1 474
Suscriptores
Sin datos24 horas
-37 días
-2130 días
Archivo de publicaciones
በአደጋው በሰው ላይ የደረሰ ጉዳት የለም ።
ዛሬ ጥቅምት 14 ቀን 2018 በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ሶር አምባ ሆቴል ፊት ለፊት ከቀኑ 6 :45 ሠዓት ላይ የትራፊክ አደጋ ያጋጠመ ሲሆን በአደጋው በንብረት ላይ መጠነኛ ጉዳት ከመድረሱ በስተቀር በሠው ላይ የደረሰ ጉዳት የለም።
አደጋው በደረሰበት ሰዓት መኪናውን እያሽከረከረ የነበረዉ ሾፌር ምንም ጉዳት ሳይደርስበት ከተገለበጠው ተሽከርካሪ ውስጥ መውጣት ችሏል።
የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የአደጋ ጊዜ ሠራተኞች በአደጋው ምክንያት የተገለበጠውን ተሽከርካሪ በማንሳት መንገዱ ለትራፊክ እንቅስቃሴው ክፍት እንዲሆን አድርገዋል፡
ለእሳትና ለሌሎች ድንገተኛ አደጋዎች እንዲሁም ለአንቡላንስ አገልግሎቶች በ939 ፈጥነዉ ያሳዉቁ!
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ምልከታ በኮይሻ’ ዛሬ ምሽት 2:30 ይጠብቁ!
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የ2018 ዓመተ ምህረት የመጀመሪያ 100 ቀናት የማክሮኢኮኖሚ አፈፃፀም ግምገማ በኮይሻ ግድብ ከሚኒስትሮች ጋር ያደረጉት ውይይት።
የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ዛሬ ጠዋት በተለያዩ ሀገራዊ ጉዳዮች እና በልዩ ልዩ የፓርቲ አጀንዳዎች ላይ ለመወያየት፣ ስብሰባ ጀምረናል።
Koreen Hojii Raawwachiiftuu Paartii Badhaadhinaa dhimmoota biyyaa garaagaraafi ajandaawwan paartii addaddaarratti marii'achuuf walgahii taa'uu eegaleera.
ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር ወሏል!
ዛሬ ጥቅምት 14 ቀን 2018 ዓ.ም በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 መነን ፀሀይ ጮራ ት/ቤት አካባቢ ከጠዋቱ 2፡08 ሰዓት ላይ በመኖሪያ ቤቶች ላይ ተነስቶ የነበረው የእሳት አደጋ ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር ውሏል።
በእሳት አደጋው በሠው ላይ የደረሰ ጉዳት እንደሌለ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል።
ለእሳትና ለሌሎች ድንገተኛ አደጋዎች እንዲሁም ለአንቡላንስ አገልግሎቶች በ939 ፈጥነዉ ያሳዉቁ!
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
አገልጋይ | ቆይታ ከአዲስ አበባ ከተማ የሲቪልምዝገባና የነዋሪዎች አገልግሎት ኤጀንሲ ጋር
AMN - ጥቅምት 13/2018 ዓ.ም
የመንገድ መብራቶችን በመጠገን ብርሀን እንዲሰጡ የማድረግ ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል
የአዲስ አበባ ከተማ መብራት አገልግሎት አስተዳደር ባለስልጣን በተለያዩ ምክንያቶች አገልግሎት የማይሰጡ የመንገድ መብራቶችን በመጠገን በምሽት በቂ ብርሀን እንዲሰጡ የማድረግ ስራውን አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡
ባለፉት ቀናት የተለያዩ የጥገና ስራዎች በማከናወን እንዲበሩ እየተደረጉ ካሉ መንገዶች ውስጥ ከአፍንጮ በር - ስድስት ኪሎ፣ ቡልቡላ 40/60 ፣ ከሳሪስ አቦ - ቡልቡላ፣ አስኮ አዲሱ ሰፈር አራት መንታ፣ ሳሪስ ብሔረጽጌና ፈረንሳይ ኤምባሲ ጊዜ ለኩሉ የውስጥ ለውስጥ መንገዶችና ሌሎችም አካባቢዎች ላይ ያሉ የመንገድ መብራቶችን በመጠገን ለህብረተሰቡ የምሽት እንቅስቃሴ ምቹ የማድረግ ስራ ተከናውኗል፡፡
በባለስልጣኑ በነዚህና በሌሎች የመንገድ መብራቶች ላይ ያጋጠሙ ብልሽቶችን በመለየትና አስፈላጊውን የጥገና ስራ በማከናወን ህብረተሰቡ የሚያነሳቸውን የመንገድ መብራት ጥያቄዎችን ለመመለስ ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡
መሰረተ-ልማቱን ከስርቆትና ሆን ተብሎ ከሚፈፀም ህገ-ወጥ ተግባር በመጠበቅና በመከላከል የመንገድ መብራቱ ተገቢውን አገልግሎት እንዲሰጥ ህብረተሰቡ የተለመደውን ትብብር እንዲያደርግ ባለስልጣኑ መልዕክቱን ያስተላለፋል፡፡
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
የፈረንሳይ ቡጉዌስ ከተማ ልዑካን ቡድን በአዲስ አበባ ከተማ እየተካሄዱ ያሉ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እንዲሁም ታሪካዊ ስፍራዎችን ጎበኙ
በአዲስ አበባ እየተከናወነ ያለው የወንዝ ዳርቻ ልማት ከተማዋን ውብ ከማድረግ ባሻገር ብክለትን ከመከላከል አንፃር የሚደነቅ መሆኑን በአዲስ አበባ ጉብኝት ያደረጉ የፈረንሳይ ቡጉዌስ ከተማ ልዑካን ቡድን ተናገሩ፡፡
ልዑካን ቡድኑ የወንዝ ዳርቻ ልማትን ጨምሮ በአዲስ አበባ ከተማ እየተካሄዱ ያሉ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እንዲሁም ታሪካዊ ስፍራዎችን ጎብኝተዋል።
በከንቲባ ሊዮኔዳስ ሰርጌ፣ ምክትል ከንቲባ ሚስተር ዣን ሉክ ኤሪክ ኩዴይራት እና ሌሎች የከተማዋ ባለስልጣናት የተመራውን የቡግዌስ ከተማ የልዑካን ቡድን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጋር በመተባበር በከተማ እየተከናወነ ያለውን የልማት ስራ አስጎብኝቷል።
በአዲስ አበባ እየተከናወነ ያለው የወንዝ ዳርቻ ልማት ከተማዋን ውብ ከማድረግ ባሻገር ብክለትን ከመከላከል አንፃር የሚደነቅ መሆኑንም ልዑካን ቡድኑ ገልጿል።
አዲስ አበባ እያከናወነች ያለውን የልማት ስራ እንደሚደግፍ እና እንደ ትምህርት ባሉ ዘርፎች በትብብር የመስራት ፍላጎት እንዳላቸውም የቡግዌስ ከተማ ልዑካን ተናግረዋል ።
የልዑካን ቡድኑ በፓሪስ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስተባባሪነት በብጉየስ እና በድሬዳዋ መካከል ያለውን የእህትማማች ከተማ አጋርነት ለማጠናከር ነው ወደ ኢትዮጵያ ለስራ ጉብኝት የመጣው።
AMN
የ2018 ዓመተ ምህረት የመጀመሪያ 100 ቀናት የማክሮኢኮኖሚ አፈፃፀም ግምገማ - በምስል
Council of Ministers’ macroeconomic evaluation for the first 100-days - in pictures
