cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegaciĂłn. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

Best children of JESUS👫

ልጅ መሆን ዋጋው አይተመንም ውርሱ እራሱ እግዚአብሔር ነውና የደም ምልክት ያረፈባችሁ የኢየሱስ ምርጦች እናንተ ናችሁ። ለማንኛውም ሀሳብና በዚህ አካውንት ማግኘት ትችላላችሁ @Everytimeshine

Mostrar mĂĄs
Publicaciones publicitarias
401
Suscriptores
Sin datos24 horas
-17 dĂ­as
-530 dĂ­as

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

ዘፍጥረት 18 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁸ አብርሃም በእውነት ታላቅና ብርቱ ሕዝብ ይሆናልና፥ የምድር አሕዛብም ሁሉ በእርሱ ይባረካሉና። ¹⁹ ጽድቅንና ፍርድን በማድረግ የእግዚአብሔርን መንገድ ይጠብቁ ዘንድ ልጆቹንና ከእርሱ በኋላ ቤቱን እንዲያዝዝ አውቃለሁና፤ ይህም እግዚአብሔር በአብርሃም ላይ የተናገረውን ነገር ሁሉ ያመጣ ዘንድ ነው። https://t.me/bestchildrenofJESUS
Mostrar todo...
Best children of JESUS👫

ልጅ መሆን ዋጋው አይተመንም ውርሱ እራሱ እግዚአብሔር ነውና የደም ምልክት ያረፈባችሁ የኢየሱስ ምርጦች እናንተ ናችሁ። ለማንኛውም ሀሳብና በዚህ አካውንት ማግኘት ትችላላችሁ @Everytimeshine

Photo unavailableShow in Telegram
የሚያወራው አለው ማርያም አንድ ተአምር ያየች ይመስል በምትሰማው ነገር ቀልቧ ተሰርቋል ኢየሱስ ያውራል ማርያም ደግሞ እግሩ ስር ተቀምጣ ትሰማዋለች፤ ጓዳ ውስጥ ደግሞ እህቷ ማርታ ለኢየሱስ ምግብ ቢጤ ለመስራት ጉድ ጉድ እያለች ነው ለወትሮ ግን እንግዳ እዚህ ቤት ሲመጣ ለመስተንግዶ ማርያም ነበርች ጉድ ጉድ የምትለው ዛሬ ግን የምቶደው ኢየሱስ ቤቷ መጥቶ የጓዳውን ስራ አስረስቷታል..መቼም እንዲህ ቀልቧን የሰረቀውን ጉዳይ መስማት በጣም ያጓጓል ፤ ግን ምን ይሆን የሚያወራት ብለን ከጠየቅን መልሱን ፍለጋ ሩቅ መሄድ አይጠበቅብንም ለምን ካላቹኝ ያ ትናንት የማርያምን ቀልብ የሰረቀው ኢየሱስ ዛሬም ለሚሰሙት ልጆቹ የሚያወራው ስላለው፤ ኢየሱስ እንደ ማርያም እግሩ ስር ተቀምጦ የሚሰማው ካገኘ ዛሬም ልጄ ብሎ የሚያወራው ይኖረዋል፤ ማርያምን ሁኑለት። @thedayofpentecost @thedayofpentecost
Mostrar todo...
“ዳዊትም ጋድን፦ እጅግ ተጨንቄአለሁ፤ ምሕረቱ ብዙ ነውና በእግዚአብሔር እጅ እንውደቅ፤ በሰው እጅ ግን አልውደቅ አለው።” — 2ኛ ሳሙኤል 24፥14 👍ባለማስተዋል የምናደርገው ነገር እኮ ትውልድ ይቀጥፋል😭😭ለምን ግን🥹😭 ጌታን አለመስማታችን ዋጋ ያስከፍለናል😭በራስ የሀሳብ መስመር አንሂድ🥹 እኛ ባለመታዘዛችን ለሌሎች ጦስ አይትረፍ የእኛ መቀጫ ጅራፍ ምንም የማያውቀው ትውልድ ላይ አይረፍ🥹🥹😭 “ዳዊትም ሕዝቡን የሚመታውን መልእክ ባየ ጊዜ እግዚአብሔርን፦ እነሆ፥ እኔ በድያለሁ ጠማማም ሥራ እኔ አድርጌአለሁ፤ እነዚህ በጎች ግን እነርሱ ምን አደረጉ? እጅህ በእኔና በአባቴ ቤት ላይ እንድትሆን እለምንሃለሁ ብሎ ተናገረው።” — 2ኛ ሳሙኤል 24፥17
Mostrar todo...
4.95 MB
እግዚአብሔርን ቀኝ እንስጠው 😭😭 ምንም ብናጠፋ እሱ ይሻለናልና ወደ ሌላ ለመፍትሄ አንሂድ ሰሪያችን እጅ ላይ ሆነን ብንደክም ይሻለናል መታዘዝ መታዘዝ መታዘዝ 🔥🔥🔥 ለእግዚአብሔር የፍቅር መግለጫችን ነው😭😭 ከመዝሙራችን ከስብከታችን ከፀሎታችን ይልቅ እግዚአብሔር መታዘዛችን ነው የሚያስደስተው🥺🥺🔥🔥🙏🙏 ዋናችንን ካልታዘዝን ቆይተን የህይወት ድንጋጤ ውስጥ እንዳንገባ እንንቃ😭 “ሳሙኤልም፦ በውኑ የእግዚአብሔርን ቃል በመስማት ደስ እንደሚለው እግዚአብሔር በሚቃጠልና በሚታረድ መሥዋዕት ደስ ይለዋልን? እነሆ፥ መታዘዝ ከመሥዋዕት፥ ማዳመጥም የአውራ በግ ስብ ከማቅረብ ይበልጣል።”😭😭 — 1ኛ ሳሙኤል 15፥22
Mostrar todo...
8.23 MB
እግዚአብሔር የሚናገረው ነገር አለው እንስማው የልባችንን ደጃፍ ከከፈትንለት እሱ የሚለውን ከሰማነው ከጥፋት እናመልጣለን እንስማው ኢየሱስን🥹🥹😞 2ኛ ሳሙኤል 24 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁵ ዳዊትም ቸነፈሩን መረጠ፤ የስንዴም መከር ወራት በሆነ ጊዜ ቸነፈሩ በሕዝቡ መካከል ጀመረ፤ ከሕዝቡም ሰባ ሺህ ሰው ሞተ።😭😭 ¹⁶ የእግዚአብሔርም መልአክ ኢየሩሳሌምን ያጠፋት ዘንድ እጁን በዘረጋ ጊዜ እግዚአብሔር ስለ ክፉው ነገር አዘነ፥ ሕዝቡንም የሚያጠፋውን መልአክ፦ እንግዲህ በቃህ እጅህን መልስ አለው። የእግዚአብሔርም መልአክ በኢያቡሳዊው በኦርና አውድማ አጠገብ ነበረ።
Mostrar todo...
8.96 MB
“ነገር ግን የንጉሡ ቃል በኢዮአብና በሠራዊቱ አለቆች ላይ አሸነፈ። ኢዮአብና የሠራዊቱ አለቆችም የእስራኤልን ሕዝብ ይቈጥሩ ዘንድ ከንጉሥ ዘንድ ወጡ።” — 2ኛ ሳሙኤል 24፥4 👉እግዚአብሔርን ካልታዘዝንበት መንገድ እንመለስ😔ያለ ፈቃዱ ከተጓዝንበት መንድ ፀፅቶን እንመለስ😭😭ፈዘን በቸልታ ከምንኳትንበት አካሄዳችን እንንቃ🙌 “ሕዝቡንም ከቈጠረ በኋላ ዳዊትን ልቡ መታው፤ ዳዊትም እግዚአብሔርን፦ ባደረግሁት ነገር እጅግ በድያለሁ፤ አሁን ግን፥ አቤቱ፥ ታላቅ ስንፍና አድርጌአለሁና የባሪያህን ኃጢአት ታርቅ ዘንድ እለምንሃለሁ አለው።” — 2ኛ ሳሙኤል 24፥10
Mostrar todo...
7.02 MB
እግዚአብሔር ፊት ምን ለብሰን ነው ስህተታችንን የምንደብቀው ? እሱ ከአፍ ከሚወጣ ቃል ይልቅ በልብ ባህር የተቀመጠውን እውነተኛ ነገር ይፈልገዋል እግዚአብሔር በአፋችን ቃል በሰዎች ፊት ለታይታ የወደድነው እየመሰልን ብንኖር ምን ይጠቅመናል ራሳችንን እየታለልን ለምን ወደ አለመታዘዝ መክነፍ አስፈለገ? በእርሱ እይታ ውስጥ እንዳለን አውቀን በቅድስናና በፅድቅ በእውነትም ጎዳና እንመላለስ!! ✅እግዚአብሔር እውነተኛ መወደድን ይፈልጋል እርሱ አውነተኞችን ይፈልጋል ደግሞም ይወዳል✝ ኢሳይያስ 29 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁰ እግዚአብሔር የእንቅልፍ መንፈስ አፍስሶባችኋል ዓይኖቻችሁን ነቢያትንም ጨፍኖባችኋል ራሶቻችሁን ባለ ራእዮችን ሸፍኖባችኋል። ¹¹ ራእዩም ሁሉ እንደ ታተመ መጽሐፍ ቃል ሆኖባችኋል፤ ማንበብንም ለሚያውቅ፦ ይህን አንብብ ብለው በሰጡት ጊዜ እርሱ፦ ታትሞአልና አልችልም ይላቸዋል፤ ¹² ደግሞም መጽሐፉን ማንበብን ለማያውቅ፦ ይህን አንብብ ብለው በሰጡት ጊዜ እርሱ፦ ማንበብ አላውቅም ይላቸዋል። ¹³ ጌታም፦ ይህ ሕዝብ በአፉ ወደ እኔ ይቀርባልና፥ በከንፈሮቹም ያከብረኛልና፥ ልቡ ግን ከእኔ የራቀ ነውና፥ በሰዎች ሥርዓትና ትምህርት ብቻ ይፈራኛልና ¹⁴ ስለዚህ፥ እነሆ፥ ድንቅ ነገርን በዚህ ሕዝብ መካከል፥ ድንቅ ነገርን ተአምራትንም፥ እንደ ገና አደርጋለሁ፤ የጥበበኞችም ጥበብ ትጠፋለች፥ የአስተዋዮችም ማስተዋል ትሰወራለች። ¹⁵ ምክራቸውን ጥልቅ አድርገው ከእግዚአብሔር ለሚሰውሩ፥ ሥራቸውንም በጨለማ ውስጥ አድርገው፦ ማን ያየናል? ወይስ ማን ያውቀናል? ለሚሉ ወዮላቸው! ¹⁶ ይህ የእናንተ ጠማምነት ነው፤ እንደ ሸክላ ሠሪ ጭቃ የምትቈጠሩ አይደላችሁምን? በውኑ ሥራ ሠሪውን፦ አልሠራኸኝም ይለዋልን? ወይስ የተደረገው አድራጊውን፦ አታስተውልም ይለዋልን? ¹⁷ ሊባኖስ እንደ ፍሬያማ እርሻ ሊለወጥ ፍሬያማውም እርሻ እንደ ዱር ሊቈጠር ጥቂት ዘመን የቀረ አይደለምን? ¹⁸ በዚያም ቀን ደንቆሮች የመጽሐፍን ቃል ይሰማሉ፥ የዕውሮችም ዓይኖች ከጭጋግና ከጨለማ ተለይተው ያያሉ። ¹⁹ የዋሃን ደስታቸውን በእግዚአብሔር ያበዛሉ፥ በሰዎች መካከል ያሉ ችግረኞችም ሐሤትን በእስራኤል ቅዱስ ያደርጋሉ። 🫵ጆሮ ያለው ይስማ 🦻ለተናጋሪው ለሰማይ አምላክ የነፍሱን ምላሽ ያሰማ ወደ እግዚአብሔር መንገድ ጉዟችንን ሸክፈን ከሄድንበት ያለመታዘዝ ቀይ መስመር እንመለስ🚶 https://t.me/bestchildrenofJESUS
Mostrar todo...
Best children of JESUS👫

ልጅ መሆን ዋጋው አይተመንም ውርሱ እራሱ እግዚአብሔር ነውና የደም ምልክት ያረፈባችሁ የኢየሱስ ምርጦች እናንተ ናችሁ። ለማንኛውም ሀሳብና በዚህ አካውንት ማግኘት ትችላላችሁ @Everytimeshine

መዝሙር 119 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁷⁹ የሚፈሩህና ምስክሮችህን የሚያውቁ ወደ እኔ ይመለሱ። ⁸⁰ እንዳላፍር ልቤ በሥርዓትህ የቀና ይሁን። ⁸¹ ነፍሴ መድኃኒትህን ናፈቀች፤ በቃልህም ታመንሁ። ⁸² መቼ ታጽናናኛለህ እያልሁ ዓይኖቼ ስለ ቃልህ ፈዘዙ። ⁸³ በጢስ እንዳለ አቁማዳ ሆኛለሁና ሥርዓትህን ግን አልረሳሁም። ⁸⁴ የባሪያህ ዘመኖች ስንት ናቸው? በሚያሳድዱኝስ ላይ መቼ ትፈርድልኛለህ? ⁸⁵ ኃጢአተኞች ጨዋታን ነገሩኝ፥ አቤቱ፥ እንደ ሕግህ ግን አይደለም። https://t.me/bestchildrenofJESUS
Mostrar todo...
Best children of JESUS👫

ልጅ መሆን ዋጋው አይተመንም ውርሱ እራሱ እግዚአብሔር ነውና የደም ምልክት ያረፈባችሁ የኢየሱስ ምርጦች እናንተ ናችሁ። ለማንኛውም ሀሳብና በዚህ አካውንት ማግኘት ትችላላችሁ @Everytimeshine

መክብብ 1 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁸ ነገር ሁሉ ያደክማል፤ ሰው ይናገረው ዘንድ አይችልም፤ ዓይን ከማየት አይጠግብም፥ ጆሮም ከመስማት አይሞላም። ⁹ የሆነው ነገር እርሱ የሚሆን ነው፥ የተደረገውም ነገር እርሱ የሚደረግ ነው፤ ከፀሐይም በታች አዲስ ነገር የለም። https://t.me/bestchildrenofJESUS
Mostrar todo...
Best children of JESUS👫

ልጅ መሆን ዋጋው አይተመንም ውርሱ እራሱ እግዚአብሔር ነውና የደም ምልክት ያረፈባችሁ የኢየሱስ ምርጦች እናንተ ናችሁ። ለማንኛውም ሀሳብና በዚህ አካውንት ማግኘት ትችላላችሁ @Everytimeshine

Elige un Plan Diferente

Tu plan actual sĂłlo permite el anĂĄlisis de 5 canales. Para obtener mĂĄs, elige otro plan.