጣኞች ሀሳባቸውን ገልፀዉ ስልጠናዉ ተጠናቋል። ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

በጎንደር በነበረን ጉብኝት የመገጭ የመስኖ ልማት ፕሮጀክትን የሥራ ሁኔታ ገምግመናል። ፕሮጀክቱ 870 ሄክታር ላይ ያረፈ ሲሆን 17000 ሄክታር መሬት በመስኖ አቅርቦት ይሸፍናል ተብሎ ይጠበቃል። የፕሮጀክቱ ቁልፍ የሆነው የወንዝ ቅልበሳ ሥራ በተሳካ መልኩ… See more

በአዲስ አበባ ከተማ ስራ አስኪያጅ ጽ/ ቤት ተጠሪ በሆኑ ተቋማት ለሚሰጡ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎቶች የሚከተሉትን አድራሻዎች ይጠቀሙ! 1.የአዲስ አበባ ከተማ ጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ቢሮ አድራሻ፡- በአራዳ ክ/ከተማ ወረዳ 1 በተለምዶ ፒያሳ እሪ በከንቱ ዮናታን ቢቲ ህንጻ ከ7ኛ ፎቅ ጀምሮ ነጻ የስልክ መስመር - 6199 ቴሌግራም፡- https://t.me/CGAACMA ዩቲዩብ ፡- https://www.youtube.com/@aacma-bu4zt ዌብሳይት፡- www.aacma.gov.et ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/profile.php?id=100064800963883 2.የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ዋና ቢሮ አድራሻ :- አዲሱ ገበያ ቱኒዝያ መንገድ ሸገር መናፈሻ ግቢ ውስጥ ነጻ የስልክ መስመር - 7533 ዌብ ሳይት (website): https://www.aacrrsa.gov.et የፌስቡክ (facebook): https://www.facebook.com/profile.php?id=100064083391686 ቴሌግራም (telegram): https://t.me/addisvaitalpress ፖስታ ሳ.ቁ (Box No)፡ 20320 3. የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ዋና ቢሮ አድራሻ ;-አራዳ ክፍለ-ከተማ ወረዳ 10 አራዳ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ፊትለፊት ነጻ የስልክ መስመር :- 939 fdrmc1926@addisfire.gov.et ፌስቡክ - https://www.facebook.com/AADRMC1 4. የአዲስ አበባ ከተማ መብራት አገልግሎት አስተዳደር ባለስልጣን የቢሮ አድራሻ:- አራዳ ክ/ ከተማ ወረዳ 1 በተለምዶ ፒያሳ እሪ በከንቱ አካባቢ ኤንሪኮ ኬክ ቤት ዝቅ ብሎ ዋስትና ንግድ ማዕከል 17ኛ ፎቅ ስ.ቁ 0111127775 ፌስቡክ ገፅ:-https://www.facebook.com/profile.php?id=61565439308107 EMail; AAESAA@aaca.gov.et Website:-https://aaesa.gov.et ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager r

የህዝብ መሀል የንግግር ክህሎትን በማሳደግና በሙስና መከላከል ፅንሰ ሀሳብ ላይ ያተኮረ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ተሰጠ። የአዲስ አበባ ከተማ የስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት በሚኒስትሪሚንግ ክፍል አስተባባሪነት ለፅ/ቤቱ ዳይሬክተሮችና ባለሙያዎች በህዝብ መሀል የንግግር ክህሎት ማሳደግና የሙስና መከላከል ፅንሰ ሀሳብ ላይ ያተኮረ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና በዛሬዉ እለት ተሰጥቷል። በስልጠናዉ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት በም/ቢሮ ሀላፊ ደረጃ የአዲስ አበባ ከተማ ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት የኮሙኒኬሽን ዘርፍ ሀላፊ ወ/ሮ ሀይማኖት ዘለቀ እንደገለፁት ስልጠናው ለፅቤቱ ሰራተኞች መሰጠቱ በተግባቦት ክህሎት ላይ ያላቸዉን እዉቀት ከማስፋት ባለፈ በቀጣይ የስራ ሂደት ላይ የራሱ የሆነ አዎንታዊ አቅም የሚፈጥር ነዉ ሲሉ ገልጸዋል። አክለዉም በተለይም ከተማችን የደረሰችበትን እድገት የሚመጥን አገልግሎትን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ከማድረግ አንፃር አዎንታዊ ተግባቦትን ማዳበርና ማጎልበት ሚናዉ የጎላ መሆኑን ገልፀው አንዳንድ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚነሱ ቅሬታዎችን በመለየትና በመፍታትና እንዲሁም ከስልጠናው የሚገኘዉን እዉቀት ወደ ተግባር ላይ በማዋል በቀጣይ በትኩረት ወደ ስራ መግባት ያስፈልጋል ሲሉ ተናግረዋል። ለስራ አስኪያጅ ፅ/ ቤት ዳይሬክተሮችና ባለሙያዎች እየተሰጠ ያለው የአቅም ማጎልበቻ ስልጠናዉ የህዝብ መሀል የንግግር ክህሎት ከማሳደግ፣የመናገር ክህሎትና አቅምን ከማሳደግ፣ የተግባቦት ምንነት፣የሙስና ፅንሰ ሀሳብ፣የሙስና ባህሪያት፣ የሙስና አይነቶች በሚሉትና እንዲሁም በሌሎች ርዕሰ ጉዳዮች ስልጠና የተሰጠ ሲሆን ስልጠናዉም የሚቀጥል እንደሆነ ተገልጿል። ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

የቀብር ስነ-ስርዓቷ ተፈጽሟል " ትላንትን ጥቅምት 26 ቀን 2ዐ18 ዓ.ም በስራ ላይ እያለች በድንገት ህይወቷ ያለፈው የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አምቡላንስ ሾፌር የወ/ሮ አበባ አሠፋ የቀብር ሰነ- ስርዓት የእሳትና አደጋ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አመራርና ሠራተኞች እንዲሁም ወዳጅ ዘመዶቿ በተገኙበት ዛሬ ጥቅምት 27 ቀን 2018 ዓ.ም በአንጦጦ ኪዳነም ህርት ቤተክርስቲያን ተፈጽሟል ። ወ/ሮ አበባ አሰፋ ባለትዳርና የሁለት ወንዶችና የሁለት ሴት ልጆች እናት ነበረች። የአዲስ አበባ ከተማ ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት በኮሚሽኑ የአንቡላንስ ሹፌር በነበሩት ወ/ሮ አበባ አሰፋ ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ሃዘን እየገለጸ ለቤተሰቦቻቸው :ለወዳጅ ዘመዶቻቸውና ለስራ ባልደረቦቻቸው ሁሉ መጽናናትን ይመኛል። ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

በመዲናችን አዲስ አበባ የተቀናጀ የሞዴል ብሎኮችና ወረዳዎች ፈጠራ ስራ በከተማዋ እየተከናወነ ካለው የኮሪደር ልማት ጋር አስተሳስሮ መስራት በመቻሉ በርካታ ብሎኮችና ወረዳዎች ፅዱ ፣ውብና ለነዋሪዎች ምቹ ፣ከአደጋ ስጋት የተጠበቁ፣ ብርሐናማ የሆኑ፣ ሌሎች አስፈላጊው መሰረት ልማት የተሟሉላቸው እንዲሆኑና የነዋሪዎች የማንነት መለያ ስርአት የተጠናከረባቸው የማድረግ ስራ በህብረተሰቡ ተሳትፎ ተጠናክሮ ቀጥሏል። ለአብነት በቦሌ ክፍለከተማ፣ በልደታ፣ በየካና በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የተቀናጀ ሞዴል ብሎክ የመፍጠር ተግባራት በምስል ተቃኝቷል። ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት ዛሬ ጥቅምት 27 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ስራ ለማከናወን በአዲስ አበባ እና ሸገር አንዳንድ አካባቢዎች ላይ ኃይል የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች :- 👉ከጠዋቱ 2፡30 እስከ 9፡30 በግብፅ ኤምባሲ፣ 6 ኪሎ ዩኒቨርስቲ፣ የካቲት 12 ሆስፒታል፣ ኤፍቢ ግቢ፣ ናይጄሪያ ኤምባሲ፣ 20 ቀበሌ፣ ሸጎሌ አንበሳ ጋራዥ ፣ ሸጎሌ መንደር-7፣ ፊናንስ፣ አበበ ቢቂላ፣ ኳስ ሜዳ፣ መሳለሚያ፣ እህል በረንዳ ፣ አውቶብስ ተራ፣ አዲስ ከተማ ት/ቤት፣ ገነሜ ት/ቤት፣ አማኔኤል ቤ/ክ ፊትለፊት 👉ቦሌ ሁላሳ ፣ ሰበታ፣ ዓለም ገና፣ ካዲስኮ ቀለመል ፋብሪካ፣ ዮሴፍ ኢንዱስትሪ መንደር፣ ጃማይካ ጫማ፣ አዲስ ሰፈር፣ ንፋስልክ ሼል ዲፖ፣ አኔ ዲማ፣ ወጣቢቻ፣ ጉዱ፣ ሙሎና ከሚሴ ከተሞች፣ ድሬ ከአስፋልትበላይ፣ ገፈርሳ ውሀ ግድብ እና አካባቢው፣ ሲሊ፣ ከረላ፣ መናገሻ እና በአካባቢው ላይ የኃይል አቅርቦት እንደሚቋረጥ Ethiopian Electric Utility -የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታውቋል፡፡ ስለሆነም አገልግሎቱ "በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን በትህትና እንጠይቃለን" ብሏል፡፡ ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager