es
Feedback
Addis Ababa City Manager Office

Addis Ababa City Manager Office

Ir al canal en Telegram
1 474
Suscriptores
Sin datos24 horas
-37 días
-2130 días
Archivo de publicaciones
ኤጀንሲው በክረምቱ ወራት የተሰሩ ቤቶችን ለባለቤቶቹ አስተላለፈ። "በጎነት ለአብሮነት!" በሚል መሪቃል የአዲስ አበባ ከተማ የፅዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ከዘርፉ ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር በክረምቱ ወራት በበጎፈቃድ የተሰሩ 5 የአቅመ ደካማ ቤቶችን በመስራት አጠናቆ ለባለቤቶቹ አስተላልፏል። ቤቶቹ የተገነቡት ከበጎ ፈቃደኞች በተገኘ ወደ 4 ሚሊዮን በሚጠጋ ብር ወጪ እንደሆነ ተገልጿል። በምርቃ ስነስርአቱ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የአዲስ አበባ ከተማ ፅዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ገዛኸኝ ዴሲሳ በክረምት በጎ ፍቃድ የሚሰሩ ሰው ተኮር ተግባራት በዝቅተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎችን ችግር ከማቅለልም ባሻገር አብሮ የማደግ ባህልን የሚያዳብር እንደሆነ ገልፀዋል። አቶ ገዛኸኝ አክለውም ልማት በመንግስት አቅም ብቻ የሚሳካ አለመሆኑን ጠቁመው፣ የሁሉንም ቅንጅታዊ ትብብር የሚጠይቅ በመሆኑ "ስንተባበር የማንችለው ነገር የለም" ሲሉ የትብብርን አስፈላጊነት አብራርተዋል። ዋና ዳይሬክተሩ አያይዘውም አቅመ ደካሞች ሀገርን በማስቀጠል ሂደት ውስጥ ትልቅ ሚና የነበራቸው መሆኑን ገልጸው፣ እነዚህን ወገኖች ቅድሚያ የልማቱ ተጠቃሚ በማድረግ ማገዝና መረዳት የትላንት ባለውለታዎችን ማመስገን መሆኑን ተናግረዋል። በተጨማሪም የከተማዋን ፅዳት ከመጠበቅ ጎን ለጎን በእንዲህ ባለ ሰው ተኮር ተግባር ላይ መሳተፍ እርካታን የሚሰጥ በመሆኑ፣ ይህ በጎ ተግባር ወደፊትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። ለቤቶቹ ግንባታና ዕድሳት ወጪውን ለሸፈኑ አካላትም ዋና ዳይሬክተሩ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከጥቅምት 4 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ አቶ ሳንዶካን ደበበ የኢትዮጵያ ኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን ኮሚሽነር አድርገው ሾመዋል።

ጥቅምት 4 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ 49ኛ መደበኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ውሳኔዎች የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 49ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡ 1. በቅድሚያ ምክር ቤቱ የተወያየው የኢትዮጵያ ኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን ማቋቋሚያ ደንብ ላይ ነው፡፡ ኮሚሽኑ ሀገራችን የኒውክለር ቴክኖሎጂን ለሰላማዊ መንገድ ከዓለም አቀፍ ማዕቀፎች ጋር በተጣጣመ መልኩ በኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት፣ በኢንዱስትሪ ልማት፣ በምግብ ዋስትና፣ በጤና አገልግሎት፣ በሳይንስ እና ምርምር ዘርፎች ላይ ለመጠቀም የምታደርገውን ጥረት የመምራትና የማስተባበር ሃላፊነት እንዲኖረው ተደርጎ ደንቡ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በጉዳዩ ላይ በሰፊው ከተወያየበት በኋላ ደንቡ በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 2. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው የኢትዮጵያ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ለሚሰጣቸው አገልግሎቶች የሚከፈል የአገልግሎት ክፍያን ለመወሰን በወጣ ደንብ ላይ ነው፡፡ ተቋሙ የሚሰጣቸውን የምርምር፣ የቴክኖሎጂ ሽግግር፣ የተግባር ተኮር ስልጠናና ማማከር እና የስፔሻላይዝድ ላባራቶሪ አገልግሎቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ለሕብረተሰቡ በማቅረብ ወጪውን በሙሉ ሸፍኖ የውስጥ ገቢውን ለማሳደግ እንዲችል የአገልግሎት ክፍያ ደንብ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በጉዳዩ ላይ በሰፊው ከተወያየበት በኋላ ደንቡ በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 3. በመጨረሻም ምክር ቤቱ የተወያየው የኢትዮጵያ የአደጋ ስጋት ምላሽ ፈንድ ጽህፈት ቤትን ለማቋቋም እና የሚሰበሰበውን የፈንድ ገቢ መጠን ለመወሰን የወጣ ደንብ ላይ ነው፡፡ የኢትዮጵያ የአደጋ ስጋት ምላሽ ፈንድ ጽ/ቤት በአዋጅ ቁጥር 1386/2017 የተቋቋመውን የአደጋ ስጋት ምላሽ ፈንድ ለማስተዳደር የሚቋቋም ሲሆን የሚሰበሰበውን የፈንድ ገቢ መጠን ለመወሰን እንዲቻልም ደንቡ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በጉዳዩ ላይ በሰፊው ከተወያየበት በኋላ ደንቡ በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

በጎነት ለአብሮነት!" በሚል መሪቃል የአዲስ አበባ ከተማ የፅዳት አስተዳደር ኤጀንሲ የዘርፉን ባለድርሻ አካላት በማስተባበር " በወርሃ ክረምቱ ያስገነባቸውን #5 የአቅመ ደካማ ቤቶችን ሙሉ በሙሉ ሰርቶ በማጠናቀቅ በዛሬው ዕለት በአራዳ ክ/ከተማ ወረዳ 06 ጃንሜዳ አካባቢ ለባለቤቶቹ እንደሚያስረክብ ገልጿል።

ከምክርቤት አባላት ለቀረቡ ጥያቄዎች የተሰጠ ምላሽና ማብራሪያ ፦ Gaafilee miseensota mana maree irraa dhihaataniif deebii fi ibsa laatame!

አዲስ አበባ ከተማ ስራ አስኪያጅ ፅ/ቤት 18ኛው የሰንደቅ ዓላማ ቀን ተከበረ። በእለቱም " ሰንደቅ አላማችንን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብስራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ›› በሚል መሪ ቃል ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡ ሰንደቅ አላማ በእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ልብ የታተመ የሃገር አንድነትና ነጻነት መገለጪያ ታላቅ የብሄራዊ ኩራት አርማ እንደሆነና ፡ሰንደቅ አላማ የአንድ ሃገር መንግስት እና ሕዝባዊ ሉዓላዊነት፣ ነጻነት፣ እድገት እና ማህበራዊ ትስስር መፍጠር የሚያስችል እንደሆነም በውይይት መድረኩ ተመላክቷል፡፡ በዉይይት መድረኩም የፅ/ቤቱ በምክትል ቢሮ ሀላፊ ደረጃ የኮሙኒኬሽን ዘርፍ ሀላፊ ወ/ሮ ሃይማኖት ዘለቀ ባስተላለፉት መልዕክት የአገራችን ሰንደቅ ዓለማ ክብር እና ተገቢውን ከፍታ አስጠብቆ ለቀጣዩ ትውልድ ለለማስተላለፍ ሀገራዊ ሉዓላዊነት እና አንድነትን ማስቀጠልእንዲሁም ህብረብሄራዊ ወንድማማችነትን በማጽናት ሀገራችንን የደረሰችበትን የእድገት ከፍታ ማረጋገጥ ከዚህ ትውልድ የሚጠበቅ ታላቅ ገራዊ ሃላፊነት አንደሆነ ገልፀዋል፡፡ አክለዉም ሰራተኛው የኢትዮጵያን ከፍታ ዘመን አካል በመሆን ባለበት እና በተሰማራበት የሥራ መስክ ከምንጊዜውም ጊዜ በበለጠ በቅንነትና በታማኝነትን እንዲሁም በሃላፊነት በተሞላበት ስሜት ሊተገብረዉ ይገባል ሲሉ አመልክተዋል፡፡

የፍል ውሃ አገልግሎት ድርጅት በካይ የፍሳሽ ቆሻሻ ወደ ወንዝ በመልቀቁ 300 ሺህ ብር መቅጣቱን ባለስልጣኑ አስታወቀ በአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 በካይ የፍሳሽ ቆሻሻ ወደ ወንዝ የለቀቀው የፍል ውሃ አገልግሎት ድርጅት 300 ሺህ ብር መቅጣቱ አስታወቀ ። ድርጅቱ ፍሳሽ ቆሻሻን ባልተገባ መንገድ ወደ ወንዝ ሲለቅ በመገኘቱ ቅጣቱ ተላልፎበታል ። ባለስልጣኑ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የወንዞች ዳርቻ ልማትና ብክለትን ለመከላከል በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 መሰረት ጠንካራ ክትትል በማድረግ አስታውቋል ። ባለስልጣኑ ተቋማትና ግለሰቦች ማንኛውም አይነት ቆሻሻ ወደ ወንዝና የወንዞች ዳርቻ ከመልቀቅ እንዲቆጠቡ እያሳሰበ ደንብ የሚተላለፉ ግለሰቦችና ተቋማትን እንደማይታገስና እርምጃውንም አጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳውቋል፡፡

ክብርት ከንቲባ አዳነች አቤቤ ኪነ ጥበብን በተመለከተ ከሰጡት ማብራሪያ :- 👉የአስተሳሰብና የተግባር አንድነት ለመገንባት ፣ ገዥ ትርክት ለመገንባት ፣ ሀገራዊ ገፅታን ለመገንባት የኪነ ጥበብ አቅም ከፍ ያለ በመሆኑ በትኩረት እየተሰራ ነው። 👉ነባሮችን ከማደስ ባሻገር ኪነ ጥበብ ከአዳራሽ ወጥታ ወደ ህዝብ ጠጋ እንድትል ፣ ወጣቶች እና ታዳጊዎች ክህሎታቸውን እንዲያወጡ 150 ፕላዛዎች ፣ 50 አንፊ ቴአትር ተገንብተዋል። 👉 ሙያዊ ነፃነታቸው እንዲከበር እራሳቸውን ችለው እንዲደራጁ የአሰራር ማሻሻያ ተደርጎላቸዋል። 👉 በሙያቸው ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ዜጐችን እንዲያፈሩ ፣ ቋሚ ገቢ እንዲያገኙም አበረታች ስራዎች ተከናውነዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ ስራ አስኪያጅ ፅ/ቤት ከጳጉሜ እስከ መስከረም አበይት የስራ ክንውኖች በምስል ሲቃኝ። ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች… See more

2025 የአፍሪካን ምርጥ 10 ከተሞችን ያወዳደር አንድ ቻናል አዲስ አበባን እንዲህ ሲል ገልጿታል

በመዲናዋ ጥራት ያለው የህክምና አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናገሩ :: የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በመዲናዋ ጥራት ያለው የህክምና አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ በርካታ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባኤውን አካሂዷል። በጉባኤው ላይ የምክር ቤቱ አባላት በተመረጡበት አካባቢ ከመራጭ ህዝብ ጋር ባደረጉት ውይይት የተነሱ የህዝብ ጥያቄዎችን ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ አቅርበዋል። ከቀረቡ ጥያቄዎች መካከል የመዲናዋን የጤና መሰረተ ልማት ሽፋን እና አገልግሎትን የተመለከተው ይገኝበታል። በመዲናዋ የጤና መሰረተ ልማት ተዳራሽነት ለማስፋት ከተማ አስተዳደሩ እያደረገ በሚገኘው እንቅስቃሴ ሆስፒታሎችን ከማደስ እና ከማሻሻል ባለፈ ሁለት አዳዲስ ሆስፒታሎች እየተገነቡ እንደሚገኝ ተገልጿል። የጤና መድህን ፣ የመድሀኒት አቅርቦት እና የባለሙያዎችን ቁጥር ማሳደግ ላይ ከተማ አስተዳደሩ የሰራቸው ስራዎች በምክር ቤት አባላቱ አድናቆት ተችሯቸዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የምክር ቤት አባላቱ ከማህበረሰቡ ጋር ባደረጉት ውይይት የጤና ጣቢያ እጥረት ያለባቸው አካባቢዎችን ችግር ለመቅረፍ ምን እንደታቀደ ተጠይቋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ በሰጡት ምላሽ በሁሉም ወረዳዎች ጤና ጣቢያ ከመገንባት ባለፈ የጥራት ደረጃቸውን ማሻሻል ላይ ትኩረት መደረጉን አንስተዋል። ለአብነትም በ2017 በጀት አመት 9 ጤና ጣቢያዎች በመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ጥራት መመዘኛ ተሰርተው ለአገልግሎት ክፍት መሆናቸውን ተናግረዋል። በተጨማሪም 13 ሆስፒታሎች የታደሱ ሲሆን የዘውዲቱ እና የሚኒሊክ ሆስፒታልን ጨምሮ 4 ሆስፒታሎች ላይ ማስፋፍያ እና እድሳት እየተከናወነ እንደሚገኝ ከንቲባዋ ጠቁመዋል። አዲስ አበባ በአለም ጤና ድርጅት መመዘኛ መሰረት የጤና ተደራሸነትን መልሳለች ያሉት ከንቲባ አዳነች፤ በቀጣይ የጥራት ደረጃን ማሻሻል እና መዲናዋን የሜዲካል ቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ ትኩረት እንደሚሰጥ ለምክር ቤቱ አብራርተዋል።