cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

አሏሁምመሶሊ ዓላሠይድናሙሐመድ

ወዓላ አሊሠይድና ሙሐመድ

Mostrar más
El país no está especificadoEl idioma no está especificadoLa categoría no está especificada
Publicaciones publicitarias
247
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
Sin datos30 días

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

በአላህ እንጠበቅ ========== የአላህ መልክተኛ [ﷺ] ከሰላሳ አራት ፈተናዎች አላህ እንዲጠብቃቸው አዘውትረው ዱዓ ያደርጉ ነበር። እነዚህ "ኢስቲዓዛዎች" በተለያዩ ሐዲሶች የተዘገቡ ናቸው። በእርግጥ ከእነዚህ ብቻ አልነበረም ተወዳጁ [ﷺ] ኢስቲዓዛ ያደርጉ የነበሩት። ሌሎች ፈተናዎችንም ሰዎች ኢስቲዓዛ እንዲያደርጉባቸው አስተምረዋል። ሰላሳ አራቱን ግን ዱዓዎቹን ሐዲሶቹ ላይ በተዘገቡበት በዐረብኛ እና ትርጉማቸውን እንደሚከተለው አቅርቤያለሁ: ‐ : ● اللَّهُمّ إنِّي أعُوذُ بِكَ مِن: ١- العَجْزِ، ٢- والكَسَلِ، ٣- والجُبْنِ، ٤ - والبُخْلِ، ٥ - والهَرَمِ، ٦ - والقَسْوَةِ، ٧- والغَفْلَةِ ٨ - والعَيْلَةِ، ٩ -والذِّلَّةِ، ١٠ - والمَسْكَنَةِ. አላህ ሆይ! ⒈ ከደካማነት፣ ⒉ ከስንፍና፣ ⒊ ከፍትሃት፣ ⒋ ከስስት፣ ⒌ ከእርጅና፣ ⒍ ከጭካኔ፣⒎ ከመዘናጋት፣ ⒏ ቤተሰብን ከሚበትን ድህነት፣ ⒐ ከውርደት፣ ⒑ ከሰው ከሚያስከጅል እጦት ባንተ እጠበቃለሁ። ● وأعُوذُ بِكَ من: ١١ - الفقر ، ١٢- والكُفْرِ،١٣ - والشِّرْك، ١٤ - والفُسُوقِ، ١٥ - والشِّقاقِ، ١٦ - والنِّفاقِ ، ١٧ - والسُّمْعَةِ، ١٨ - والرِّياءِ. አላህ ሆይ! ⒒ ከድህነት፣ ⒓ ከክህደት፣ ⒔ ባንተ ላይ ከማሻረክ፣ ⒕ በአንተ ላይ ከማመፅ፣ ⒖ ከሐቅ መራቅ፣ ⒗ ከንፍቅና፣ ⒘ ከይስሙልኝ ፍላጎት (ሱምዓ)፣ ⒙ ከይይሉኝ አባዜ (ሪያእ) ጠብቀኝ። ● وأعُوذُ بِكَ من: ١٩ - الصمم ، ٢٠ - والبَكَم، ٢١ - والجُنُون، ٢٢ - والجُذامِ، ٢٣ - والبَرَص ، ٢٤ - وَسَيِّىءِ الأَسْقامِ. አላህ ሆይ! ⒚ ከመደንቆር፣ ⒛ ከመታወር፣ 21. ከእብደት፣ 22. ከቁምጥና፣ 23. ከለምጥ፣ 24. ከአስከፊ በሽታዎች በሙሉ ጠብቀኝ። ● وأعوذ بك من: ٢٥ - غلبة الدَين، ٢٦ - وقهر الرجال. አላህ ሆይ! 25. በእዳ ከመረታት፣ 26. በጠላት ከመሸነፍ ባንተ እጠበቃለሁ። ● وأعوذ بك من: ٢٧ - زوال نِعْمَتِك، ٢٨- و تَحوُّلِ عافِيَتِك، ٢٩- وفُجَاءَةِ نِقْمَتِك ، ٣٠- و جَميعِ سَخَطِك. አላህ ሆይ! 27. ፀጋህ እንዳይነሳብኝ፣ 28. ጤናዬ እንዳይወገድ፣ 29. በድንገት የሚመጣ ቅጣትህ እንዳያገኘኝ፣ 30. ከሁሉም ቁጣህ (ቅጣትህ) ባንተ እጠበቃለሁ። ● وأعوذ بك من: ا٣- جَهْدِ الْبَلاَءِ ، ٣٢- وَدَرَكِ الشَّقَاءِ ، ٣٣- وَسُوءِ الْقَضَاءِ ، ٣٤- وَشَمَاتَةِ الأَعْدَاءِ . አላህ ሆይ! 31. መሸከም ከማልችለው ፈተና፣ 32. ለክስረት ከሚያጋልጥ ነገር፣ 33. ከሚያስከፋኝ ውሳኔህ እና 34. ከጠላት ሽሙጥ ባንተ እጠበቃለሁ! : እነዚህን "ኢስቲዓዛዎች" እንጠቀምባቸው። ለሰዎችም እናጋራ! ወቢላሂት‐ተውፊቅ! ኡስታዝ ቶውፊቅ ባህሩ https://telegram.me/wdunebyaselamualeykum
Mostrar todo...
አሏሁምመሶሊ ዓላሠይድናሙሐመድ

ወዓላ አሊሠይድና ሙሐመድ

ገበያ መሐል በንዴት እያጉረመረመ አንድ ሰው ይዟዟራል። ከጉርምርምታው መሀልም የአለማቱን እዝነት ክብራቸውን በማጉደፍ ይሳደብም ነበር። ይህ ስድብ ድንገት ከጆሮው ውል ያለበት አንድ ወጣት ከገበያው መሀል ለግብይት ከተደረደሩ ቢላዎች አንዱን ያነሳና ተሳዳቢውን እስከ ወድያኛው ያስወግደዋል። ቀናት ተቆጠሩ። ገዳይ ፍርድ ቤት ቆመ፣ ችሎቱ በታዳሚዎች ተሞልቷል። ገዳይም የወንጀለኛ መቆምያ ቦታ ላይ እጁን ወደ ኋላ አጣምሮ የሚተላለፍበትን ብያኔ ለማዳመጥ ቁሟል። ዳኛው ከዙፋኑ ተሰይሞ ገዳይን እንዲህ ሲል ጠየቀው፦‹‹ሰውዬውን ለምን ገደልከው?›› ወጣቱ ስሜቱ እንደ አዲስ ተቀሰቀሰ፣ ከቆመበት ሁኖ ሲቃ እየተናነቀው እንዲህ አለ፦‹‹ክቡር ዳኛ! ሰውዬው ረሱልን ዐለይሂ ሶላቱ ወሰላምን ሲሳደብ ሰማሁ፤ እኔ ደግሞ እወዳቸዋለሁ፣ እናፍቃቸዋለሁም...ይህን ስሰማ መቋቋም አቃተኝ። እማደርገው ሁላ ከቁጥጥሬ ውጭ ሆነ ና ገደልኩት›› ዳኛው አውጥቶ፣ አውርዶ እሚያደርገው እሚወስነው ግራ ቢገባው የውሳኔ ትዕዛዙን እንዲህ ሲል ችሎቱ ላይ አስደመጠ፦‹‹ተከሳሽ ለፈፀመው የግድያ ወንጀል ፍርድ ቤቱ የ15 አመት ፅኑ እስራት ወስኖበታል›› ወጣቱ ከችሎት ቆሞ ከእድሜው 15 አመታትን ለረሱል ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም እንደጀባ ሲሰማ ውስጡ በሀሴት ተሞላ። ለረሱሉ 15 አመት ፊዳ ለመሆንም ራሱን አዘጋጀ። ዳኛው ንግግሩን ቀጠለ፦‹‹ፍርድ ቤቱ ከወሰነው ውሳኔ ላይ የቅጣት ማቅለያ ብሎ ግማሹን ያቀለለልህ ሲሆን እኔም የተቀረውን ግማሽ እዚህ በቆምክበት ያህል አካክሼ ቅጣትህን አቅልዬልሓለሁ፤ ፖሊስ እጁን ፍታው ›› ብሎ ከተቀመጠበት የፍርድ ዙፋን ወረዶ ወደ ወጣቱ መጣ። ‹‹ልጄ! ውዳችን ረሱልን የሰደበን ሰው በየትኛው እጅህ ነው የገደልከው›› ብሎ በስስት ጠየቀው። ወጣቱም ቀኝ እጁን በምልክት አሳየው። ‹‹ልጄ እባክህ እጅህን ዘርጋልኝ!›› ሲል በትህትና ጠየቀው። ልጁ እጁን ዘረጋለት፤ በናፍቆት እንባ ያረገዙ የዳኛው አይኖች እንባ እያፈሰሱ የወጣቱን እጅ በስስት ሳመው።በችሎት አዳራሹ ረሱል ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰልም ታወሱ፣ ታዳሚው በሙሉ የናፍቆት ለቅሶውን ያለቅስ ጀመር። መዝገቡ ተዘጋ፣ ችሎቱም ተበተነ። በነጋታው የኩወይት ፍትህ ቢሮ ወደ ሀገሪቱ ፍትህ ሚኒስቴር ይህንን ዳኛ ‹‹የገዳይ እጅ ስሞ በነፃ አሰናብቷል›› ሲል ክስ መሰረተበት። የፍትህ ሚኒስቴሩም አቤቱታውን በአፅንኦት ከተመለከተ በኋላ፦‹‹ይህ ዳኛ በአስቸኳይ የ ነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም ቀብር መገኛ ወደሆነችው መዲና እንዲወሰድ ›› ሲል ትዕዛዝ አስተላለፈ። ወዳጅም ወደ ወዳጁ ሀገር ተሸኘ። ----------------------------- እኚህን ዳኛ ታውቃለህ? ትልቁ አሊም፣ አሳማኝ ከያኒ፣ የባለ ብዙ ድርሰት ባለቤት፣ የብዙ የረሱልን ግጥሞች ደራሲ፣ የተሰዉፍ ነፀብራቅ የሆኑት ዩሱፍ ኢብኑ ኢስማኢል ኢብኑ ዩሱፍ አነብሀኒ ናቸው። 1932 ላይ ነው ያለፉት https://telegram.me/wdunebyaselamualeykum
Mostrar todo...
አሏሁምመሶሊ ዓላሠይድናሙሐመድ

ወዓላ አሊሠይድና ሙሐመድ

#ሰዎች_እንደተረዱህ_ሳይሆን_አንተን_እንደገባህ_ኑር መልካም ብትሆንላቸው መለማመጥ ይመስላቸዋል ኮስተር ካልክ ክፉ ያደርጉሀል ካወራህ ወረኛ ይሉሀል ዝም ካልክም ምክንያት በማድረግ ይርቁሀል። የሰዎችን ተግባር በመከተል ማንነትህን አትጣ እንደራስህ... እንደገባህ ኑር ይበድሉህ መልካም ሁንላቸው፤ ይራቁህ በችግራቸው ከጎናቸው ሁን፤ ይጥሉህ ውደዳቸው ህይወት አድካሚ ናት በተለይ ራስህን ዝቅ አድርገህ ለሰዎች የምታስብ የምትጨነቅ ከሆነ አላማ ቢስ ከንቱ ፍጥረት አድርገው ያስቡሀል፤ግን እንዲ አሰቡ ብለህ ከመልካም ተግባርህ አትዘናጋ መልካም ማሰብ በራሱ ደስ ይላል። አንድ ቀን ሁሉም ሲገባቸው እንደ ሰው ማሰብ ሲጀምሩ ማንነትህን ይረዱሀል። https://telegram.me/wdunebyaselamualeykum
Mostrar todo...
አሏሁምመሶሊ ዓላሠይድናሙሐመድ

ወዓላ አሊሠይድና ሙሐመድ

🍃 #ዛሬ #ከምታይዋቸው #ውድና #ምርጥ #ቴክስት #ነው ➊ ☞ #ነብዩ ሰ·ዐ·ወ አሉ በኔ ላይ በየቀኑ 1000 ሰለዋት የሚያደርግ ሰው በጀነት ሳይበሸር አይሞትም። ➋ ☞ #ነብዩ ሰ·ዐ·ወ አሉ በኔ ላይ በየቀኑ 100 ሰለዋት የሚያደርግ አላህ 100 ሀጃውን ያወጣለታል 70 በጀነት 30 በዱንያ። ➌ ☞#ነብዩ ሰ·ዐ·ወ አሉ ሲነጋ 10 ሲመሽ 10 ሰለዋት ያደረገ የኔን ሸፈኣ የቂያማ ቀን ያገኛል። ➍ ☞#ነብዩ ሰ·ዐ·ወ አሉ በኔ ላይ አንድ ሰለዋትን ያለ አላህ 10 ሰለዋት ይልበተል 10 ሀጥያት ይሰርዝለታል 10 ደረጃ ከፍ ያረገዋል። ➎ ☞ #ነብዩ ሰ·ዐ·ወ አሉ ማንም ሰው ሰላም አይለኝ ም አላህ ሩሄን መልሶልኝ ሰላምታውን ብመልስለት እንጂ። ➏☞#ለኔ የመጀመርያ ሰዎቼ የቂየማ ቀን እነዚያ በኔላይ በብዛት ሰለዋትን ያደረጉብኝ ናቸው። ታድያ ምን እየጠበቅን ነው እኛም ሰለዋት በማብዛት ለረሱት ይሄንን መልእክት ሰደቃ ጃርያ በማሰብ. ብናስተላልፍ የቂያማ ቀን ያላሰብነው ስንት ሀሰናት ይጠብቀናል ። 👏የአጅሩ ተካፋይ እንሁን ለምታውቃቸው ሙስሊሞች ሁሉ ላኩ። በዚህ ቻናል👇 ✔ስለ ወርቃማው ታሪካችን እናወራለን። ✔ዑለሞቻችንን እናወሳለን፤ ✔ጀግኖቻችንን እንዘክራለን፤ ✔ሳይንቲስቶቻችንን እናነሳለን። ለመቀላቀል ይህን ይጫኑ 👇👇👇👇👇👇👇 https://telegram.me/wdunebyaselamualeykum
Mostrar todo...
አሏሁምመሶሊ ዓላሠይድናሙሐመድ

ወዓላ አሊሠይድና ሙሐመድ

🌴በህልማችን ቴምር ማየት? ቴምርን በህልም መስኮት ካየን እንደአፈታቱ አይነት ቢቀያየርም አብዛኛውን ግዜ የመልካም ብሥራት ደውል ሆኖ ይታያል! 🍃ቴምር ገንዘብ እና ሃብትን ይወክላል። •አንድ ሰው በህልሙ ቴምር ሲመገብ ከተመለከተ ሃላል ከስብ እየከሰበ መሆኑን አሊያም ቅዱስ ቁርዐንን ማንበብ እና ከዲነል ኢስላም መጠቀምን ያመላክታል! 🍃የተቀበሩ ቴምሮችን ማለም ቁጠባን ሲያመለክተን አላሚው ቴምሮችን ሲቀብር ካየ ደግሞ ባለህልሙ የየቲሞችን ገንዘብ ለመብላቱ ጥቆማ ይሆናል። 🍃በደረቅ ቦታ ላይ የተቀመጠ ቴምር ቆይታ የሌለውን የሚከስም ሃብት ጠቋሚ ነው። በተመሳሳይ ከደረቀ ግንድ ላይ የሚለቀም ቴምር ከሙናፊቅ ወይም ከመጥፎ ሠው የሚገኝን ጠቃሚ እውቀት ያመለክታል። 🍃በቴምር መሰብሰብያ ወቅትላይ ቴምሮችን ሲያፍስ የተመለከተ ወንድ የተከበረች እና ባለጸጋ ሚስት ሊያገባ እንደሆነ ተበስሯል - እንደሰውዬው ሁናቴዎች ይህ አይነቱ ህልም በበርካታ መልካም ፍቺዎች ሊተረጎም ይችላል። ከፍቺዎቹ መሃከል -ምስጉን ፍሬያማ እውቀትን ማካበት- ይገኝበታል። 🍃የቴምር መሰብሰብያ ወቅት ሳይደርስ ቴምር ሲለቅም የተመለከተ ሠው ወደ ተግባር የማይለውጠውን እውቀት እየሰበሰበ ስለሆነ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶታል - ለፍቶ መና- ይሄኛውም ህልም እንደሰውዬው ሁኔታዎች በተለያዩ መጥፎ ህልሞች ሊፈታ ይችላል። 🍃ቴምርን እየፈለቀቅን ፍሬውን ስናወጣ ከተመለከትን የወንድ ልጅ መወለድ ብሥራት ነው። 🌹አንዲትን የኢማም ኢብን ሲሪን የህልም ፍቺ ገጠመኝ ተጨዋውተን እንለያይማ! ህልሙን ለማስፈታት ወደ ታላቁ ታቢኢይ ኢማም ኢብን ሲሪን የመጣው ግለሰብ ህልሙን እንዲህ ሲል ያረዳቸዋል። •• ኢማም ሆይ እኔ በህልሜ 40 ቴምሮችን አግኝቼ ተመልክቼአለሁ•• ኢማሙ አሰብ አድርገው መልስ ሰጡት ••አንተ ሰው ህልምህ በአሏህ ፍቃድ የ40 ጂራፍ ግርፋቶችን ታመላክታለች •• በሌላኛው ቀን ላይ አንድ ህልም ለማስፈታት ወደርሳቸው የዘለቀ አላሚ ተመሳሳይ ህልም ይነግራቸዋል ••ያ ኢማም በህልሜ ከሱልጣን ደጃፍ ላይ 40 ተምሮችን አግኝቼ ተመልክቼአለሁ•• ኢማም ኢብን ሲሪን ግን ካለፈው የተለየ ፍቺ ነበር የነገሩት •• አንተ ሰው 1000 ዲርሃሞችም በቅርቡ የምታገኝ ይሆናል••። የፍቺዎቹን መለያየት ያጤኑት የኢማሙ ተማሪዎች ግራ በመጋባት ሸይኻቸውን ስለልዩነቱ ሲጠይቋቸው ኢብን ሲሪን እንዲህ ብለው መለሱላቸው። ••የመጀመሪያው ሰውዬ 40 ተምሮችን የተመለከተው ቴምር በማይቀነጠስበት ምድር የደረቀችበት ወቅት ላይ ነው።ይሕኛው አላሚ ደግሞ የዛፎች ሥር በውሃ የሚረጥቡበት የልምላሜ ወቅት ላይ ቴምሮችን ተመለከተ። የአፈታት ስልት እንደ ወቅታዊ ሁኔታዎች እንደሚለያይ እወቁ•• ብዙም ሳይቆይ ሁለቱም ሠዎች ኢማሙ እንዳሏቸው አንደኛው በግርፋት ሌላኛው በሺ ዲርሃም ሽልማት የተባለላቸውን አግኝተዋል። 💡 ይህ የኢማም ሙሀመድ ኢብን ሲሪን የህልም አፈታት ጥበብ ከየት መጣ ? መጻህፍትን አገላብጠው ይሆን? ወይስ ከአስተማሪያቸው ወርሰው? ልብ በሉ ይህ ጥበብ ተሚንኢንዲላህ ነው።አሏህ ፍራሻቸው ላይ በተኙበት የፍቺውን ንጉስ ነቢ ዩሱፍ(አለይሂሰላም) ልኮላቸው ከራሳቸው ከሰይድ ዩሱፍ እጅ ••የምስክር ወረቀት •• እንዳሸለማቸው ኢማሙ የተናገሩበት አጋጣሚ አለ። 😊እናንተስ በህልማችሁ የበላችሁት ነገር የለም? መልካም ህልምዎን ያጋሩን @heyrri #ሼር https://telegram.me/wdunebyaselamualeykum
Mostrar todo...
አሏሁምመሶሊ ዓላሠይድናሙሐመድ

ወዓላ አሊሠይድና ሙሐመድ

#ሚዛን ቴፒ 👉 Isma'el Zemedkun 0936102857 👉Abdullah Kassa 0917345995 🌹 www.mtu.edu.et #ራያ ዩኒቨርሲቲ 👉jemal 0962546301 #ጂንካ ዩኒቨርሲቲ 👉Abdurezak Habib 0978424322 #አክሱም ዩኒቨርሲቲ 👉shikur 0921675678 👉Esa 0922881731 #አዲግራት ዩኒቨርሲቲ 👉0914306610 👉Miftah 0987196477 #አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ 👉muhammed 0945669006 👉elyas 0960749005 #ደምቢደሎ ዩኒቨርሲቲ 👉Ahmed 0923627488 👉Abdusomed 0988022178 #ኦዳቡልቱም ዩኒቨርሲቲ 👉Arefa 0949046747 #ኮተቤ ዩኒቨርሲቲ 👉muhammed 0916254793 #ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ 👉Abdulkerim 0921170033 #አምቦ ዩኒቨርሲቲ 👉muhammed wedaje 0918546305 👉muhammed musa 0935852383 ➡️ ጉዟችሁን ያማረ እና የትምህርት ቆይታችሁ የተሳካ እንዲሆንላችሁ ከፍጡራን ባህሪያት የተጥራራውን አሏህ እንማፀነዋለን።
Mostrar todo...
#ሊላህ_ብለን_ሸር(share) #የአካዳሚክ_እውቀት_ተማሪዎችንም_ከወሀቢያ_እንታደግ! በተለያየ የሀገራችን ጉዳዮች ላይ ሀገራቸውን ወደተሻለ እድገት ለማሻገር የሚማሩ ሙስሊም ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን በትክክለኛው የእስልምና እምነት የታነጹና ለሰውም ለሀገርም የሚጠቅሙ ይሆኑ ዘንድ ሁላችንም ድርሻችንን እንወጣ፡፡ዩኒቨርሲቲይ ላይ ወሀቢያዎች ብዙ አመታትን በጅህልና ዲግሪ እያስመረቁ በመበተናቸው ስንቱ እንደተበጠበጠ ከማናችንም አይደበቅም፡፡ለዚህም በዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ላይ ትኩረትን ማድረግ አለብን፡፡ ወደ የትኛውም ዩኒቨርስቲ አዲስ የምትገቡ ሙስሊም ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን እናንተን ለመቀበል የተዘጋጁ የተቀባይ ስም እና ስልክ አጠናክረን እነሆ እንላችኋለን። ❗️#ማሳሰቢያ❗️ ➖ እኒህ #የረሱል ዐለይሂሶላቱ ወሰላም #የሶሐባዎች፣ #የሰለፎች ፣ #የኸለፎች ፣የአራቱም መዝሀብ፣ #የመሻይኾች-የአንይ-የገትይ-የዳንይ-የቃጥባርይ፣የአብሬትይ-የጀበርትይ-የገለምስይ-የሌሎችንም እምነትን የሚያደምቁ የአሕለሱና ወልጀመዓ ተከታዮች ናቸው። ➖የሴቶች ስም እና ስልክ አላስቀመጥንም በዋና አስተባባሪዎች ወይም በአሚሮች ማግኘት ትችላላችሁ። ➖ለዐቂዳችሁ ትኩረት በመስጠት ለመሻይኾቻችን ጥላቶች እጅ እንዳሰጡ እያልን ለተቀባይ መረጃ ይህንኑ ብቻ ይጠቀሙ። ➖የተቀመጠው ስልክ ካልሰራ በነዚህ #0942428586 #0942426150 #0947109721 ስልኮች ብትደውሉ ፈጣን ትብብር ይደረግላችኋል። #አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 👉Seid sendew 0929458918 👉 Murad 0949997198 👉 suleyman 0925460128 📌ሰኔ 19 ና 20 #ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ዋና አስተባባሪ 👉ሰዒድ ሙሀመድ 0920211206 👉ጀማል ሙሐመድ 0965143040 📌ሰኔ 26 እና 27 #ወልዲያ ዩኒቨርሲቲ 👉ሙሐመድኑር 0901831491 👉kedir 0939447709 📌ሰኔ 29 እና 30 #አስቱ ዩኒቨርሲቲ 👉አሚር 0984052898 👉Ali 0909529255 📌ሰኔ 24 #ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ዋና አስተባባሪ 👉Abdulqadir Hamdihun 0947033585 ♻️Tewodros_campus 👉Esa Ahmed 0927502403 ♻️Maraki_campus 👉Yunus Adem 0909375026 📌ሰኔ 23 ና 24 #ወለጋ ዩኒቨርሲቲ ዋና አስተባባሪ 👉 ሰይድ 098374798 👉ሰይድ በላይ 0947438837 📌ሰኔ 28 ና 29 🌹www.wu.edu.et #እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ 👉ymam 0935884420 📌ሰኔ 28-30 #ዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ 👉 Temkin 0919469572 📌ሰኔ 29 ና 30 #አሶሳ ዩኒቨርሲቲ 👉 Arebu 0928325496 👉khalid 0940414402 📌ሰኔ 26-30 #ወሎ ዩኒቨርሲቲ 👉seid Muhammed(dese) 0927454599 👉Seid mufti (kocha) -0928438737 📌ሰኔ 29 ና 30 #ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ 👉Abdurehman 0953043233 👉muhammed 0917575363 📌ሰኔ 21 ና 22 #ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ 👉Efa 0922660745 👉Sualih 0943396459 📌ሰኔ 28 ና 29 #ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ 👉kasim 0918250409 👉Seid 0962827698 📌ሰኔ 26-30 #AASTU 👉Amir 0923350066 📌ሰኔ 24 ና 25 #ደብረ ብርሀን ዩኒቨርሲቲ 👉Ahmed Seid 0984161563 👉 Hussein 0939575262 📌ሰኔ 25-30 #ጂማ ዩኒቨርሲቲ ዋና አስተባባሪ 👉ዐብደልጀሊል ኢስሐቅ 0936636216 ♻️ Main campus and beco 👉amir Abubeker seid 0943747934 📌ሰኔ 24 እና 25 #ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ 👉ebrahim 0934566720 👉 seid 0919485575 📌ሰኔ 24 ና 25 #ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ 👉ymer 0940932882 🌹www.wku.edu.et 📌ሰኔ 28 ና 29 #አርሲ ዩኒቨርሲቲ 👉Usman 0942426150 👉hassen 0938629943 #መቀሌ ዩኒቨርሲቲ 👉Redwan 0942755330 👉Seid Ahmed 0935577716 📌ሰኔ 21 - 26(ጊዚያዊ) 🌹 www.mu.edu.et #ድሬደዋ ዩኒቨርሲቲ 👉ዋና አሰተባባሪ መእሩፍ 0943501054 👉ማህዲ ፈትሂ 0920465084 📌ሰኔ 27 - 30 #ዲላ ዩኒቨርሲቲ 👉Sadat 0922074363 👉muhammed 0975321388 🌹 www.du.edu.et 📌ሰኔ 22 ና 23 #ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ 👉ዋና አስተባባሪ ♻️Muhammad--0906417217 ♻️edris ---0966131310 ♻️ poly campus Muhammad yusuf( amir-09455559099 ♻️zenzelma Hussein --0917601890 ♻️peda campus muhammed nur 0979695042 ♻️selam campus Nuredin adem 0962742166 ♻️yibab campus muhammed 0925311184 📌ሰኔ 22 እና 23 #ጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ 👉Abdi, 0943755349 👉kedir 0904479606 📌ሰኔ 28 እና 29 #መቱ ዩኒቨርሲቲ 👉suleyman, 0995678277 👉nuruhussein 0953085914 📌ሰኔ 28 እና 29 #ሰመራ ዩኒቨርሲቲ 👉Abdu Ali 0921791890 🌹www.su.edu.et 📌ሰኔ 26 እና 27 #መዳወላቡ ዩኒቨርሲቲ 👉Habtamu hussen 0918902784 📌ሰኔ 28 እስከ 30 #ወራቤ ዩኒቨርሲቲ 👉Remeto 0922772838 📌ሰኔ 28 እና 29 #ኢትዮጵያ ቴክኒካል ዩኒቨርሲቲ 👉Muhammed Adem 0914418440 📌ሰኔ 28 እና 29 #ቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ 👉Awol 0948908528 🌹 www.bhu.edu.et 📌ሰኔ 28 እና 29 #ጂጂጋ ዩኒቨርሲቲ 👉edris 0960884200 🌹 www.jgu.edu.et 📌ሰኔ 28 እስከ 30 #ሀረማያ ዩኒቨርሲቲ 👉Khalid 0927870969 👉Jewuhar Hussein 0925892045 🌹www.hru.edu.et #ደብረማርቆስ ዩኒቨርሲቲ 👉Qasim Ahmed 091825040 👉 Abdulwahid Siraj 0963253396
Mostrar todo...
ያ የጂብሪል ወዳጅ... ክንፈኛው ጂብራኢል ወደ ናፍቆት አዝመራው ፡ ሲያረፍድ ^ምነው በሰላም?^ እያለ የጌትዬውን መክር ሲፈራ ሚያባሽረውን ወደ አጫዋቹ የዐለሙ ራህመት ሲከንፍ ብቅ አለለት። ሐቢቡ በጂብራኢል መድረስ ልሳናቸው ተፈታች... በሷሂቡ ከላም ተደሳ -እናውራ እንጫወት አንተ የኔ አይናማ- ሲለው አህመዱ እንዲህ አሉት <<ያ ጂብሪል ረሃብ ከሙሐመድ እና ከቤተሰቦቹ ጎጆ ዘልቆ አንግቷል....>> የዐኢሸቱ ጓዳ ከማገዶ ተኳርፎ... እናቴ ፋጢማም ተርባለች! ዋ የሀሰነይኖቹ ለቅሶ! ረሱል ተናግረውም ሳይጨርሱ ከወደሰማዪ አስበርጋጊ ጓጓታ ተሰማ። ለጂብራኢሉ ዘወር ብለው << የሰማሁት ምነው ባክህ አንተዬ>> ሲሉት የምድርን ምንጣፍ ረግጦ የማያውቀው የቂያሙን አስበርጋጊ መለከት የሚነፋው ሰይድ ኢስራፊል ከተፍ..<<አንተ የሰማዩ አህመድ የምድሩ ሙሐመድ የከፍተኛው ዐለም ነዋሪያን ለመራብህ ደንግጠዋል ....እኔም በጌታየ ትዕዛዝ 2ምርጫዎችን ይዤልህ መጥቼልሃለው >> የኔ ከንፈር ይድረቅ..የኔው አንጀት ይላወስልህ! ምነው መቀጠሉን በቻልኩ? ከዐለማት ጌታ የተላከ የምርጫ ሃሳብ ተጣለላቸው <<አንተ ዘንፋላዬ ነብይነትህ እንዳለ ሆኖ ቀምጣላ ንጉስ ላድርግህ ? ወይስ ለኔ የተዋደቅህ ባሪያዬ ትሆናለክ?>> ጂብራኢሉ ምርጫውን ሲሰሙ ጎሸም አደረጓቸው <<ባርያነትን ምረጥ የኔ አይናማ>>። ቀድሞውንስ ዱንያን መች ከጅለው? ስማ አንተ የሙስጦፋ ናፍቂ መልሳቸው እንዲህ ያለ ነበር !<<እኔ የጌታዬ ደካማ ባሪያ ነኝ! እኔ የጌታዬ ደካማ ባሪያ ነኝ እኔ የጌታዬ ደካማ ባሪያ ነኝ>> ኢጃባውን የደጋገሙት ኢስራፊል ዳግም በዱንያ ጉዳይ ሹራ ሊቀማመጥ ብቅ እንዳይልባቸው ይመስላል። አንዴም ጠግቦ ያልበላ ሲጨነቅልን ለኛ አዛብ እንዳንወርድ! ሰላም ይድረሶት ሆዴ💚 ሸጋ ጁምዐ https://telegram.me/wdunebyaselamualeykum
Mostrar todo...
አሏሁምመሶሊ ዓላሠይድናሙሐመድ

ወዓላ አሊሠይድና ሙሐመድ

Elige un Plan Diferente

Tu plan actual sólo permite el análisis de 5 canales. Para obtener más, elige otro plan.