የሳዳት ከማል የድምፅ ፋይል የሚሰራጭበት ቻናል
Ir al canal en Telegram
የሳዳት ከማል የድምፅ ፋይል በቀላሉ ለማግኘት እና የሌሎች ኡስታዞችን ሙሀድራዎች ጭምር ለማግኘት ተስፈንጣሪውን ይጫኑ እንዲሁም #ሼር በማድረግ ለወዳጅ ዘመድወ ያካፍሉ!! Telegram👇 t.me/Sadatcom1 t.me/Menhaj_Salafiya t.me/IbnuMuneworcom t.me/Muhammedsiragecom t.me/SadatKemalAbuMeryem
Mostrar más1 888
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
Sin datos30 días
Archivo de publicaciones
📌 አዲስ ዳዕዋ
❝ ሕይዎትን በሱና መቀየር ❞
በኢብኑ አባስ ኢስላሚክ ሴንተር (ኬሚሴ) የተደረገ የመክፈቻ ዳዕዋ
🎙 በኡስታዝ ሳዳት ከማል «ሐፊዘሁሏህ»
t.me/Sadatcom1
╔╾╾╾╾╾⊰⊱╾╾╾╾╾╗
╽ t.me/AbuOubeida/2536
╽ t.me/AbuOubeida/2536
╘╾╾╾╾╾⊰⊱╾╾╾╾╾╜
Repost from ⚘ሱና የኑሕ መርከብ ናት قناة السنة سفينة نوح
አሕባሾች እና መሰሎቻቸው አላህ ከዐርሽ በላይ ነው የሚለው እምነት በኢብኑ ተይሚያ ዳብሮ በሙሀመድ ብኑ ዐብዲል ወሃብ የተሰራጨ የ ወሃቢያ እምነት አድርገው እንደሚያስቡት ህፃን አዋቂው ዘንድ ይታወቃል።በዚህ ስራዬ ውስጥ ለነዚህ ሀሰተኞች ስበብ ላለመስጠት የሙሀመድ ብኑ ዐብዲል ወሃብን ቀርቶ የኢብኑ ተይሚያ እና የተማሪዎቻቸውን ንግግሮችም አላካተትኩም ።
ከቁርኣን እና ከሐዲስ ባለፈ ቀዳሚ ትኩረቴ ያደረኩት የአሽዐሪያ አንጃ ከመፈጠሩ በፊት ባለፊት እስከ 300 ሂ . ድረስ በነበሩ ዑለማዎች ላይ ነው ።
ከዚህ ዘመን በኋላ በመጡ ስመ ገናና ዑለማዎች ሊሞግቱን ለሚሹ ማርከሻ ይሆን ዘንድ ያክል ብቻ ከ300 ሂ . ጀምሬ እስከ 7ኛው ክ/ዘመን 2ኛ አጋማሽ ድረስ ከለፉ ዑለማዎች እያለፍኩ አጣቅሻለሁ።
"ከዐርሹ በላይ" ከሚለው መፅሀፍ መግቢያ የተወሰደ
https://t.me/fejir_tube
t.me/Menhaj_Salafiya
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
"ከዐርሹ በላይ" መፅሀፍ ገበያ ላይ ወጥቷል። አልሐምዱ ሊላህ ቢኒዕመቲሂ ተቲሙ ሷሊሓት።
መገኛ፦ አተውባ መክተባ (አንዋር መስጂድ አጠገብ)
=
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from كوني زوجة صالحة تقية
السلام عليكم ورحمة الله وبركاته
قناة نصائح وإرشادات للزوجين فتاوى تحتاجها الأسرة درر وفوائد متنوعة بنشر أحاديث الصحيحين وغيرهما
t.me/Kunizewjeten1
Repost from የሙሀመድ ሲራጅ የድምፅ ፋይል የሚሰራጭበት ቻናል
ክፍል 1____5
( كتاب الصيام" ኪታቡ ሲያም )
عمدة الأحكام ዑምደቱል አህካም
t.me/Muhammedsiragecom
Repost from MuhammedSirage M.Noor
ኢስቲዋእ እና ዑሉውን በተመለከተ በማስረጃዎች የተሞላ ምርጥ መፅሀፍ ።
የተፃራሪዎች ማደናገሪያ እየተጠቀሰ ድባቅ የተመታበት ውብ ስራ ።
የሱና ሰዎች የሚደሱትበት አስደናቂ ፅሁፍ ! !
አላህ ስራህን ይቀበልህ !!!
https://t.me/Muhammedsirage
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
የመጨረሻ የውይይት ጥሪ
~ ~~~~
بسم الله الرحمن الرحيم
ከሆነ ጊዜ ወዲህ ያለው ንትርክ ውል ለማስያዝ ብለን የውይይት ጥሪ ያደረግንላቸው አካላት እስካሁን ድረስ ሰበብ እየደረደሩ ማሰናከሉን ተያይዘውታል። አሁን ደግሞ "ህዝብ ምን ያውቃልና ነው ዳኛ የሚሆነው?" በማለት ለህዝብ ክፍት መሆኑን እየነቀፉ ነው። በጉዳዩ ላይ ግር ያለው ሁሉ ከአሉባልታ ባለፈ በቀጥታ በመከታተል የጠራ አቋም ይይዝ ዘንድ ለህዝብ ክፍት ይሁን አልን እንጂ ህዝብ ዳኛ ሆኖ ነጥብ ይስጠን አላልንም። በዚያ ላይ ካልተግባባን የደረስንባቸውን ነጥቦች በጋራ ፅፈን በጋራ ለምናምንባቸው ዓሊሞች እናቅርባለን ብለናል። አንድ ጫፍ ላይ ሳንደርስ "ዓሊም እናስመጣለን" ወይም "ወደ ውጭ እንሄዳለን" ማለት መሸሻ ሰበብ እንጂ መፍትሄ መሻት አይደለም። ይህን ያክል ጉዳዩ ለታላላቅ ዓሊሞች እንዲቀርብ ብትፈልጉ ኖሮማ ተብዲዕ ውስጥ ከመዋኘታችሁ በፊት ተረጋግታችሁ ትጠብቁ ነበር።
ደግሞስ ከዚህ በፊት ለተለያዩ ወገኖች በግልፅ የውይይት ጥሪ ስናደርግ እንደነበር ይታወቃል። ለምን ያኔ አትነቅፉም ነበር? ጉዳዩ ወደናንተ ሲመጣ ነው ሰበብ የምትደረድሩት?
ለማንኛውም "ውይይቱ በአካል ቢሆን" ስትሉ ለነበራችሁ አካላት ሁሉ! ይሄው ጥያቄያችሁን በበጎ በማየት አንድ እርምጃ ለመቅረብ ወስነናል። ስለዚህ ሁለት ወይም ሶስት ሆነን ወደ ባህርዳር እንሄዳለን፣ ኢንሻአላህ። ይሁን እንጂ በር ዘግተን ከጥቂት ሰዎች ጋር ብቻ የምናወራበት ሁኔታ አይኖርም። በእንዲህ አይነት አካሄድ በተደጋጋሚ ተነድፈናል። ስለዚህ ባህዳር ውስጥ ካሉ መስጂዶች ውስጥ በአንዱ ይመቻች። የፈለገ ይታደምበት ዘንድ በሩ ክፍት ይሁን። ውይይቱን መቅዳትም፣ ቀጥታ ማስተላለፍም ለፈለገ አካል እንዲሁ ክፍት እንዲሆን እንፈልጋለን። ውይይቱን ለመምራትም የውጭ ሰው እንዲሆን አንጠይቅም። እዚያው ባህርዳር ያሉ መሻይኾች (ሸይኽ ዐብደላህ፣ ሸይኽ አሕመድ፣ ሸይኽ ሙሐመድ አወል፣ ኡስታዝ ዩሱፍን ጨምሮ) ይምሩት።
ለመረጃ ያክል ከውስጣችሁ ከኢኽዋን ጋር በግልፅ ውይይት ያደረገ ሰው አውቃለሁ። ይህንን የማነሳው ጥሪያችንን በሆነ ማመሀኛ እንዳትገፉት ነው።
NB፦
~~
በነገራችን ላይ ሰሞኑን በሕሩ የለቀቀውን ድምፅ አልሰማሁትም። የሰሙ ሰዎች ሲነግሩኝ ግን በዚህ መጠን መድረሱ ገርሞኛል። እንዲህ አይነቱን የዙልም አካሄድ ለህዝብ መበተኑ "ለአኺራዬ ያዋጣኛል" ካለ ምርጫው የራሱ ነው። ለጊዜው ግን ለራሴ እየተከላከልኩ ምላሽ በመስጠት ዋናውን የውይይት አጀንዳ ማደብዘዝ አልፈልግም። እቅጩን ስናገር ከውይይቱ ጥሪ ሰበብ እየደረደሩ የሚሸሹት የያዙት አቋም ሆድ የሚያስነፋ እንዳልሆነ ጠንቅቀው ስለሚያውቁ ነው። ስለዚህ የሚፈልጉት ወይ በተዘጋ ክፍል ውስጥ ወይ ደግሞ ጭፍን ደጋፊ ብቻ ባለበት ቦታ ያለ ጠያቂ፣ ያለ ሞጋች እንደፈለጉ መወንጀል ነው። በዚሁ መልኩ ብቻ ነው የምንቀጥለው ካሉ፣ ለህሊናቸው ካልጎረበጣቸው መንገዱን ጨርቅ ያድርግላቸው። "እናንተ ዘንድ የሌላ እውነት አለን" ካሉ ይሄው ለመታረም ዝግጁ ነን እያልን ነው። እኛ እጅ ለመስጠት ፈቃደኞች ካልሆንም "እውነታቸውን" ገልጠው እንደሚያስቡት በኛ የተሸወዱትን አካላት የሚያተርፉበትን እድል ይጠቀሙበት። የቀደመ አቋሙን የቀየረው ማን እንደሆነ ይለይ። እዚያም እዚህም የምንሰማው የተምይዕ ውንጀላም ተፍረጥርጦ ይውጣ። ይሄ ወደ ሱና በመጣራትና ቢድዐን በመዋጋት ጭንብል የተንሰራፋው ውሸትም ይጋለጥ። ባጭሩ እንገናኝና ወይ አጥፊው ይታረም፤ ወይ ውሸታሙ ይፈር።
~ ሰላም ~
እውቀትን ማሰራጨት‼
ታላቁ ዓሊም ሸኽ ሷሊህ አሊ አሸይኽ እንድህ አሉ;
ታላቁ የአሏህን ጠላቶችና ሸይጧንን የምትዋጋበት/የምትታገልበት እውቀትን ማሰራጨት ነው በየትኛውም ቦታ በምትችለው/ባቅምህ ልክ አሰራጨው(እውቀትን)
አልወሷያ አልጀሊያ (ገፅ 46)
t.me/Menhaj_Salafiya
ወንድሞች እና እህቶች
የሃገራችን የተለያዩ ክፍሎች ላይ የተፈጠረው ነገር እጅጉን ከባድ ነው ። የሞተው ሞቶ የተራበው እየተራበ ከቤት ከንብረቱ የተፈናቀለው ተፈናቅሏል ። ወዳጅ ከወዳጅ ተለያይቷል ።
የአላህን ውሳኔ አለም ቢሰበሰብ ሊቀይረው አይችልምና እሱ የወሰነው ሁሉ እየሆነ ነው ።
ሁሉም በአላህ የተወሰነ መሆኑን በማመን ታላቅ አጅርን ለሚያጎናፅፈው ትእግስት እንዘጋጅ - አላህን ከመለመንና ወደሱም ከመመለስ ጋር
مَا أَصَابَ مِن مُّصِيبَةٍ فِي الْأَرْضِ وَلَا فِي أَنفُسِكُمْ إِلَّا فِي كِتَابٍ مِّن قَبْلِ أَن نَّبْرَأَهَا إِنَّ ذَلِكَ عَلَى اللَّهِ يَسِيرٌ (٢٢) [ሱረቱ አል ሐዲድ: 22]
* በምድርም በነፍሶቻችሁም መከራ (ማንንም) አትነካም ሳንፈጥራት በፊት በመጽሐፍ የተመዘገበች ብትኾን እንጅ፡፡ ይህ በአላህ ላይ ገር ነው፡፡
لِّكَيْلَا تَأْسَوْا عَلَى مَا فَاتَكُمْ وَلَا تَفْرَحُوا بِمَا آتَاكُمْ وَاللَّهُ لَا يُحِبُّ كُلَّ مُخْتَالٍ فَخُورٍ (٢٣) [ሱረቱ አል ሐዲድ: 23]
* (ይህ ማሳወቃችን) ባመለጣችሁ ጸጋ ላይ እንዳታዝኑ አላህም በሰጣችሁ ነገር (በትዕቢት) እንዳትደሰቱ ነው፡፡ አላህም ኩራተኛን ጉረኛን ሁሉ አይወድም፡፡
ትእግስት ማጣትና ተገቢ ያልሆነን ንግግር መናገራችን አንዳች ነገር ሊቀይርም ሆነ የተፈለገውን ሊያስገኝልን አይችልም - በወንጀላችን ላይ ሌላን ወንጀል ይጨምራል እንጂ ።
ወደ አላህ መንገድ እንመለስ በየአቅጣጫው ለሚገኙ ወገኖቻችን ሁሉ ዱዓ እናድርግ ።
የመንደራችን ብጥብጥ ብቻ ሣይሆን የወንድምና የእህት ሁሉ ሁኔታና ሠላም ማጣት ያሣሥበን !
የዱንያው ፈተና እምነታችንን እንዳይሸረሽረውና እንዳያጠፋው ጥንቃቄን እናድርግ !! ጉዳዩ ከባድ ነውና በጉዳዩ ላይ እንዳሻን እየተናገርን የፈትዋ ባለቤቶች ከመሆን እንቆጠብ ።
ሰላም ማጣት የመን ውስጥ አፍጋኒስታን ውስጥ ሌሎች ቦታዎችም ውስጥ አለ የነሱንም ሆነ የኛን ሰላም አላህ ይመልስልን
አገራችንን አላህ ሰላም ያድርግልን
t.me/Muhammedsirage
ምን ይሻላል?
~~~~ ~~
ሰው እንዴት አንድ ጥፋት ባላጠፋበት ሁኔታ ቋንቋው ወይም ዘሩ ስለተለየ ብቻ ይገደላል? ለምንስ ንብረቱ ይዘረፋል ይቃጠላል? እንዲያው ምን አይነት ጊዜ ላይ ደረስን? ስለ አሃዳዊነትና ፌደራሊዝም ሰርክ የምትተነትኑ ፖለቲከኞች ሆይ! የሰው ህይወት የማይገደው፣ ሰው ሰው የማይሸት ፖለቲካችሁን ቀቅላችሁ ብሉት!! ለህዝቡ ከመከራ በቀር ቁምነገር የሌላችሁ እርኩሶች ናችሁ!! እናንተ ናችሁ ስለ ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብት የምትደሰኩሩት? ከየትም ብሄር ሁኑ! የተቀናቃኝ ፖለቲከኞችን ቃላት እየሰነጠቃችሁ እርኩስ ትንታኔ የምትሰጡትን ያክል ምናለ በብሄራችሁ አባላት የሚፈፀሙ አውሬያዊ ተግባራትን በስሱ እንኳ ብትነቅፉ! ይሄ ነው የመማራችሁ ጥግ? ይሄ ነው የንቃታችሁ መጠን? ይሄ ነው ለወገን መቆርቆር? እንቆረቆርለታለን የምትሉትን ትውልድ የእውነት ብታስቡለት ኖሮ ስነ ምግባሩን ለመግራት በሰራችሁ ነበር!! ግማሹ ህይወት እየረገፈ ከትላንት ጋር ተጣብቆ የአፄዎችን ብፁእነት ሊግተን ይውተረተራል። ሌላው ትላንት በአፄዎቹ የደረሰበትን ግፍ ምንም በማያውቁ ምስኪኖች ላይ ያወራርዳል። ሶስተኛው ረድፈኛ አጉል ሚዛናዊ ነኝ ባይ በየለቱ ከሚረግፈው ነፍስ ይልቅ በሚነቅፋቸው አካላት ቃላት ስንጠቃ ላይ የተጠመደ ነው። ሁሉም ነቅቻለሁ ባይ እንቅልፋም! ሁሉም ሚዛናዊ ነኝ ባይ ወልጋዳ! ሁሉም ሰው ነኝ ባይ አውሬ! የወገናችን እጣፈንታ በነዚህ የዝንጀሮ ሸንጎዎች ላይ ወድቆ አበሳው በዛ!! ምንድነው የሚሻለን? ወላሂ ስንት ወገኖች ናቸው በሰላም የሚኖሩበት ብቻ ሳይሆን ሸሽተው ለመውጣት እንኳ መንገድ የተዘጋባቸው!! ምንድነው የሚሻለን?
ወላጆች ሆይ! ያገር ሽማግሌዎች ሆይ! አቅመ ደካማ ምስኪኖችን ዘር እየለዩ፣ ቋንቋ እየመረጡ እያጠቁ ያሉት የናንተው ልጆች እንጂ ከሌላ ፕላኔት የመጡ አይደሉም። ምናለ ልጆቻችሁን ብትቆጣጠሩ? ምናለ “ኧረ አይበጅም! ግፉ ለትውልድ ይተርፋል። መቋጫውስ ምንድነው?” ብላችሁ ብትመካከሩ? እንዴት ባገር በቀየው አስተዋይ ይጠፋል? ምን አይነት የእንጨት ሽበት የበዛበት ዘመን ላይ ደረስን!!
በያቅጣጫው እየደረሰ ያለውን ችግር ሰምታችሁ እንዳልሰማችሁ፣ አይታችሁ እንዳላያችሁ የዝሆን ጆሮ ይስጠን ያላችሁ ዱዓቶች፣ ኡስታዞች፣ መሻይኾች ሆይ! ለመሆኑ ችግሩ ምን ሲደርስ ነው የምትናገሩት? ምንም በማያውቁት ምክንያት በየጥሻው እየታረዱ እየወደቁ ያሉ ደካሞች የናንተ ቤተሰቦች ቢሆኑ እውነት ዝም ትሉ ነበር? እውነት እየጠፋ ያለው የወገናችን ነፍስ ከናንተ የመጅሊስ ሽኩቻ ያነሰ ጉዳይ ነው? እንዴት ባደባባይ ወጥቶ ለሁሉ በሚደርስ መልእክት አላህን ፍሩ የሚል ይጠፋል? ነው ወይስ እየደረሰ ያለው ጉድ አይሰማችሁም አይታያችሁም? ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን!!
በአውሮፓ ኳስ ጧት ማታ የምትነዛነዙ ገልቱዎች፣ በአርቲ ቡርቲ ነጋ ጠባ ጆሯችንን የምታደነቁሩ ኮተታም ሚዲያዎችና ጋዜጠኞች! ምናለ ትውልዱን በመቅረፅ፣ ለችግሩ እልባት በመፈለግ ላይ ብትተጉ! በይሉኝታ ተሸብባችሁ፣ በከርሳችሁ እያሰባችሁ የምታልፉት እያንዳንዱ ግፍ ነገ በራችሁን ማንኳኳቱ አይቀርም።
በመጨረሻም ችግሩን ለመፍታት ወይም ለመቀነስ ከሁሉም የተሻለ ሰበብ እያላችሁ ቆማችሁ የምትመለከቱ አልፎም የምታባብሱ ሹማምንቶች፣ ነፍጥ አንጋቾች፣... ከአኺራ በፊት አላህ ዱንያ ላይ ያዋርዳችሁ! አላህ የጃችሁን ይስጣችሁ! ከቤታችሁ ሃዘን ይግባ! መከራ ይመላለስባችሁ!
أَلَا لَعۡنَةُ ٱللَّهِ عَلَى ٱلظَّٰلِمِينَ
https://t.me/IbnuMunewor
ርሑስ ዒድ ኣል -ኣድሓ ኣል ሙባረክ ይግበረልኩም
እንኳን ለ1442ኛው የኢድ አል አድሀ በዓል በሰላም አደረሰን!
በአሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የደስታ፣ የጤና ይሁንላቹ ሀገራችን ሰላም ያርግልን ! አላህ የናንተንም የኛንም መልካም ስራ ይቀበለን!
t.me/Menhaj_Salafiya
