es
Feedback
የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መዝሙር 🇪🇹

የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መዝሙር 🇪🇹

Ir al canal en Telegram

@Tewahdo27 የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መዝሙሮች 🌠በዝህ ቻናል የተለያዩ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ መዝሙሮች የሚያገኙበት ቻናል ነው። መራግብራችን :-👇 ✅መዝሙሮች✅ የንስሐ መዝሙሮች✅ ያሬዳዊ ዜማ✅ የማርያም ውዳሴዎች✅ መፅሐፍ ሀይማኖት........ ወ.ዘ.ተ 🔵 YouTube 🔴ለሃሳብ እና አስታያየት @Tewahdo27

Mostrar más
5 117
Suscriptores
-524 horas
-197 días
-6330 días
Archivo de publicaciones
ባለጠጋ ለመሆን የሚፈልጉ ግን ወደ ፈተናና ወደ ወጥመድ፣ እንዲሁም ሰዎችን ወደ መፍረስና ወደ ጥፋት ወደሚያዘቅጠው ወደ ብዙ ከንቱና ክፉ ምኞት ይወድቃሉ። 1 ጢሞቴዎስ 6፥9 ይህ መልእክት በገንዘብ ባለ ጠጋ ለሆኑ ሰዎች የተጻፈ አይደለም። በፍጹም፣ ይህ ሀብትን ለምንፈልግ ለሁላችንም የተጻፈ መልእክት ነው። ምድራዊ ሀብትን አጥብቆ መፈለግና ማሳደድ ለብዙ አስከፊ ችግሮች ይዳርገናል። የምናየውን ነገር ሁሉ እንድንፈልግ በሚናገሩ ማስታወቂያዎችና የማኅበራዊ ሚዲያ መልእክቶች በሞላበት ዓለም ውስጥ፣ "አትመኝ..." ዛሬም ከእግዚአብሔር ዐሥርቱ ትእዛዛት መኻል አንዱ መሆኑን ማስታወስ አለብን። ኢየሱስ ይህን መከላከል እንችል ዘንድ ሌላ ትእዛዝን ሰጥቶናል፤ "ከሁሉ አስቀድማችሁ ግን የእግዚአብሔርን መንግሥትና ጽድቁን ፈልጉ፤ እነዚህም ሁሉ ይጨመሩላችኋል" (ማቴ. 6፥33)። https://kedusbible.com

ኖኅ ግን በ እግዚአብሔር ዘንድ ሞገስን አገኘ። ዘፍጥረት 6፥8 ይህ ምንባብ ኢየሱስ በተጠመቀ ጊዜ እግዚአብሔር የተናገረውን ያስታውሰኛል፤"...በአንተ ደስ ይለኛል" (ሉቃስ 3፥21-22)። ኖኅ በኖረበት ኀጢአት በነገሠበት ባህል ውስጥ እርሱ ግን የተለየ ነበር! እግዚአብሔር የኖኅን ልብ ታማኝ ሆኖ አግኝቶታል፤ በዚህም ለርሱና ለቤተ ሰቡ በረከትን አምጥቷል፤ የዓለምንም ወደፊት አመቻችቷል። በእግዚአብሔርና በመንገዱ ላይ ዐመፃ በሞላበት ዓለም ውስጥ በጽድቅ፣ በርኅራኄና በታማኝነት መኖር ከባድ ነው። "ነገር ግን ኖኅ በእግዚአብሔር ዘንድ ሞገስን አገኘ፤" ብርሃን በሌለበት ዓለም ላይ ለእግዚአብሔር ስንኖር ለእኛም እንዲሁ ይሁን። በሥራዎቻችን፣ በትምህርት ቤታችን፣ በሰፈራችን፣ በጓደኝነታችንና በምንዝናናበት ስፍራ ሁሉ ብርሃን እንሁን። ሁላችን እንደ ኖኅ ለመሆን ብንወስን ምን ያህል ለውጥ ማምጣት እንደምንችል ዐስባችሁታል? https://kedusbible.com

አትታለሉ፤ እግዚአብሔር አይዘበትበትም። ሰው የሚዘራውን ያንኑ ያጭዳል። ገላትያ 6፥7 እግዚአብሔርን አናታልለውም። ዓለማችን የሚሠራበትን መሠረታዊ መርሕን ልናመልጥ አንችልም። ለሌሎች ሰዎች ማስመሰል ብንችልም እግዚአብሔር ልባችንን ያውቃል። ልባችን ትኲረት ያደረገበትና ሁሉን የሰጠበት ነገር በስተመጨረሻ በሕይወታችን ውስጥ ይገለጣል። የዘራነውን ያንኑ እናጭዳለን! ስለዚህ፣ ሀብታችንን፣ ጊዜያችንንና ጕልበታችንን ለራሳችን ብንሰጥና ለእግዚአብሔር ደግሞ የቀረውን ብንሰጥ ብዙ መንፈሳዊ በረከቶችን አናገኝም። ለሌሎች የምናደርገውም ነገሮች እጅግ አስፈላጊ ናቸው፤ መልካምንም እናጭዳለን። ራሳችንን እንደምንወድድ ባልንጀሮቻችንንም ልንወድድ ይገባል። ምክንያቱም፣ እያንዳንዱ ሰው ለእግዚአብሔር ዋጋ ስላለው ለእኛም ዋጋ ሊኖረው ይገባል። እግዚአብሔር የሚወድደውን ዘር እንዝራ፤ ከዚያም እኛንና በዙሪያችን ያሉ ሰዎችን የሚባርክ በረከትን እናጭዳለን! https://kedusbible.com

አንተ ግን ስትጸልይ ወደ ክፍልህ ግባ፤ በሩንም ዘግተህ በስውር ወዳለው አባትህ ጸልይ፤ በስውር የተደረገውን የሚያይ አባትህም ዋጋህን ይከፍልሃል። ማቴዎስ 6፥6 ጸሎት በልባችን ያለውን ነገር ለእግዚአብሔር ማጋራት የምንችልበት እርሱ የሰጠን አስደናቂ ጥሪ ነው። ቃላት ባጠረን ጊዜ እንኳ፣ ሙሉ ለሙሉ እንደተሰማን እናውቅ ዘንድ በመንፈሱ ይረዳናል (ሮሜ 8፥26-27)። ይህ በውዱና በኀያሉ የእግዚአብሔር መንፈስ የሚደገፍ ጥብቅ ግንኙነት፣ ለታይታና ለትዕቢት መጠቀም የለብንም (ማቴዎስ 6፥5)። ጸሎት ለሌሎች ቅድስናችንን የምናስመሰክርበት መሣሪያ ሳይሆን ከሁሉን ቻዩ እግዚአብሔር ጋራ ያለንን ግንኙነት የምናጠብቅበት፣ አባታችን እንደሚሰማን፣ ስለ ሕልሞቻችንና ተስፋዎቻችን፣ ስለ ፈተናዎቻችንና ስለሚያስጨንቁን ነገሮች እንደሚያውቅና እንደሚጠነቀቅልን ለልባችን የምናረጋግጥበት መንገድ ነው። https://kedusbible.com

የማትገመት ሰዉ ሁን ስልክከን አዉጣና ለአሪሲ ኦርቶዶክሳዊያን ድምፅ ሁናቸው!!!!! Repost!!!!!!!! https://vt.tiktok.com/ZSQLL4Ro2/
+1
የማትገመት ሰዉ ሁን   ስልክከን አዉጣና ለአሪሲ ኦርቶዶክሳዊያን ድምፅ         ሁናቸው!!!!! Repost!!!!!!!! https://vt.tiktok.com/ZSQLL4Ro2/

ወደ ኀላ ዞር ብለን ካየን በእግዚአብሔር ያላለፍነዉ ምን አለ ግን?

የትንሣኤ እሳት | መምህር ሔኖክ ኃይሌhttps://youtube.com/shorts/7T1CAo-38gY?si=LZEb1dKuW9tdmvOB

ቀዳም ስዑር || ዲያቆን ሔኖክ ሃይሌ #ቀዳምስዑር https://youtube.com/shorts/UJC91THXhFk?si=oIShvb-TMtO5BIz_

"ተፈጸመ አለ፥ ራሱንም አዘንብሎ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ" (ዮሐ 19፥30)
+5
"ተፈጸመ አለ፥ ራሱንም አዘንብሎ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ" (ዮሐ 19፥30)

“በሙሴ ሕግና በነቢያት በመዝሙርም ስለ እኔ የተጻፈው ሁሉ ይፈጸም ዘንድ ይገባል አላቸው።” - ሉቃ 24፡44
“በሙሴ ሕግና በነቢያት በመዝሙርም ስለ እኔ የተጻፈው ሁሉ ይፈጸም ዘንድ ይገባል አላቸው።” - ሉቃ 24፡44