Broken words
ωειι сомε το my channel ❤️😊 ιονειγ_ριc τικ_τοκ & #ροεм Amazing fact мемеs & #jοκε Cross or any comment 👇 👇👇 @mer563 https://t.me/broken356
Mostrar másEl país no está especificadoEl idioma no está especificadoLa categoría no está especificada
906
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
Sin datos30 días
- Suscriptores
- Cobertura postal
- ER - ratio de compromiso
Carga de datos en curso...
Tasa de crecimiento de suscriptores
Carga de datos en curso...
Photo unavailableShow in Telegram
አንገትሽ ጉማሬ
ግምባርሽ የበሬ
ቀለምሽ ጥቀርሻ
ቂጥሽ ማንከሽከሻ
ፈጣሪ ያሳየኝ
ያንቺን መጨረሻ
#እርሱ
#ኤልያስ_ሽታኹን
የተፉበት ንቀት ምራቅ
ፀሀይ መውጫ ዓይኑ ምስራቅ
እሾህ ንቀት ሰጡት አክሊል
ሸክሙ ልዝቅ ቀንበር ቀሊል
ቀዳደዱት ቀሚስ ልብሱ
ባህር ያለ እሳት እርሱ።
#እርሱ
ጉልበታቸው የቅዱሳን
የካህናት ዜማ ልሳን
የዓለም ገዢ ስሙ ንጉሥ
ጸንቶ ያለ ያለምርኩዝ...
#እርሱ
አምላክ ነው ሚገዛ
በቀይ ደም የወዛ
ጌታ ነው ለባህር
ጌታ ነው ለየብሱ
የዓለም የጊዜ የማያረጅ ልብሱ።
#እርሱ
ሲጠሩት እንደልጅ
የሚያውቁት እንደእጅ
ለጠላት አሳዳጅ
ሲለምኑት ወጃጅ
አሜን ሲሉት ሰጪ
ቂሜን ሲሉት ቀጪ
የአባት ያህል ገፁ
የእናት ያህል ድምፁ።
#እርሱ
የሰማይ አሞራ ልጠይቅሽ ወሬ
ተቃጠለ መሰል ሸተተኝ ሀገሬ
ልክ እንደ ፈንድሻ የበቆሎ ፍሬ
ከላይ እየሳቀች ነደደች ሀገሬ
ማሽላና ስንዴ ባንድ አብረን ስንቆላ
እያረረ ሳቀ የባህር ማሽላ
ከሰል የሚሆኑ ብዙ እንጨቶች ሳሉ
ዝግባ ለምን ይሆን ይቆረጥ የሚሉ
፡
የሞት ህመም ይዟት ኢትዮጵያ ታማለች
ጌታ ሆይ መድኃኒት ካንተ ዘንድ ትሻለች
🇪🇹🇪🇹🇪🇹
° ° #አምላክ_ሀገራችንን_ይባርክ
ባልሽ የት ሄደ ...?
ባልሽ የት ሄደ…………… አሰላ
ምን ለብሶ………………..ነጠላ
ለዛ ነው ሚበርደኝ : አጥንቴን ሰርስሮ፣
የጀገንኩበትን … ጉልበቴን ሰባብሮ ።
**
ነጠላሽ ነጠላው : በአንድነት ተገምደው፣
የልባችሁ ርቀት : በክሮች ተዛምደው...
መኖር ስትችሉ ……መለያየት ሳይኖር፣
እርሱም ወደ አሰላ… ወደ መራው መንደር፣
አንቺም ወደ ማጀት … ወደ ሰጡሽ ስፍር።(ሴት ለማጀት_የተሰፈረላት)
**
ታወቀኝ ነጠላሽ : ብርድ እንዳስገባብሽ፣
አስታውቆኛል ዛሬም … ተሰምቶኝ ህመምሽ፣
አፍቃሪ እኮ እንዲህ ነው … አንዳች ሳይንቋሸሽ…
ያደምጣል ዝምታን : የፍቅሩን እስትንፋስ : ጆሮዎቹን ሰብቆ፣
ልቡን በፅሞና …… ከልብሽ ሸምቆ።
****
የባልሽ ቂጣ … እንክትክቱ ይውጣ
ብዬ አልራገም : የእህል አምላኩ : ክፉ እንዳይቆጣ፣
አውቅሻለሁ ፍቅር : ፅኑ እምነት አለሽ : ባልሽ እስኪመጣ፣
ከእርሱ ጋር ነውና … የመዳፍሽ ዕጣ፣
የልጅነታችን …….....ናፍቆቴን ልወጣ፣
ባልሽ ሳይመጣ …… ሳሚኝና ልውጣ።
★"በታክሲ ስትሄድ አንድ ጋጠወጥ ሰው ቢገጥምህና የማይሆን ቃል ቢናገርህ ለርሱ ቦታ አትስጠው አንዱ ፌርማታ ላይ ይወርዳል ፣ ከዚያ በኋላ አታገኘውም ። አንተን ግን ቀኑን ሙሉ ሲበጠብጥህ ይውላል ።"
★"ቁንጫ የጠረጉት ዕለት ባለጌም የመከሩት ዕለት ይብሰዋል" እንዲሉ ምክር ለሁሉ አይሰጥም ፣ መልስ ለሁሉም አይመለስም ፣ ክርክር ከሁሉም ጋር አይደረግም ። "
🎤መጋቤ ሀዲስ እሸቱ አለማየሁ
መልካም ዕለት
አንድ ብዙዎች አንገታቸውን የሚያቀረቅሩበት ቀን አለ ሲያወድሱት የነበረው ክፉ፤ ሲሳለቁበት የነበረው ደግሞ ጀግና እንደነበር የሚረዱበት!
👉ቶሎ አውቆ ቶሎ ሚሰለች!
👉ቶሎ ተግባብቶ ቶሎ ሚቀየር!
👉ቀድሞ ፈጥኖ ቀድሞ ሚለዝብ! እንዲሕ አይነት ባህሪ ካለን ለወረት አብዝተን የተጋለጥን ነን! ይህም ከጥቅም ፍለጋ የተነሳና እራስን ከተግባቢነትና አቅም ካላቸው ተርታ በፍጥነት ማሰለፍ ስለምንፈልግ ነው።
👉በጥሞና ነገሮችን ሚመረምር!
👉መቸኮል ለጥፋት እንደሚዳርግ የተረዳ!
👉ነገራቶችን በመልካም አይን የሚያይ!
👉በማስተዋል የተካነ እና ጥራት ያለው ተግባራትን ሚፈጽም ሰው ስለ ስራው እርሱ ባያወራው እንኳ ተግባሩ አንደበት አውጥቶ ያወራል!!! እንዲህ አይነት ሰው መቸኮል ባህሪው ስላልሆነ እያደር እንደሚጥም ቀስ በቀስ በመላመድ ውስጥ ጠንከር ያለ ወዳጅነትን በመገንባት ፤ በስራው ጥራት ካሰበበት ከፍታ ላይ ይደርሳል!!!
Watch "🔴 አዲስ የበገና ዝማሬ | "የማይሞተው ሞተ" | ዘማሪ ዳንኤል ጥበበ ሥላሴ" on YouTube
https://youtu.be/YMBzAScE34g
🔴 አዲስ የበገና ዝማሬ | "የማይሞተው ሞተ" | ዘማሪ ዳንኤል ጥበበ ሥላሴ
በማኅቶት ቲዩብ የተለቀቁ ተወዳጅ መዝሙሮችን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፡፡ 👇 👇 👇
https://bit.ly/3C2YHGp🔴አዲስ የበገና ዝማሬ | "የማይሞተው ሞተ" | ዘማሪ ዳንኤል ጥበበ ሥላሴ
Photo unavailableShow in Telegram
አ'ያ ዕድል
አንድ ሰሞን ቀን አንግሶ
አንድ ሰሞን ቀን'ህ ሲሽር፤
እንደ ቀላል አነጣጥፎ
እንደ ቀላል ሲመነሽር!
አንድ ሰሞን ጊዜ አንስቶ
አንድ ሰሞን ጊዜ ሲጥል፤
እንደ ቀላል አሞጋግሶ
እንደ ቀላል ሲያብጠለጥል!
በአንድ ሁናቴ ዘመን ክቦ፥
እንደ አህያ አንከብክቦ፥
ፈጣሪህን አሸክሞ...
በሰዎች ልብስ ተረጋጠህ፥
በዘንባባው ተረማምደህ፥
ተብሎልህ "እልል እልል"፤
በማግስቱ በስልቻ
ትጫናለህ ኩንታል እህል!
#ዕድል