cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

my_Love

ተከታታይ ታሪኮች ሙዚቃ ጥቅሶች Cross & comment 👉 @kingLovebot

Mostrar más
El país no está especificadoEl idioma no está especificadoLa categoría no está especificada
Publicaciones publicitarias
683
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
Sin datos30 días

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

ደስተኛ ሰው ነገን ለመኖር ባለው ስሜት በዛሬ ይረካል
Mostrar todo...
ሕይወት የምትጀምረው መቼ ነው? ሁለት ሰዎች በአንድ ጉዳይ ላይ ይከራከሩ ነበር፡፡ አንዱ፣ “ሕይወት የምትጀምረው ልክ አንድ ጽንስ በተጸነሰበት ቅጽፈት ነው” በማለት ያንን እምነቱን በግለት ያስተጋባል፡፡ ሌላኛው ደግሞ፣ “አይደለም! ሕይወት የምትጀምረው የተጸነሰው ልጅ የመጀመሪያውን ትንፋሽ ወደመተንፈስ ደረጃ ሲደርስ ነው” በማለት የተጋጋለ ምላሹን ይናገራል፡፡ ይህንን ሃሳብ ሳይለቁ ለሰዓታት ሲከራከሩ የተመለከተ አንድ ሰው እያዋዛ አንድን ትምህርት ትቶላቸው አለፈ፣ “ሁለታችሁም ተሳስታችኋል፤ ሕይወት የምትጀምረው ሰው የተፈጠረለትን ዓላማውን ሲያውቅና ያንን መከተል ሲጀምር ነው”!!! ዓላማችንን እንወቅ! በግለት እንከታተለው! እንኑረው! @my_Loveu1 @my_Loveu1
Mostrar todo...
እኔ የሁኔታዬ ውጤት አይደለሁም። እኔ የውሳኔዎቼ ውጤት ነኝ።
Mostrar todo...
#ጥላቻ_እና_ፍቅር ከጥላቻሽ ብዛት አቃጥለሽ ብትገዪኝ አርከፍክፈሽ “ቤንዚን” ደስ ይልሽ ነበረ ፤ ኖሮሽ መርዘሽኝ ብትገዪኝ በ"ራይዚን” ደስ ይልሽ ነበረ፤ እሳተ ጐመራ በድንገት ፈንድቶ ወዲያው ቢጠፋልሽ እኔን ብቻ አጥፍቶ ደስ ይልሽ ነበረ፤ ሰማይ ቢያዝንብልሽ ቀላቅሉ በረዶ ጐጆዬ እንዲገለኝ ላዬ ላይ ተንዶ ምኞትሽ ነበረ ደስታሽም ነበረ በ “ነበረ” ቀረ፡፡ ወይ ነዶ!... ወይ ነዶ!... ይኸው እኖራለሁ ወይ ወዶ!... ወይ ወዶ!... ውዴ አፈቅርሻለሁ:: ጥላቻሽን ፋቂው እውነቱን እወቂው፡፡ ከፍቅሬ የተነሳ ይጨንቃል ማሰቡ ኑሮዬን ያላንቺ ከዚህ ዓለም ብጠፋ የኔ ውድ ብትሞቺ ከፍቅሬ የተነሳ አዕምሮዬ አምኖ እንዴት ይቀበላል?!? እንዴት እሆናለሁ?!? ሞትሽ ከፍቶ ያይላል፡፡ ጨርቄን ያስጥለኛል እርቃን ያስቀረኛል የኔ ውድ ብትሞቺ የማብድ ይመስለኛል፡፡ ሞትሽ ይቅርና ካይዬ ሦር ሰሸትርቂ ላንዲት ቅፅበት እንኳን ሐዘኔ ይከፋና በፍጥነት ልቤ ውስጥ ይተከላል ድንኳን ከፍቅሬ የተነሣ ያለአንቺ አልኖርም ሕይወቴ ጣዕም ያጣል ይኼውልሽ እንዲ ነው ፍቅር ከጥላቻ ሺ ጊዜ ይበልጣል። 🔘ፋሲል ተካልኝ🔘 @my_Loveu1 Share
Mostrar todo...
❤️ 5
ሼር
Comment
#15_ምርጥ_አባባሎች! : 1. ዝቅተኛ እውቀት ባለህ ቁጥር የምትተኛው እንቅልፍ ከፍተኛ ይሆናል፡፡ 2. የሰው ልጅ ከደስታው ይልቅ የሀዘኑን ጊዜያት መቁጠር ይወዳል፡፡ 3. በአብዛኛው ጊዜ ሴቶች የፍቅርን ትርጉም የሚጠፋባቸው በውበታቸው ማምለክ ሲጀምሩ ሲሆን ወንዶች ደግሞ በገንዘባቸው ማምለክ ሲጀምሩ ነው፡፡ 4. መጀመሪያ ለራስህ ራስህ መሆን ስትጀምር ለማን ምን መሆን እንዳለብህ ትገነዘባለህ፡፡ 5. የሰው ልጅ የማሰብ ችሎታው ሲጨምር የጓደኞቹን ብዛት ይቀንሳል፡፡ 6. ከሰዎች ጋር ሮጠህ ያልደረስክበት ነገር ካለ ወደ ተነሳህበት ተመልሰህ ከፈጣሪህ ጋር መሮጥ ጀምር፣ ያኔ ካሰብክበት ሳይሆን ካሰበልህ ቦታ ትደርሳለህ፡፡ 7. ጓደኛን አለማመን ከመካድ የከፋ ነው፡፡ 8. የራስህን ትኩስ እንጀራ ለመጋገር ስትል የሌላውን ቂጣ አትርገጥ፡፡ 9. አንዳንድ ሰዎች የሚወድቁት ሌሎችን በሁለት እግሮቻቸው ለመርገጥ ሲጣጣሩ ነው፡፡ 10. ሰው ከጊዜ እና ከማጣት ብዙ ይማራል፡፡ 11. አንዳንዴ ሽንፈትም ከድል የበለጠ ዋጋ አለው/ ከማሸነፍ ይልቅ በመሸነፍ ውስጥ ብዙ እውቀት አለ፡፡ 12. ሠው የበለጠ እያገኘ በሄደ ቁጥር የበለጠ ስግብግብ እየሆነ ይሄዳል፡፡ 13. ሠዎች ትርጉም ያለው ሥራ መስራት ካልቻሉ የመኖር ትርጉምም ይጠፋባቸዋል፡፡ 14. ባንኮች ዝናብ ሳይኖር ዣንጥላ ያበድሩህና መዝነብ ሲጀምር ግን ዣንጥላውን ይነጥቁሃል፡፡ 15. አዋቂ ሆኖ ለመታየት የምናደርገው ጥረትና ከንቱ ድካም አላዋቂ አድርጎ ያስቀረናል፡፡ ከተመቻቹህ like 👍 & ሼር JOIN US ON 👇👇 @my_Loveu1
Mostrar todo...
👍 10
@my_Loveu1 የ80 ዓመቱ አዛውንት 2 ሰአት ላይ ለሕክምና ቀጠሮው ቸኩሏል። በፍጥነት ጨርሶ ሶስት ሰአት ላይ ሌላ ቀጠሮ ላይ መገኘት አለበት። ዶክተሩ "ስለቀጠሮው ማወቅ ይቻላል?" ሲል ጠየቀው። ዘወትር ጠዋት 3 ሰአት ላይ በሆስፒታል ከባለቤቱ ጋር ቁርስ እንደሚበላ በኩራት ተናገረ። ሚስቱ በምን አይነት ሁኔታ ውስጥ አንደምትገኝ ሐኪሙ ጠየቀው። ሰውዬው ባለቤቱ የመርሳት በሽታ እንደያዛት እና ላለፉት 5 ዓመታት ማን እንደሆነ እንደማታስታውሰው መለሰ። ዶክተሩ ተደንቆ እስካላወቀችው ድረስ ለምን በታማኝነቱ ሊቀጥል እንደፈለገ ሲጠይቀው… አዛውንቱ "ምክንያቱም እኔ አሁንም ድረስ እሷ ማን እንደሆነች አውቃታለሁ።" ብሎ መለሰለት። ፍቅር እንደዚህ ነው…❤️❤️❤️ ... JOIN US ON TELEGRAM 👇👇 @my_Loveu1
Mostrar todo...
❤️ 7
.........እንዴትነውነገሩ........ ልቤን ምን ነክቶት ነው ፣ ቀልቤን ወዴት ጥዬ ስምሽን የፃፍኩት ፣ ስሜን ልፃፍ ብዬ😔 ሆ! ምን ነካኝ!!😅🍂 Join & share @my_Loveu1 👍
Mostrar todo...
👍 6
"ለምን አታገባም?"......እውነተኛ ታሪክ! ~~ "ለምን አታገባም?" የእናቴ ጥያቄ ነበር!ሀሙስረፋድ 4:00አከበቢ ከኪቺኑ በር አጠገብ ባላች ትንሽዬ ኩርሲ ላይ ሆኘ እናቴ ምትጋግረውን እንጀራ እየተመለከትኩ በወሬ እያጀብኳት ነበር፤ የምጣዱ ግለት እና የአከምባሎው እንፋሎት መሃል ታፍነው የሚበስለው የእንጀራው ነገር የኔ ኑሮ መስሎ ታየኝ፤ ስጋ እንደ አየ ውሻ አስሬ ምራቄን ስውጥ አየችኝ መሰል ትኩስ እንጀራውን ቅቤ ለቅልቃ በርበሬ ቀብታ ሰጠችኝ ገና አንድ ጉርሻ ከመጠቅለለ ታናሼ መጣና እየበላሁ ያለሁትን ትኩስ እንጅራ እኔ ሶስት ቦታ የሚጎርሰውን በአንዴ ጠቅልሎ ዋጠ፣ ጩጬዋም መጣችና የአቅሟን ቆረሰች እሷ እንኳን በርበሬው ሲለበልባት ውሃ ብላ ሮጠች፤'ሁልችሁም መዘንጋት የለለባችሁ ነገር ቢኖር የቤቱ ታላቅ መሆኔን ነው!'ብዬ ጎርነን ባለ ድምፅ አስገነዘብኩ አንስቶ ቢወረውረኝ ከሰማይ የወረደ እንቁላል የሚያደረገኝን ታናሽ ወንድሜን የጎሪት እየሾፍኩ! "እውነቱን ነው አለች!" እናቴ እኔን በማገዝ እንጀራውን ለማውጣት ሰፌዱን ከስር እየሰደደች "በዚህ እድሜየኮ የልጅ ልጄን የማይበት ጌዜ ነው"አለች ሊጡ ወደ አለበት ባልዲ እጇን እየላከኝ" "አዎ አግባ እንጂ ምን ትጠብቃለህ" ብሎ ሰሃኗ ላይ ወደ ቀረች አንዲት ጉርሻ እንጀራ አይኑን ቀሰረ 'አንተ ምን አለብህ' አልኩት ገና የአንደኛ አመት የዩኒቬርሲቲ ተማሪ መሆኑ ትዝ እያለኝ 'ገና ለገና አምስት አመት በቤተሰብ ድጎማ አኖራለሁ የምትል ተስፈኛ ነህ" እኔኮ ለመመረቅ መቶ ቀናት የቀሩኝ እጩ ስራ አጥ እና ጡረተኛ ነኝ አልኩት የዚህ አመት ተመራቂ ተማሪዎች ስራ አጥነታችን ብቻ ሳይሆን ተስፋ አጥነታችን ጭምር ከፊቴ ድቅን ሲል!! "እሱን አላህ ያውቃል የአሁነን ግን አስብበት"ብላ እንጅራ ልትጨምርልን ስታመጣ እንደ በቃኝ ነገርኳት "እዚሁ ቤት ውስጥ ትኖራላችሁ ሳሎኑን በፈረቃ እንጠቀማለን እንግዳ ሲኖረን ትለቁልናላችሁ እንግዳ ሲኖራችሁ ደግሞ የራሳችሁ ነው"ብላ ያመጣችውን እንጅራ ለወንድሜ ሰሃኑ ላይ አደረጋለት ስትመለስ መብርት ጠፋች "ኢትዮጵያዬ እንጀራ እንኳን ተጋግሮ እስኪያልቅ የመይታገስ የመብራትሽ ሀይልሽ ግሩም ነው!!' ብዬስለ አባይ ግድብ እና ግብፅ ሀሳብ መሰንዘር ፈልጌ ከበላውት ትኩስ እንጀራና ከእናቴ የጋብቻ ሀሳብ ጋር ተዳብሎ ሲወብቀኝ ትቼያቸው ወደ ክፍሌ አመራሁ መብራቱ እስኪመለስ ሽንኩርቷን መላጥ ጀመረች ወደ ክፍሌ ገብቼ ያልተነጠፈ አልጋዬ ላይ ጋደም አልኩና ለጓደኛዬ ልደውልላት ስልኬን ከኪሴ መዘዝኩ፦ ምን ልበላት? እንጋባ እላታለሁ! ከዚያስ? እሺ ትለኛለቻ እምቢ ቤታችሁ አይሆንም ካለችኝስ? እንደዚያማ አትለኝ የኔ ቆንጆ ብትለኝስ ግን? ከራሴ ጋር ግብ ግብ ገጥሜ የክፍሌን ስፋት እና ፅዳት እየቃኘሁ የአልጋዬን ግማሽ አካል የወረረውን የቁስ አይነት መታዘብ ጀመርኩ ኮምፒውተር፣ ቻርጀር፣ የጆሮ ማዳመጫ፣ መነበብ ላይ ያለ መፅሀፍ፣ ወለሉ ላይ አይኔን ሰደድኩ ካልሲ፣የተፋቁ የሞባይል ካርዶች፣ ተፅፎ ያላለቁ ፅሁፍ የያዙ ብጫቂ ወረቀቶች ይኸ ሁሉ ያለው አንዲት ሁለት በሶስት የሆነች ጠባብ ክፍል ውስጥ ነው።ሲበዛ ሰነፍ ነኝ ክፍሌን የሚያፅዱልኝ ታናናሽ ወንድሞቼ ናቸው ያውም ጉቦ ከፍዬ አልያም ሳንቲም ሲፈልጉ ለሽንት ወይም ቲቪ ለማየት ከክፍሌ ስወጣ ተፀድቶ ይጠብቀኛል ያኔ ግን የሚገፈትርላቸው ጨላ ከለለኝ ረፍት ይነሱኛል፣መልሶ ሊያቆሽሹት ሁሉ ይችላሉ!! ለጓደኛዬ የመደወል ሀሳቤን ለነገ አስተላልፌ ስልኬን አስቀመጥኩ፤ የዛሬዋን ምሽት ግን ከሷ ጋር ማሳለፍ ክፍሌ ፈለግኩኝ፤ የዚያን ቀን ምሽት ነሸጠኝ ቢያንስ አልጋዬን ማንጠፍ አለብኝ ብዬ ቆርጬ ተነሳሁ፣ ባለ ትዳር ሊሆንም አይደል ተፍ ተፍ ልበላ FM እየሰማሁ ማንጠፌን ቀጠልኩ ለዘመናት ብቻዬን ስገላበጥበት የከረምኩትን አልጋ ላጋራ፣ አተኛኜን ሳይቀር ላስትካክል ነው ኤታባቱ!!! አልጋዬ ውስጥ ገባሁ ያነጠፍኩት አንሶላ ላይ የምናብ ሸራዬን ደረብኩ በግራ ጎኔ ተኝቼ በቀኜ ልስላት!! ጅስሜን ወደሷ ቀሳስሬ፣ ሀሳቤን ወዲህ ሸብልዬ ጀመርኩ FM ላይ የሰርግ ሙዚቃ እየተደመጠ ነው የፀጋዬ እሼቱ፦ ችቦ አይሞላም ወገቧ2× ምን ቢሆን ነው ቀለቧ.... የሚለው ስንኝ ጆሮዬን ሰንጥቆ ገባ፣ሌላ ነገር ሳያመጣብኝ ጥርቅም አድርጌ ዘግቼ ወደ ስዕሌ ተመለስኩ ሌቱ ተጋምሷል፣ፀጥታ ሰፍኗል፣ክንዴን አንተራስኳት፣የታሰሬ ፀጉሯን ፈትቼ ለቀቅኩት፣ መደባበስ፣ ትንፋሽ ለትንፋሽ መማማግ፣ አብሮ የሚፈልቅ ላቦትን መጋራት፣ከስር ያነጠፍኩት አንሶላ ሲጨማደድ ተላይ የደረብነው ሲገፈፍ ሳልኩት፤ ሌቱ ሊነጋጋ 11:40 ከመስጂዱ ሙዓዝኑ በለጠቀው አዛን ከምናብ አለሜ ባነንኩ።እንዲሁ ስኳትን የሱብህ ሰላት ደረሰ በምናብ ተጀምሮ በምናብ የሚያልቅ የማይዳሰስ ህይወት እስከ መች ይገፋል ብዬ ሌቱን እየረገምኩ ተነሳሁና ተጣጥቤ ሰገድኩ። ተመልሼም ተኛሁ..... ከእንቅልፌ ስነቃ ጠዋቱ 3:46 ይላል የስልክ ሰአቴ ከአልጋዬ ራስጌ በነበረች ትንሽዬ ወንበር ላይ ቁርሴ ተቀምጠዋል ሰሃኑን ከፈትኩት ጨጨብሳ ነበር የምግብ ፈላጎቴ የለም ተውኩት፤እናቴ በሀሳብ መሰባበሬን የተረዳች ይመስላል ከጎኑ አጥሚት ነበር እሱን ግን አልማርኩትም በአንድ ትንፋሽ ጭልጥ አደርኩት ፤ከትንሽ ደቂቃ በኋላ የማታ ሀሳቤ መቋጫ መንገድ ዱዓ/ፀሎት መሆኑ ሲሰማኝ ወደ ጁምዓ ሰላት ለመሄድ መሰናዳት ጀመርኩ፤ሻወር ወሰድኩ ፣ ጀለቢያዬን አጠለኩ፣ ጥምጣሜን ጣል አደረኩ ፣ሽቶዬን ነስነስ አድርጌ መስታወት ፊት ለፊት ተገተርኩ "ከሰማይ የወረደ መላዐክ መስለሃል"አለኝ ያ ታናሽ ወንድሜ ለነቆራውን መልስ ሳልሰጠው አላህን የሚለምናቸው ዝርዝር ጉዳዮቼን በሀሳቤ አመላለስኩ፤ ከግራ ጎኔ ጋር በቀኝ እንድያውለኝ፣ እኔ እና እሷ መሀል ያለውን ግርዶሽ አፍርሶ እንዳያደባልቀን ፀሎቴን ላደርስ ወደ መስጂድ አቀናሁ.....ብዙ ችግሬን ዘክዝኬ ተማፀንኩት አቤት ቻይነቱ የሰው ልጅ ቢሆንኮ ምስጢርህን ከሰማ በኋላ መልሶ በእሱ ያሾፍብሃል........ሰአትደርሶ ተሰገደ ከጁምዓ ሰላት መልስ ከእናቴ ጋር እዚያው መስጂዱ ፊት ለፊት ያለች አንድ ቡቲክ ገባን ለጩጬዋ ልብስ እያማረጠች እኔም ዝም ብዬ ከምወጣ አልኩና አንድ ፓንት እና ካልሲ ወሰድኩ እውነት ለመናገር የታክሲ ጨላ እንኳን ኪሴ አልነበረም ለመውጣት ስንል አይን አይኗን ተመልከትኩ ቦርሳዋን ከፍታ ቢሉን ዘጋችው። ወዲያው ከቅድቤ ስር ላብ ሲፈልቅ፣ በግምባሬ ላይ ያለው ደምስሬ ሲገተር፣ ማታ ሳወጣና ሳወርድ ያደርኩት የጋብቻ ሀሳቤ እንደ ጉም ጠጉሬን ፈንቅሎ ሲትን በቤቱ ግድግዳ ላይ በተንጠለጠለው መስታወት ውስጥ ራሴን ተመልከትኩ፣ አዘንኩ እናቴ ሳታውቅ ሞራሌን ስብርብሩን አወጣችው፣ ተረማመደችብኝ እሷ መች ይኼን አስባ የደግነቷን ፣የእናትነቷን ማደረጓ ነበር። እኔ ግን የውስጥ ልብሴን መቀየርያ ሳንቲም እንኳን በኪሴ ያልያዝኩ ብኩን መሆነ ሲገለጥልኝ ሸክምነቴ ከእሷ ብላይ እኔን ተጫጫነኝ፣ የእሷ ባለ እዳ ብቻ ሳልሆን እስከ አሀኗ ሰአት እኔ ራሴ እዳ እንደሆንኩ ተሰማኝ። ወደ ቤት እየተመለስን በዝምታ ማዕበል ተዋጥኩ፣ የአልፎ ሂያጅን ጫጫታ ስቃኝ ቤት ደረስን።የማግባት ሀሳቤን ላልተወሰኔ ጊዜ አራዘምኩ፤ ያቺ አፍ አውጥታ ብትናገር ብዙ ምስጢር የምፈነዳ ክፍሌ ገብቼ እንዲህም የሚል ፅሁፍ መፅፍ ጀመርኩ "በስርዝ ድልዝ የተሽሞነሞነች ቀፋፊ አለም" ኤጭ! 💓💓 Join&share @my_Loveu1 @my_Loveu1
Mostrar todo...
👍 4
❤ለወዳጅ ለማጋራት
💬አስታየት💬
Join
Black Monday ምናምን የለም ውጣ ስራህን ስራ ገንዘብ ያዝ ዘንጥ ትኩረት ሳብ ተዝናና ልብህን ከክፋት አፅዳ ተካፍለህ ብላ ግዜህን ጉልበትህን ሳያልፍብህ ተጠቀምባቸው !! በተረፈ ማንንም እንዳትሰማ !!😠
Mostrar todo...
እብድ ለሰዉ እንጂ ለራሱ ልክ ነው 😉😉
Mostrar todo...
Elige un Plan Diferente

Tu plan actual sólo permite el análisis de 5 canales. Para obtener más, elige otro plan.