cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

Habesha news🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹

News and entertainment

Mostrar más
El país no está especificadoEl idioma no está especificadoLa categoría no está especificada
Publicaciones publicitarias
7 657
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
Sin datos30 días

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

ሚኒስትሯ የአፍሪካ ምርጧ የባህልና ቱሪዝም መሪ ተብለው ተሸለሙ፡፡ ባሕር ዳር፡ ኅዳር 23/2013 ዓ.ም (አብመድ) የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትሯ ዶክተር ኂሩት ካሳው የ2019 ምርጧ የአፍሪካ ቱሪዝም መሪ (WOMEN IN AFRICA TOURISM 2019 MOST ENERGETIC AND PASSIONATED AFRICAN TOURISM LEADER AWARD) አሸናፊ ሆነው መመረጣቸውን በጋና የሚገኘው ስትሪት ኦፍ ጎልድ ፋውንዴሽን የተሰኘው ድርጅት አስታውቋል፡፡ ሽልማቱ ከቀናት በኋላ ከአስር ቀን በኋላ ታህሳስ 3 ቀን 2013 ዓ.ም አዲስ አበባ እንደሚደረግ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ከሽልማት ኮሚቴው ያገኘውን መረጃ ጠቅሶ በይፋዊ የማኀበራዊ ትስስር ገጹ አስፍሯል፡፡ ሚኒስትሯ በይፋዊ የፌስቡክ ገጻቸው ሽልማቱን አስመልክቶ ባሰፈሩት መልዕክት "በቱሪዝም፣ በሆቴልና መስተንግዶ በአጠቃላይ በዘርፉ ላይ ለተሰማራችሁ እና ለባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ሰራኞተችና የሥራ ኃላፊዎች በሙሉ እውቅናው የእናንተው ነውና እንኳን ደስ አላችሁ" ብለዋል፡፡ እጅ ለእጅ ተያይዘን ከሰራን ገና ሩቅ እንጓዛለን ነው ያሉት ሚኒስትሯ 👍
Mostrar todo...
ሚኒስትሯ የአፍሪካ ምርጧ የባህልና ቱሪዝም መሪ ተብለው ተሸለሙ፡፡ ባሕር ዳር፡ ኅዳር 23/2013 ዓ.ም (አብመድ) የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትሯ ዶክተር ኂሩት ካሳው የ2019 ምርጧ የአፍሪካ ቱሪዝም መሪ (WOMEN IN AFRICA TOURISM 2019 MOST ENERGETIC AND PASSIONATED AFRICAN TOURISM LEADER AWARD) አሸናፊ ሆነው መመረጣቸውን በጋና የሚገኘው ስትሪት ኦፍ ጎልድ ፋውንዴሽን የተሰኘው ድርጅት አስታውቋል፡፡ ሽልማቱ ከቀናት በኋላ ከአስር ቀን በኋላ ታህሳስ 3 ቀን 2013 ዓ.ም አዲስ አበባ እንደሚደረግ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ከሽልማት ኮሚቴው ያገኘውን መረጃ ጠቅሶ በይፋዊ የማኀበራዊ ትስስር ገጹ አስፍሯል፡፡ ሚኒስትሯ በይፋዊ የፌስቡክ ገጻቸው ሽልማቱን አስመልክቶ ባሰፈሩት መልዕክት "በቱሪዝም፣ በሆቴልና መስተንግዶ በአጠቃላይ በዘርፉ ላይ ለተሰማራችሁ እና ለባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ሰራኞተችና የሥራ ኃላፊዎች በሙሉ እውቅናው የእናንተው ነውና እንኳን ደስ አላችሁ" ብለዋል፡፡ እጅ ለእጅ ተያይዘን ከሰራን ገና ሩቅ እንጓዛለን ነው ያሉት ሚኒስትሯ
Mostrar todo...
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአስር ዓመት ምርጥ የአፍሪካ አየር መንገድ ሽልማትን አሸነፈ አዲስ አበባ፣ ህዳር 22፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአስር ዓመት ውስጥ የአፍርካ ምርጥ አየር መንገድ ሽልማት አሸናፊ መሆኑ ተገለጸ። ለአቪዬሽን ኢንዱስትሪው አስቸጋሪ በሆነው የአፍሪካ ቀጣና እና ፈታኝ በሆነ ወቅት ባስመዘገበው ድንቅ ስኬት መሸለሙም ታውቋል። እንዲሁም የኢትዮጵያ አየር መንገድ እውነተኛው የፓን አፍሪካኒዝም ምሳሌ በመባል አድናቆት ተችሮታል። አየር መንገዱ በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ያስመዘገበው ትርፍም የስኬት… https://www.fanabc.com/የኢትዮጵያ-አየር-መንገድ-የአስር-ዓመት-ም/
Mostrar todo...
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአስር ዓመት ምርጥ የአፍሪካ አየር መንገድ ሽልማትን አሸነፈ - Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አዲስ አበባ፣ ህዳር 22፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአስር ዓመት ውስጥ የአፍርካ ምርጥ አየር መንገድ ሽልማት አሸናፊ መሆኑ ተገለጸ። ለአቪዬሽን ኢንዱስትሪው አስቸጋሪ በሆነው የአፍሪካ ቀጣና እና ፈታኝ በሆነ ወቅት ባስመዘገበው ድንቅ ስኬት መሸለሙም ታውቋል። እንዲሁም የኢትዮጵያ አየር መንገድ እውነተኛው የፓን አፍሪካኒዝም ምሳሌ በመባል አድናቆት ተችሮታል። አየር መንገዱ በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ያስመዘገበው ትርፍም የስኬት መንገዱን […]

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከህዳር 22 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ በአሮጌው የብር ኖት መገበያየት እንደማይቻል ገልጿል፡፡ በባሕር ዳር ከተማ ግብይት እንዴት እየተፈፀመ እንደሚገኝ አብመድ ቅኝት አድርጓል፡፡ ባሕር ዳር፡ ኅዳር 22/2013 ዓ.ም (አብመድ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከህዳር 22 ጀምሮ በነባሩ የብር ኖት መገበያየት እንደማይቻል አስታውቋል፡፡ የብር ኖቶቹ በባንክ ቤት እንዲቀየሩ መመሪያ ቢያስተላልፍም ጥቂት የማይባሉ የህብረተሰብ ክፍሎች እየተገበያዩበት መሆኑን አብመድ ዛሬ በባሕር ዳር ከተማ ገበያ ባደረገው ቅኝት መታዘብ ችሏል። በባሕር ዳር ከተማ አዲሱ የብር ኖት በአብዛኛው በግብይት ላይ እየዋለ ቢገኝም በግብይት ላይ እንዳይውል መከልከል በጀመረበት በዛሬው ዕለት ግን አሮጌው የብር ኖትም ሥራ ላይ እየዋለ ነው፡፡ አቶ ሰርጉ አክሊሉ የሚተዳደሩት በንግድ ሥራ ዘርፍ ነው፡፡ ከዛሬ ጀምሮ ነባሩ የብር ኖት በገበያ ላይ እንደማይውል መረጃ ቢኖራቸውም ደምበኞቻቸውን ላለማስከፋት ብለው ሲቀበሉ መዋላቸውን ተናግረዋል፡፡ የተሰጠው የቀን ገደብ ከመጠናቀቁ በፊት ነባሩን የብር ኖቶች መቀየር ስለሚችሉ ከደንበኞቻቸው እየተቀበሉ መሆኑን ነው አቶ ሰርጉ የተናገሩት፡፡ ደንበኞች በድጋሜ ሲመጡ አዲሱን የብር ኖት ብቻ ይዘው እንዲመጡ እየመከሩ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ ሲገበያዩ ካገኘናቸው ውስጥ ወጣት ትዕግስት አለነ እንደተናገረችው "ከዛሬ ጀምሮ በአሮጌው ብር መገበያየት እንደማይችል መረጃው አለኝ፤ ለዚህም ነው አዲሱን የብር ኖት ለግብይት ይዤ ወደ ገበያ የወጣሁት" ብላለች፡፡ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የባሕር ዳር ተወካይ ጥናትና ምርምር ባለሙያ አቶ አንተነህ ገረመው ኅብረተሰቡ የቀሩት ቀናት ውስን ስለሆኑ ሳይዘናጋ አሮጌውን የብር ኖት ወደ ባንክ በማምራት እንዲለውጥ አሳስበዋል፡፡ አሮጌውን የብር ኖት በአዲሱ የብር ኖት ለመቀየር መንግሥት ሦስት ወራትን የሰጠ መሆኑ ያስታወሱት ተወካዩ ከዛሬ ጀምሮ ኅብረተሰቡ በነባሩ ብር ግብይት መፈጸም ሳይሆን ወደ ባንክ ቤት ሄዶ መቀየር እንደሚገባውም መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
Mostrar todo...
አስተያየት ሀሳብ ጥያቄ ካላችሁ @Daverrr በዚህ ሊንክ ጻፉልኝ
Mostrar todo...
መልካም ቀን ይሁንላችሁ አዳዲስ መረጃዎች ቶሎ እንለቃለን😘😘😘👍👍👍
Mostrar todo...