cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegaciĂłn. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

💡የሂወት ሚስጥሮች💡

🤔 አብዝተህ አቅድ 😷 ጥቂት አዉራ 🔨 ጠንክረህ ስራ ⤵⤵⤵⤵↘↘↘ @Piclose @habetinse1 @hivzz t.me/hivzz

Mostrar mĂĄs
EtiopĂ­a8 856AmĂĄrico8 001La categorĂ­a no estĂĄ especificada
Publicaciones publicitarias
433
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 dĂ­as
-930 dĂ­as

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

🔥🔥እሳትና ውሀ🌊🌊 የታፈነ ውሀ በብረት ድስት ገብቶ በጭቆና ሲኖር ነፃነቱን አጥቶ      ስንት ስቃይ አይቶ       ታጋሽ ሆኖ ሳለ አንድ ጉልበተኛ እሳት የተባለ ብረት ድስቱን ሊያግል እየተቀጣጠለ እራሱን አግዝፎ ድንገት ከተፍ አለ:: : : ቃጠሎ ንዳዱ ውሀው ሲበዛበት የስቃዩ ማብቂያ ጊዜው ሲረዝምበት ትግስቱ ተሟጦ የሚገነፍል ለት         የእሳቱ ግለት      ምን ያክል ቢከፋ የታፈነው ውሀ በምሬት ሲደፋ ሀያሉም ነበልባል አብሮት ነው ሚጠፋ::                     ✍  @hivzz
Mostrar todo...
ለድሀ በእውነት የሚፈርድ (በእውቀቱ ስዩም) አዲስአበባ ውስጥ እንደ ቦሌ መድሀኒያለም እሚገርመኝ  ሰፈር የለም፤ ከመድሀኒያለም ፊትለፊት አስፓልቱን ተሻግሮ ትልልቅ ህንጻዎች ፥ ይበቅላሉ፤ ምርጥ ካፌዎች ሬስቶራንቶችና በርገር ቤቶች  ያብረቀርቃሉ   !  አስፓልቱ ሁሌም በእግረኞች እንደተሞላ ነው፤ ከመድሀኒያለም ጀርባ ደግሞ ሌላ እዩኝ እዩኝ የማይል   አለም አለ፤  በቆርቆሮና በሰማያዊ ሸል የተዋቀሩ የንግድ ቤቶች ተደርድረዋል፤  ባብዛኛው   ምግብ ቤቶች ናቸው፤”  የኛ ሽሮ፥ እድላዊት ምግብ ቤት “ ወዘተ የሚል መጠርያ አላቸው፤ እንደ “ ቃተኛ “ ያሉ የቅንጦት ምግብ ቤቶች ውስጥ የመብላት አቅም የሌላቸው የመንግስት ሰራተኞች እዚህ በተመጣጣኝ ዋጋ ደና ምግብ ይሸምታሉ፤ ለመጨረሻዎቹ  ድሆች”   ርጥብ  “ የተባለ ምግብ ይቀርባል! ርጥብ የቅቅል ድንች ክትፎ ነው፤ በዳጣ ሰላሳ ብር ሲሆን  እንቁላል ሲታከልበት ስድሳ ብር ያስከፍላል፤    ሁሌም ከምግብ ቤቶች ፊትለፊት ሞተርሳይክሎች ተደርድረው ቆመው ይታያሉ፤  እቃ ለማመላለስ ላይ ታች ሲሉ የሚውሉ  ልጆች ባብዛኛው የዚህ ሰፈር ታዳሚ ናቸው:: ቅድም   በዚያ ሳልፍ ቤቶች እየፈረሱ ነው፤ ተወዳዳሪ የሌለው ሀዘን ወረረኝ፤ በቅርቡ እየተደረገ ያለው  የዶዘር ዘመቻ፥ የትምና  መቼም ታይቶ የሚታወቅ አይደለም፤    በአውሮፓ በአሜሪካ በቻይና የዙረት እድል የገጠመን ሰዎች እንደምንመሰክረው ጉሊት አለምአቀፍ ነው፤ በየትኛውም ትልልቅ ከተማ ምግብ ሰርተው መንገድ ላይ የሚሸጡ ሰዎች ይኖራሉ፤ መንግስት መብታቸውን ያከብርላቸዋል፤ “ ሰው በላው ካፒያሊዝም” የሚባለው ስርአት  በሰፈነባቸው ሀገሮች ሳይቀር ድሆች በዚህ መጠን አይገፈተሩም፤  ቤቶች መስጊዶች ያለ ነዋሪው ፈቃድ አይፈርሱም፤ የግድ ሆኖ ሲፈርሱ እንኩዋ ለባለቤቶች ካሳ እና ምትክ ቦታ ይሰጣቸዋል :: አዲስ አበባ እኔ ሳውቃት፥  ትልቁንና ትንሹን አቻችላ የምታሳድር  ሆደ ሰፊ ከተማ  ነበረች፤ አሁን ይሄ እየቀረ ነው!   የተወሰኑ ሰዎች  መሬት ሸጠው ሌክሰስ እንዲነዱ በላባቸው የሚተዳደሩ  አያሌ ድሆች መድረሻ አልባ መሆን አለባቸው? እየተስተዋለ እንጂ ጎበዝ!   በግሌ አቅመቢስ ነኝና ፥ የመዲናይቱ ጌቶች እና እመቤቶች ሰሞኑን  ለሚያደርጉት ነገር በሙሉ ለህሊናቸው አሳልፌ እሰጣቸዋለሁ፤  በዚያ ላይ፥  አማኞች ስለሆኑ የፈጣርያቸውን  ቃል ላስታውሳቸው፥ “ ጻድቅ የድሆችን ፍርድ ይመለከታል! ሀጥእ ግን እውቀትን አያስተውልም! ፌዘኞች ግን ከተማቸውን ያቃጥላሉ! ለድሀ በእውነት የሚፈርድ ንጉስ ፥ዙፋኑ ለዘላለም ይጸናል “ (መጽሀፈ ምሳሌ ምእራፍ 29) @hivzz
Mostrar todo...
#ጦርነትህን_ለራስህ_ተዋጋ ጓደኛህ ትግልህን አይታገልልህም! የምትወደው ሰው ህመምህን በአካል አይወስድልህም! የቅርብ ሰው አንተን ወክሎ አምሽቶ ሲሰራ አያድርም! ስለዚህ እራስህን ተንከባከብ፤ እራስህን ጠብቅ፤ እራስህን አሳድግ። የህይወት ክስተቶችን በእውነቱ ዋጋ ካላቸው በላይ ዋጋ አትስጣቸው። ስትሰብር ካንተ በቀር ማንም አይፈውስህም፤ ስትሸነፍም ከቁርጠኝነትህ በቀር ማንም ድል እንደማይሰጥህ እወቅ። እንደገና ለመቆም እና ለመቀጠል መቻል የራስህ ኃላፊነት ነው። ዋጋህን በሰዎች ዓይን አትፈልግ፤ ዋጋህን ከንቃተ ህሊናህ ፈልግ!! ንቃተ ህሊናህ ሰላም ከሆነ ወደ ላይ ትወጣለህ፤ እራስህን በትክክል ካወቅክ ስለ አንተ የሚነገረው አይጎዳህም። ወዳጄ ጦርነትህን ለራስህ ተዋጋ እሺ! አስቸጋሪ ሁኔታዎችን ለማሸነፍ እና ወደ መሪነት ለመድረስ ደግሞ የማይልስ ሙንሮ #ሁለት መጽሐፍት ይረዱሀል፡፡ #አስቸጋሪ_ሁኔታዎችን_ማሸነፍ እና #የመሪነት_ሳይንስ መጽሐፍት በየመጽሐፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ይገኛሉ።
Mostrar todo...
#10_ችግሮች_ቢከሰቱ_9ኙ_የሚፈቱት_በገንዘብ_ነው ስለገንዘብ የነበረኝንና ያለኝን እይታ፣ ምን ምን ውጤቶች እንደነበሩና እንደነበረኝ ላካፍል። #ገንዘብ ለመገኘቱም ለመታጣቱም ዋናውና ቁልፉ ጉዳይ ያለው አእምሮ ጋር ነው። እንዴት ካላችሁኝ አእምሮ በተወቀረው (ፕሮግራም) በሆነበት ልክ ነው ሰው በገንዘብ የሚደኸይም የሚከብርም። ለምሳሌ "ገንዘብ የኀጢያት ስር ነው" እየተባለ ያደገ ስለገንዘብ ያለው አመለካክት ጥላቻ ነው። እየጠሉት የመቅረብ ሕግ ደግሞ ስኬት ሕግ ላይ አይሠራም፤ የሚስብ ተመሳሳዩን ነውና። በዚሁ አጋጣሚ ራሴን ምሳሌ ባደርግ የበለጠ ግልጽ ይሆናል ብየ አምናለሁ። እኔ የጥላቻ አመለካክት ነበረኝ። የነበረኝም ካለመረዳትና ባልተረዱ ሰባክያን ነበር። ገንዘብ ራሱ በምንም ተአምር ኀጢያት ሊሆን አይችልም። በገንዘብ ኃጢያት የሚሠራ ኊልቆ መሳፍርት የሌለው ሰው ግን አለ። ለጽድቅ አርአያ ከሚሆኑኝ ብነሳ አብርሃም መስቀለኛ መንገድ ላይ ድንኳን ዘርግቶ ሁሉን የሚመግብ እንግዳ ተቀባይ ነበር። ሁሉንም እንግዳ ተቀብሎ የሚመግበው ስላለው ነው። ንጉሥ ሰሎሞን ረሀብ ምን እንደሆነ የማያውቅ ቅንጡ ሐብታም ንጉሥ ነው።ጥበባትን የገለጸለትና ቤተ መቅደሱን ሳይቀር የሠራው በገንዘብ ነው። ንጉሥ ዳዊት በጣም ባለጸጋ ነው። ነገር ግን ኃጢያተኛ ሳይሆን ልበ አምላክ የሚባል ነቢይ ሁኖ ዓለምን ወዴት እንደምትሄድ ቀድሞ ያየና 150 ያህል መዝሙራትን ለአምላኩ ያቀረበ ነው። አሁን ገንዘብን የተጠቀምክበት ዘዴ ነው ገንዘብ ራሱ ኃጢያት? ሌላ የተሳሳቱ ብዙ ብሂሎች አሉ። ድሐም ሐብታምም አንድ እንጀራ በልቶ ነው የሚያድር፣ ሽህ ቢታለብ ያው በገሌ፣ ጎመን በጤና ወዘተ. #እንዲህ አይነት እይታ ውስጥ በነበርኩበት ወቅት በገንዘብ እጦት ተርቤያለሁ፣ ተጠምቻለሁ፣ ታርዠያለሁ። በዚህ ፈጣሪዬን ማማረር ነው ወይስ ኑሮኝ ማመስገን ጽድቅ ሊሆነኝ የሚችል? ኑሮኝ የተራበች ሥጋዬን ብመግብና ባመሰግን ነው። 10 ችግሮች በሕይወታችን ቢከሰቱ 9ኙ የሚፈቱት በገንዘብ ነው። እውነቱ ይህ ሆኖ ሳለ ስለገንዘብ ያለንን እይታ እንድናበላሽ ሁነን ስላደግን የአእምሮ እውቅና እውነቱ ገንዘብ መጥላት እንደሆነ ስለሆነ ይህን ለመስበርና አእምሮን ፕሮግራም ለማድረግ የገንዘብ ሳይኮሎጅ መጽሐፍ ከፍተኛ አስተዋኦ ያደርጋል። #አሁን አንተ ገንዘብን በምን መልኩ ታየዋለህ? ካላችሁኝ ቅዱስ መገልገያ አድርጌ አየዋለሁ። ገንዘብንም በሥራዬ በቀላሉ እንደምፈልገው እያገኘሁት ነው፤ አገኘዋለሁም። ለዚህ መሠረት የሆነኝና ለገንዘብ ያለኝን አመለካክት ያስተካከለልኝ የሕሌና ቀመር ስልጠና ነው፤ ያሰለጠነኝን ከልብ ሳላመሰግን አላልፍም። #ሁሉም ነገር ያለው አእምሮ በተወቀረበት እይታ ልክ ነው። የጥበብ ሁሉ ጥበብ አእምሮን መግራትና ለሕይወት የሚበጁንን መመገብ ነው። እይታ ሲስተካከል በእያንዳንዱ ነገር ላይ ያለን ውጤትም ይስተካከላል።
Mostrar todo...
✔ ህይወትህ ቀላል እንዲሆንልህ አትፀልይ፡፡  ጥንካሬ እንድታገኝ ፀልይ እንጂ፡፡ በአቅም ልትሰራው የምትችለውን ነገር ለማግኘት አትፀልይ፡፡  ልትሰራው ካሰብከው ነገር ጋር የሚመጣጠን ሀይልን እንድታገኝ ፀልይ፡፡ ☞ከዚያ አስደናቂው ነገር 'የሰራህው ስራ' ሳይሆን 'አንተ' ትሆናለህ፡፡
Mostrar todo...
#ይከብደኛል : : እውነት ለመናገር ናፍቀሺኛል ማለት አንቺን ይከብደኛል፤ ልቤ አፍ አውጥቶ ውሸታም የሚለኝ ደርሶም ይመስለኛል። : : ለምን ይመስልሻል ውሸታም እንዳይለኝ፤ ፈራ ተባ ምለው ልቤ እንዳይኮንነኝ? : : ይሄኔ እኮ አንቺ አሉታ አስበሻል፤ ምንም ትዝ ያላልሺኝ እንደዚያ መስሎሻል። : : እውነት እውነት ውዴ... እረስቼሽ ብቻ የመሰለሽ እንደው፤ እንዲያ በማሰብሽ በጣም ነው ምነደው። : : ምክንያቱ ደግሞ... እንኳን ተራርቀን እንኳን ሳንተያይ፤ ቀኑን አብረን ውለን ማታ ስንለያይ፤ አንድ ሁለት እርምጃ እንደመሰንዘሬ፤ ባሳብ እነጉዳለው እያሰላሰልኩኝ ውሎዋችንን ዞሬ። ያላየውሽ ቀንም ያነጫንጨኛል፤ ሰዎች ሰላም ሲሉኝ አሽሙር ይመስለኛል። አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ንፋስ ለምናለው ማደርገው ሲጠፋኝ ልክ አማራጭ ሳጣ፤ የጥሪኝን ዝባድ ሚያስንቅ ጠረንሽን ካለሁበት ድረስ ይዞት እንዲመጣ። : : ይህ እንዳለ ሆኖም ... እውነት ለመናገር ናፍቀሺኛል ማለት አንቺን ይከብደኛል፤ ልቤ አፍ አውጥቶ ውሸታም የሚለኝ ደርሶም ይመስለኛል። : : ለምን ይመስልሻል ውሸታም እንዳይለኝ፤ ፈራ ተባ ምለው ልቤ እንዳይኮንነኝ? : : ይሄኔ እኮ አንቺ አሉታ አስበሻል፤ ምንም ትዝ ያላልሺኝ እንደዚያ መስሎሻል። : : እውነት እውነት ውዴ... እረስቼሽ ብቻ የመሰለሽ እንደው፤ እንዲያ በማሰብሽ በጣም ነው ምነደው። : : ምከንያቱ ደግሞ... ገና ከጅምሩ ስላንቺ ማንነት ውጥኑን ሳሊዘው ምኑንም ሳልቃኘሁ፤ አይተሽ የለም እንዴ ካንጀት ስትስቂ ግራ ጎን አጥንቴን እንዳልኩኝ አገኘሁ። መቼስ ታውቂዋለሽ ለማብሰል ስታገል ወጥን በስልቻ፤ ያለምንም ስስት አንቺ እንደሰጠሺኝ ድስትና ጉልቻ። ይሄም አይጠፋሽም ልክ ዐይንሽን ሳየው የልቤ ትርታ፤ በፊት ከነበረው ፈጥኖ እንደሚመታ። : : እርግጥ ነው ታውቂያለሽ እኔም ብሆን አውቃለው፤ ይህ በንዲ እንዳለ አንቺን ናፍቀሺኛል ማለት እፈራለው። ልቤ አፍ አውጥቶ ውሸታም የሚለኝ ደርሶ ይመስለኛል፤ ናፍቀሺኛል ማለት አንቺን ይከብደኛል። : : ቢልም እውነቱን ነው ... እርግጥም ውሸት ነው ... : : እንደው እንደዘበት ናፍቀሺኛል ፍቅሬ ብሎ ለመናገር አንቺን የከበደኝ፤ ስጋት ያደረብኝ የራሴው ልብ ዞሮ እራሴን መልሶ እንዳያዋርደኝ፤ ለዚህ ነው ንግስቴ ለዚህ ነው እንቁዬ፤ በልቤ ተክዬሽ እንዲያው ስለማድር ከመናፈቅ በላይ ስናፍቅሽ ውዬ።
Mostrar todo...
ዛሬ ከባድ ነው.....ነገ ደግሞ ይበልጥ ይከብዳል....ከነገ ወድያ ግን ያማረ ይሆናል አብዛኛው ሰው ግን ነገ ይሞታል 🗣 Jack ma
Mostrar todo...
ያንተን ህይወት ከሌሎች ጋር አታወዳድር ፀሐይና ጨረቃ በራሳቸው ጊዜ ደምቀውና አምረው እንደሚታዩ አስተውል ሁሉም በጊዜው ውብ ይሆናል እና ደሞ ፈገግታ እንደሚያምርብህ አትርሳ መልካም ቀን
Mostrar todo...
ንጹህ እምባ ሲፈስ ፍርዱን ያላወቁ በምስኪኖች ጩኸት ከሚመጻደቁ ም'ነበር ግብጽ ወርደው ፈርኦንን ባወቁ! ይህ ነው የምባ ፍሬ... ሰማያትን ዘልቆ ከእግዜር ደጃፍ ሲደርስ ዙፋኑ ፊት ሲከስ፣ ፍርድ የሚቀሰቅስ፣ እጣ የሚቀይስ፣ ላልቃሽ ሳቅ አፍልቆ ፣ገዳይ የሚያስለቅስ ማን ያውቃል... ብቻ ጽናት ይስጠን ብቻ ትግስት ይስጠን ያበደረ ሁሉ ብድራት ሊቀበል፣ የስራውን ፍሬ ሲሰፍር እናያለን! እስከዛው... በተስፋ እያነከስን፣ዝም ብለን እናልቅስ ትኳኩስ እምባችን፣ሳይታክተው ይፍሰስ
Mostrar todo...
ዉጤታማ እስክትሆን ፍሬ እስክታፈራ አንተም እንደሚስማር እየመቱህ ስራ 💡#ከሂወት___ሚስጥሮች 💡 @hivzzzz
Mostrar todo...
Elige un Plan Diferente

Tu plan actual sĂłlo permite el anĂĄlisis de 5 canales. Para obtener mĂĄs, elige otro plan.