cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

My unexplained feelings

Hlw everyone this is a channel where u can find psychological facts, memes & pp too we hope u enjoy it😊 For any comments @b_amlak19 @Mekinat

Mostrar más
El país no está especificadoEl idioma no está especificadoLa categoría no está especificada
Publicaciones publicitarias
160
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
Sin datos30 días

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

#የአባ_እንጦንስ_ምክሮች ✞ ከዕለታት በአንድ ቀን አባ ፓምቦ አባ እንጦስን "ማድረግ ያለብኝ ነገር ምንድን ነው?" ብሎ ይጠይቃል።አባ እንጦስም እንዲህ ሲል መለሰለት "በራስህ ጽድቅ አትታመን፤ላለፈው አትጨነቅ፤ይልቁኑ አንደበትህንና ሆድህን ግዛ።" ✞ አባ እንጦስ በአንድ ወቅት እንዲህ አለ፦ "በዚች ምድር ላይ ስንኖር ህይወታችንንም ሆነ ሞታችን ከባልጀራችን ጋር ነው። ወንድማችንን ገንዘብ ካደረግነው እግዚአብሔርን ገንዘብ እናደርጋለን፤ ወንድማችንን ካስቀየምነው ግን በክርስቶስ ላይ ኃጢአትን እናመጣለን።" ✞ በአንድ ወቅት አንድ ወንድም አባ እንጦስን "ጸልይልኝ" በማለት ይጠይቃል። እንጦስም "አንተ ራስህ ጥረት የማታደርግና ወደ እግዚአብሔር የማትጸልይ ከሆነ እኔም ሆንሁ እግዚአብሔር ምህረት ልናደርግልህ አንችም" አለው። ✞ እግዚአብሔር ሆይ አፈርና ትቢያ ሆኜ ሳለ ጻድቅ አድርገው ከሚቆጥሩኝ ሰዎች አድነኝ። ✞ ኃጢአታችንን እኛ እያሰብን የምንፀፀት ከሆነ እግዚአብሔር ይረሳልናል፤ ኃጥያታችንን እኛ እረስትን የምንፅናና ከሆነ እግዚአብሔር ያስብብናል። ✞ ብዙ ጊዜ ሰዎች ብልህ ነን እያሉ ይሳሳታሉ። ነገር ግን ብልህ የሚባሉት ብዙ የተማሩና ብዙ ያነበቡ ብዙ የሚናገሩ ብቻ አይደሉም። ይልቁንም ጠቢባን የሚባሉት ጥብብት መጥበቢት ብልህ ነፍስ ያላቸው፤ የእግዚአብሔርንና የሰይጣንን ለይተው ለእግዚአብሔር ሆነው የሚኖሩ ናቸው። ፍጹም ምልዓተ ኃጢአትንና ከጦር ይልቅ የሚወጉ የኃጢአት እሾሀቸውን የነቀሉ ናቸው ጠቢባን። ✞ ጠቢባንስ እግዚአብሔርን ያለጥርጥር በሙሉ ልብ የሚያምኑት፤ አምነውም እንደ ፈቃዱ የተከተሉት፤ በክንፈ ጸጋ ተመስጠው ከልብ በሚወጣ ውዳሴ ከእርሱ ጋር ተዋሕደው የሚኖሩ ናቸው። የነፍሳቸውን ረብሕ ጥቅም አውቀው ዕለት ዕለት ያንን የሚለማመዱ በእውነት ጠቢባን እነዚህ ናቸው። ✞ የጋለ ብረትን ለመቀጥቀጥ የሚነሣ ሰው አስቀድሞ በብረቱ ምን ለመሥራት እንዳሰበ መወሰን አለበት፤ መጥረቢያ፥ ሰይፍ፥ ወይስ ማጭድ? እኛም በምን ዓይነት የሕይወት መስመር ፍሬ ለማፍራት እንዳሰብን አስቀድመን ልቡናችንን ማዘጋጀት አለብን፡፡ ✞ ዘወትር በዐይንህ ፊት ፈሪሃ እግዚአብሔር ይኑር፤ ሕይወትና ሞት የሚሰጠውን አዘክረው፡፡ ዓለምንና በዓለም ያለውን ሁሉ ጥላው፤ ከሥጋ የሚመጣውን ደስታና ሰላም አትሻ፤ ለዚህኛው ኑሮ ሙትና ለእግዚአብሔር ሕያው ሁን፤ ለእግዚአብሔር ቃል የገባኸውን አትርሳ፤ ያም በፍርድ ቀን ካንተ ይፈለግብሃል፡፡ ረኀብን በጸጋ ተቀበለው፤ ተጠማ፥ ተራቆት፥ ንቁና በሐዘን የምትኖር ሁን፡፡ በልቡናህ አልቅስና ጩኽ፤ ለእግዚአብሔር የምትመች መሆን አለመሆንህን ፈትን፤ ሥጋህን ቀጥተህ ነፍስህን ታድናት ዘንድ፡፡ ✞ የቱንም ያህል በመከራ ቢወድቅብህ የቱንም ያህል በአስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ ብታልፍ ይህንን ለጌታዬ ለመድኃኒቴ ለኢየሱስ ክርስቶስ ስል እቀበላለሁ በል። ቀላል ይሆንልሀል። የጌታችን የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ኃይል ነውና። በእርሱ ማእበሉ ፀጥ ይላል ሰይጣንም ይሸሻል። ✞ ለተወሰን ጊዜ ለሀይማኖት መከራከር፤ ጠበቃ መሆን፤ መዋጋት ብሎም መሞት አይከፋም ሁልጊዜ ለሀይማኖት መኖር ግን ከሁሉ የበለጠ መስዋእትና ክብር ያለው ህይወት ነው፡፡ (#ከተለያዩ_ጽሑፎች_የተሰበሰቡ)
Mostrar todo...
🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰
Mostrar todo...
Watch "አገሬ ምን ነካሽ በሂሩት ገ/እየሱስ/Hirut G/Eyesus" on YouTube https://youtu.be/H2WelcLUM_0
Mostrar todo...
አገሬ ምን ነካሽ በሂሩት ገ/እየሱስ/Hirut G/Eyesus

ስለተከታተላችሁን እናመሰግናለን። በዚህ ፕሮግራም ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ ጥንዶች፣ ላጤዎች፣ ጓደኛሞች፣ የቤተሰብ አባላት ወ.ዘ.ተ በሚከተሉት አድራሻዎች ያግኙን። Telegram=

https://t.me/Brhan5

Twitter = d

https://mobile.twitter.com/home

Facebook =

https://www.facebook.com/Ethio-Israel

በአንድ ወቅት አንድህፃን ልጅ ከአዋቂዎች መሀል ተቀምጦ የቤቱ ባለቤት እንግዶቹን ሽርጉድ እያሉ ከሚስቱ ጋር ያስተናግዳሉ መብሉ አልቆ ቆሎ ቀረበና ጨዋታ ያዙ ያንጊዜ የቤቱ ባለቤት ከጫፍ ጀምሮ ቆሎውን እየዞረ ማዘገን ጀመረ ከዛም ህፃኑልጅ ጋርደረሰ አቢዬ ያዝ ቆሎ ቢለው አይ ጋሼ እርሶ ዘግነው ይስጡኝ ይላቸዋል አንገቱን ደፍቶ እጁን በጉልበቱ እያፋተገ አይአቢዬ ብሎእርሱ ዘግኖ ይሰጠውና ቁጭ ይላል ከዛም ሌሎች ልጆች እራሳቸው ሲዘግኑ እርሶ ስጡኝያለው ህፃን ልጅ ትህትናው ገርሟቸው አይ አቢ እያሉ ተጠግተው ቤቢዬ እኔየምልህ ሌሎቹ ልጆች ራሳቸው ሲዘግኑ አንተ ለምን እኔ እንድሰጥህ ፈለግኽ? ሲሉት ★ልጁ፡- አይ ጋሼ የእኔ እጅ ትንሽናት የእርሶግን ትልቅነው ስለዚህ ብዙ አፍሰው እንዲሰጡኝ ነው አላቸው በሹራቡ ያስቀመጠውን ቆሎ እየቆረጠመ::
Mostrar todo...
በአንድ ሀገር የነበረ ንጉስ እንዲ ሆነ እንጀራ ፈላጊ ሰዎች ወደንጉሱ ይሄዱና ንጉስ ሆይ ሺ ዓመት ንገስ በግዛትህ ሁሉ እስከዛሬ ድረስ ታይቶ በማይታወቅ ጥበብ ሀጥያተኛ ሰው ሊመለከተው የማይችለው ልብስ እንስራልህ ይሉታል ይሄ ንጉስም ተገርሞ እናንተ ለመስራት ያብቃችሁ እንጂ ሽልማታችሁን እኔ አዘጋጃለሁ ብሎ ክፍል ተሰቷቸው መስራት ይጀምራሉ ከዛም እስኪ ምንላይ እንደደረሱ እያቸው ተብሎ አንድ አጋፋሪ ይላካል ይሄም አጋፋሪ ይሄድና ቢያይ አንዳች ነገር የለም በባዶ ቦታ እጃቸው እያወናጨፉ የሚሸምኑ ይመስላል እንጂ አንዳች የለም ጠቢባኑም ተነስተው ተመልከት እጀ ጠባቡና ወራጁ አልቋል ትንሽነው የቀረን ይሉታል ያአጋፋሪ መልሶ ሀጥያተኛ ላለመባል ግሩም ነው ንጉስ ይህን ሲያዩ በጣም ደስ ይላቸዋል በርቱ ብሎ ሄደ ለንጉሱም ሄዶ አጋኖ ክቦ ይነግረቸዋል ንጉሱም ሊያየው ይሄዳል ከዛምንጉሱም ሲያይ አንዳች የለም እነዛ ጠቢባን ግን እንደሸማኔ እጃቸው እየተወራጫ አልቋል ንጉስሆይ ተመልከቱት ጥቂት ነው የቀረን እያሉ ሲያሳይዋቸው ከንጉሱ ጋርም አብረዋቸው ያሉት ሀጥያተኛ ላለመባል ግሩም ነው ጥበቡን እዩት ይላል ግማሹ ሌሎች ደም ወራጁን ክሩን ጨርቁን እያሉ አደነቁ ንጉሱም ሀጥያተኛ ንጉስ ላለመባል ምንም በሌለበት አብረው አድንቀው ወጡ የማያልቅ የለም አለቀ ና ሀጥያተኛ የማያየው ልብስ ተሳራ ተብሎ ህዝቡ ተሰበሰበ ንጉሱ ለጠቢባኑ ሽልማታቸውን ሰጥተው ሀጥእ የማያየውን ልብስ ለበስኩ ብለው የተከበሩት ንጉስ እራቁታቸውን ሰረገላቸው ላይ ሆነው ህዝቡን እጅ እየነሱ መሄድ ጀመሩ ዝናቡም ሊመጣ ብሏል ንፋሱም ያንዘፈዝፋቸው ጀመር ህዝቡ ግን ግማሹ ያደንቃል ግማሹም በአፉ እያደነቀ በሆዱ ንጉሱ አበዱ እንዴ ይላል ሀጥያተኛ ላለመባል ታዲያ በዚህ መሀል አንድ ህፃን ኸረ ንጉስ ራቁታቸውን ናቸው እያለ እየተከተለ ይሳቃል ሰዎችም ይሄ በልጅነቱ ሀጥያት የወረሰው ይህን የመሰለ ልብስ ለብሰው ራቁታቸውን ይላል እያለ ክፍክፍ አሉት ግማሹሳቁን መቆጣጠር እያቃተው ከህፃኑ ጋር ይስቃል የዝናቡም ካፊያ ሲጀምር ገላቸውን ነካቸው ልብስ እንዳላረጉ የህፃኑም ንፁህነት ተገለጠላቸው ልብስ አምጡልኝ ከሁላችሁም በላይ ይሄ ልጅነው ንፁህ እውነቱንም የተናገረው አሉ ይባላል ከዛም ሰዎቹ ግማሹ መጀመሪያ የተላከው አጋፋሪ ነው ጥፋተኛአሉ ንጉሱ ናቸው ጥፋተኛ ያሉም አሉ ሁሉንም ያስገረማቸው ንጉሱ እራቁተቸውን ናቸው ብዬ ለህፃኑ የነገርኩት እኔነኝ ያለው ሰውዬ ነበር፡፡ ✍ "እውነት እላችኋለሁ ካልተመለሳችሁ እንደህፃን ካልሆናችሁ መንግስተ ሰማይ ከቶ አትገቡም" ማቴ 18፡3 እውነትን እውነት ሀሰትን ሀሰትበሉ
Mostrar todo...
ሁላችንም ይህንን profile አድርጉት ቦታችንን እናስከብር
Mostrar todo...
አስቸኳይ የሃይማኖት ጥሪ
Mostrar todo...