cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

ማኅበረ ቅዱሳን ሩቅ ምሥራቅ ማዕከል

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ይህ ቻናል የማኅበረ ቅዱሳን ሩቅ ምሥራቅ ማዕከል መረጃ መቀበያ እና ማስተላለፊያ ነው። ያሎትን ሀሳብ ፣ አስተያየት እና ጥያቄዎች ይህን @MKfareastbot የውስጥ መቀበያና ማስተላለፊያ ሳጥን በመጠቀም ያስፍሩልን። https://www.youtube.com/@MKFEC-Media ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን!

Mostrar más
Publicaciones publicitarias
967
Suscriptores
Sin datos24 horas
+207 días
+7030 días

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

Mostrar todo...
"ዋይ ዜማ መንፈሳዊ ግጥም"ZwT||ዜማ ወጥበብ ዘማኅበረ ቅዱሳን (Official Video)

"ዋይ ዜማ መንፈሳዊ ግጥም"ZwT||ዜማ ወጥበብ ዘማኅበረ ቅዱሳን (Official Video) #MKZwT#ዜማወጥበብዘማኅበረቅዱሳን#Mahiberekidusan Subscribe:

https://www.youtube.com/channel/UC2U27bED0bj7ONXPNmBEKmA

Telegram:

https://t.me/+5e0PniMWKnsyMWFh

Photo unavailableShow in Telegram
Topic :የአርብ ጸሎትና ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ የልምድ ልውውጥ መርሐ ግብር (ክፍል ሁለት) ሰዓት:በኢትዮጵያ አቆጣጠር 10:00 ሰዓት (9:00BJT) ቦታ: Zoom Meeting https://us02web.zoom.us/j/89212264330?pwd=MjM3S3JxUGxMb2NyaGRiQ3JybEhGQT09 Meeting ID: 892 1226 4330 Passcode:123456 ማ/ቅ ሩቅ ምሥራቅ ማእከል ትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ዋና ክፍል
Mostrar todo...
👆👆👆👆👆👆👆 #በዝክረ ቅዱስ ያሬድ የተካሄዱ መርሐግብራት
Mostrar todo...
በእኅት ደብሪቱ
Mostrar todo...
2
"ያልተዋኘ ባሕር" በመምህር ኃይሌ አርአያ
Mostrar todo...
በዲያቆን ግርማ
Mostrar todo...
የፍልስፍና ትምህርትን ከአንድራጋቶስ የንግግር ጥበብን ከሊባንዮስ አብሮት ከተማረው ጓደኛው ከታላቁ ባስልዮስ ጋር አብረው እውነተኛውን ሕይወትና ፍልስፍና መኖር ጀመሩ። ቅዱስ ዳዊት በመዝሙሩ ‹‹ከቸር ሰው ጋር ቸር ሆነህ ትገኛለህ፤ ከቅን ሰው ጋር ቅን ሆነህ ትገኛለህ፤ ከንጹሕ ጋር ንጹሕ ሆነህ ትገኛለህ፤ ከጠማማም ጋር ጠማማ ሆነህ ትገኛለህ›› በማለት እንደ ገለጸው። (መዝ.፲፰፥፳፭-፳፮) የሁለቱ የጓደኝነት ሕይወትም በንጽሕና ያሸበረቀ እንደ ዕንቁ የሚያበራ እንደ ወርቅ የጠራ ነበር። ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ስለ ጓደኛው ቅዱስ ባስልዮስ ሲናገር እንዲህ ይላል፤ ‹‹እርሱ ከክብር ወደ ክብር ከቅድስና ወደ ቅድስና ከፍ እያለ ሄደ፡፡›› በዚህም ለክህነት ሲታጩ ዮሐንስ አፈወርቅ ‹‹እኔ ለክህነት የበቃሁ አይደለሁም፤ ወንድሜ ግን ክህነት ይገባዋል›› በማለት አብረው ከጸናበት አቋሙ ከቅዱስ ባስልዮስ ጋር ለጊዜው ቢስማሙም በኋላ ግን ቅዱስ ባስልዮስ ለጊዜው አሠረ ክህነትን ሊቀበል እንደ ቀረ በእንተ ክህነተ የተሰኘው መጽሐፉ ይነግረናል። ክህነት ምን ያህል የከበረ እንደሆነም በቅዳሴው ‹‹ከባሕርይ አባቱ ከአብ ጋር በልዕልና የሚቀመጥ እርሱ በዚያች ሰዓት በሁሉም ካህናት እጅ ይያዛል፤ ሊቀበሉትና ሊዋሐዱት ለሚፈልጉትም ለሁሉም ራሱን ይሰጣል። ወዮ የእግዚአብሔር ቸርነት ምን ይደንቅ? ምን ይረቅ? መጠንና ልክ የሌለውን እሳት በእጁ የሚይዝ ካህን!›› በማለት የክህነትን ታላቅነት አሳይቷል፡፡ ለወንድሙ ቅዱስ ባስልዮስ በላከው መልእክቱ ደግሞ ‹‹ክርስቶስ እንደሚፈልገው አድርጌ ይህን ኃላፊነት ለመወጣት የበቃሁ ሆኜ ሳለሁ እምቢ ብዬ ሸሽቼ ቢሆን ኖሮ አነጋገሬ ሰዎችን ሊያጠራጥራቸው በቻለም ነበር። ነገር ግን የመንፈሴ ደካማነት ለዚህ አገልግሎት የማልጠቅም ስለሚያደርገኝ ንግግሬ ለምን በጥያቄ ውስጥ ይወድቃል? መንጋው በደኅናና በጥሩ ምግብና ላይ ሳለ የጥበቃውን ኃላፊነት ብወስድና ከዚያ በኋላ ግን በእኔ አላዋቂነትና ጥበብ የለሽነት ምክንያት ባጠፋቸው እነርሱን ለማዳንና ለመቤዠት ሲል ራሱን የሰጠላቸውን እግዚአብሔርን በራሴ ላይ አነሳሳዋለሁ ብዬ እፈራለሁና›› ሲል ተናግሯል፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ከክህነት ሸሽቶ መኖር ቢፈልግም ወደ ክህነት መምጣቱ አልቀረም። በአንዲት ሌሊትም ሲጸልይ የእግዚአብሔር መልአክ እንደ በረድ ነጭ በሆነ ልብስ ተገለጠለት፤ ቅዱስ ዮሐንስም ሲያየው ደንግጦ በምድር ላይ ወደቀ፤ መልአኩም አርአያውን ለውጦ እንደ ሰው ሆኖ ታየው፤ ‹‹ወዳጄ አዲስ ዳንኤል ሆይ፤ አትፍራ፤ ተነሣ›› አለው። መልአኩ አዲስ ዳንኤል ብሎ የተጠራበት ምክንያት የናቡከደነፆር ራእይ ንባቡ ከነትርጓሜው ከጠፋ በኋላ ንባቡ ከነትርጓሜው በመንፈስ ቅዱስ ተገልጾለት እንደተናገረ እርሱም ራእየ ዮሐንስን ንባቡ ከነትርጓሜው ከጠፋ በኋላ በመንፈስ ቅዱስ ተገልጾለት ተርጉሞታልና። ዳግመኛም ዳንኤል ጸዋሚ ተሐራሚ እንደሆነ ሁሉ እርሱም ጸዋሚ ተሐራሚ በመሆኑ ዳንኤል ሐዲስ ብሎታል። የቅዱስ ዮሐንስም ልቡናው ተጽናንቶ ‹‹ጌታዬ አንተ ማን ነህ? ግርማህ አስፈርቶኛልና›› አለው የእግዚአብሔር መልአክም ‹‹ትሠራው ዘንድ የሚገባህን ልነግርህ ወደ አንተ የተላኩ ነኝ›› አለው። ‹‹አሁንም እግዚአብሔር አምላክ ያዘዘህን ለመሥራት ልብህን አበርታ፤ ቃልህ ከጽንፍ እስከ ጽንፍ በአራቱ ማእዘን ይደርሳልና። እልፍ አእላፍትም ትምህርትህን ተቀብለው ትእዛዝህን ሰምተው ወደ ፈጣሪያቸው እግዚአብሔር ተመልሰው ይድናሉና። በእግዚአብሔር መንግሥት ውስጥ የጸና የብርሃን ዓምድ ትሆናለህ። እነሆ የአንጾኪያ ሊቀ ጳጳስ ወደ አንተ ይመጣል፤ የሚያዝዝህንም አድርግ፤ የእግዚአብሔር ትእዛዝ ነውና ልትተላለፍ አይገባህም›› አለው፡፡ ከዚያም በኋላ ያ መልአክ ለአባ ፊላትያኖስ ተገልጦ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅን ቅስና እንዲሾመው አዘዘው። በማግሥቱም ሊቀ ጳጳሳቱ መጣ ከእርሱ ጋራም ካህናት አሉ ቅዱስ ዮሐንስንም ይዞ ቅስና ሾመው። የቊስጥንጥንያ ሊቀ ጳጳስ ባረፈ ጊዜ ንጉሥ አርቃዲዮስ ልኮ አስመጥቶ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅን በቊስጥንጥንያ ላይ ሊቀ ጵጵስና እንዲሾም አደረገው። ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅም እንደ አባቶቹ በጵጵስናው ሥራ ጸና፤ ሕይወትነት ባላቸው ትምህርቶችና ተግሣጾች ሕዝቡን ሁልጊዜ የሚያስተምር ሆነ። ማንንም ሳይፈራ ሕግ ተላላፊዎችን ከቤተ መንግሥትም ከቤተ ክህነት ወገንም ይገሥፃቸው ጀመር። በዚህም ፊት አይቶ የማያዳላ መምህና መገሥፅ በመባል የሚታወቅ ሆነ። አንድ ቀን የንጉሥ አርቃዲዮስ ሚስት አውዶክስያ የአንዲት ድኃ መበለት ቦታዋን በግፍ ወሰደች፤ ያች መበለትም ወደ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ መጥታ ንግሥቲቱ ቦታዋን እንደ ነጠቀቻት ነገረችው። እርሱም ‹‹የድኃዋን ቦታ መልሽላት›› ብሎ ከብዙ ምክር ጋር እንድትመልስላት ንግሥቲቱን ለመናት፤ እርሷ ግን እንቢ አለች። ቅዱስ ዮሐንስም ስለ አንዲት መበለት ንግሥቲቱን ሳያፍርና ሳይፈራ ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብታ ሥጋውን ደሙን እንዳትቀበል አውግዞ ለያት። ንግሥቲቱም እርሱ ከሹመት የሚሻርበትን ነገር መሥራት ጀመረች፤ ስለ ክፉ ሥራቸው ከሹመታቸው እርሱ የሻራቸውን ኤጲስቆጶሳት ሰበሰበች፤ እነርሱም ንግሥቲቱን ስለተቃወመ ስደት እንደሚገባው ተስማምተው ጻፉ፤ እርሷም አጥራክያ ወደ ሚባል ደሴት ሰደደችው። የሮሜ ንጉሥ አኖሬዎስና ሊቀ ጳጳሳቱ ዮናክኒዶስ ስለ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ስደት በሰሙ ጊዜ እጅግ አዘኑ፤ በንጉሥ አርቃድዮስ ላይም እንዲህ የሚል ደብዳቤ ጽፈው ላኩ፤ ‹‹ከዚህ ከክፉ ሥራ ተጠበቅ፤ ትእዛዛችንንም ተቀብለህ የከበረ ዮሐንስን ከስደቱ ካልመለስከው በአንተና በእኛ መካከል ሰላም አይኖርም።›› መልእክታቸውንም ባነበበ ጊዜ እጅግ አዘነ፤ ሚስቱንም አግዶ ልኮ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅን ከስደቱ መለሰው። ከጥቂት ቀኖችም በኋላ ንግሥቲቱ ወደ ክፋቷ ተመልሳ ሁለተኛ ወደ አጥራክያ ደሴት ሰደደችውና በዚያው ዐረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፤ እኛንም በዚህ አባት ጸሎት ይማረን፤ በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር አሜን። ምንጭ፡-ስንክሳር ዘወርኃ ግንቦት ፲፪፤ ድርሳን ዘቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ (የታሪክ አምድ)፤በእንተ ክህነት በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ገብረ እግዚአብሔር ኪዴ እንደተረጎመው፤ ጽዋኤ በዲያቆን ታደሰ ወርቁ፤የቅዱስ ዮሐንስ ሕይወቱና ትምህርቱ በዲያቆን ያረጋል አበጋዝ
Mostrar todo...
👍 3 1