es
Feedback
TheDeepThingsOfGod

TheDeepThingsOfGod

Ir al canal en Telegram

Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!

Mostrar más
1 810
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
Sin datos30 días
Archivo de publicaciones
Where did God come from? #Best Answer!!! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

አትሳቱ! ዓለም እውነቱን እየነገረቻችሁ አይደለም ለወደፊትም አትነግራችሁም። ከዓለም የሆኑ የኃይማኖት ተቋማት እና የተለያዩ የፍልስፍና ሊቆች እውነቱን አይነግረችሁም። ያላችሁበት ማሕበረሰብ እውነትን አይነግረችሁም፥ የዜና ተቋማት እና ማህበራዊ ድረገጾች እውነቱን አይነግሯችሁም። በዓለም ያሉ ስመ ጥር ሰዎች እውነቱን እየነገሯችሁ አይደለም፥ የትምህርት ተቋማትም ጭምር። በዘመናዊው ዓለም የተጻፉ ከ130 ሚልዮን በላይ መጽሐፍት እውነትን እየነገሯችሁ አይደለም። እውነቱ ምንድነው? አይናችሁን ከፍታችሁ ተመልከቱ፥ እያንዳንዱን ነገር በቅዱሳት መጽሐፍት መነጽር ማየት ጀምሩ፥ ይህ የማይሆን ከሆነ የምትሰሙት ድምጽ መዳረሻችሁን ይወስናል፥ ሞት ወይም ሕይወት መምረጥ የእናንተ ነዉ ምንም ከሚመስሉ ከሰዎች ንግግር ጀምሮ በዛሬው ዓለም በስርዓት(systematically) ተደራጅተው በተለያየ መልኩ እስከሚሰበኩ ትምህርቶች፥ ከአስተሳሰቦች እስከ ድርጊቶች እያንዳንዱ ነገር በቅዱሳት መጽሐፍት ብርሃን ሰይቃኝ እና በቃሉ እሳት ሰይፈተን ወደልባችሁ አታስገቡት፥ መልሳችሁም አታድርጉት። የአሁኑ ትውልድ የበላይ ስልጣናትን እና ሃይላትን የማያከብር ብቻ ሰይሆን የሚክድም ነዉ፥ ይህም ቅዱሳት መጽሐፍትን ጨምሮ ነዉ። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

Shocking! "He is coming"/3×/ "He is coming on the way" "The King" የሁለት አመት ህጻን ከእንቅልፏ እንደነቃች የጌታን ተመልሶ መምጣት እና የቤተክርስቲያንን ንጥቀት ስትናገር። ትልልቆቹ ስለታወሩ ልዑል እግዚአብሔር ለሕጻናት የአባቶችን ልብ አድርጎ ትልቅ ራዕይ እያመለከታቸው ነዉ። @TheDeepThingsOfTheSpirit

እጅግ የከበረውን የጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን ተመልሶ መምጣት ስትጠባበቁ በነገር ሁሉ እግዚአብሔርን ማወቅ፥ መበርታት እና በሃይል መስራት ማድረግ እንዲሆንላችሁ እጸልያለሁ። As you wait the Glorious coming of the Lord Jesus Christ, i pray that you may know God, be strong and do exploits in everything. “So that you come behind in no gift; waiting for the coming of our Lord Jesus Christ:” — 1 Corinthians 1:7 “ስለዚህ የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን መገለጥ በጒጒት በመጠባበቅ ላይ ሳላችሁ፣ ማንኛውም መንፈሳዊ ስጦታ አይጐድልባችሁም።” — 1ኛ ቆሮንቶስ 1:7 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

#መንፈሱና_ቃሉ! ሩቅ የሚሄድ ትውልድ መንፈስን ብቻ የያዘ ወይም ቃሉን ብቻ የያዘ አይደለም። ሁለቱን ነጣጥሎ የሚይዝ ሳይሆን መንፈሱን እና ቃሉን አንድ ላይ አጣምሮ የያዘ ትውልድ ሩቅ ይሄዳል። ንስር በአንድ ክንፍ መብረር እንደማይችል ሁሉ መንፈሱና ቃሉ የአንድ ሩቅ ተጓዥ ክርስትያን ሁለቱ ክንፎች ናቸው። መጽሐፍ ቅዱስ — ኤፌሶን 5፥18 ላይ “መንፈስ ይሙላባችሁ...” ይለናል: — ቆላስይስ 3፥16 ላይ ደግሞ “የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ፤...” ይለናል! ሃሌሉያ! መንፈሱና ቃሉ በሙላት ያሉበት ሰው ምንም ሊያስቆመው አይችልም: ሁለት ጤነኛ ክንፎች እንዳሉት ንስር ነዉ። ሩቅ አለመሄድ አይችልም፥ እስከ ክርስቶስ ቀን ድርስ ይበራል! ስለዚህ ሁለቱንም አጥብቃችሁ እንድትፈልጉ እና እንድትይዙ በፍቅር የሆነ ምክሬ ነዉ። ክብር መንፈሱን እና ቃሉን ለሰጠን ለእግዚአብሔር ይሁን!

ሮሜ 13 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹¹ ከእንቅልፍ የምትነሡበት ሰዓት አሁን እንደ ደረሰ ዘመኑን እወቁ፤ ካመንንበት ጊዜ ይልቅ መዳናችን ዛሬ ወደ እኛ ቀርቦአልና። ¹² ሌሊቱ አልፎአል፥ ቀኑም ቀርቦአል። እንግዲህ የጨለማውን ሥራ አውጥተን የብርሃንን ጋሻ ጦር እንልበስ። ¹³ በቀን እንደምንሆን በአገባብ እንመላለስ፤ በዘፈንና በስካር አይሁን፥ በዝሙትና በመዳራት አይሁን፥ በክርክርና በቅናት አይሁን፤ ¹⁴ ነገር ግን ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን ልበሱት፤ ምኞቱንም እንዲፈጽም ለሥጋ አታስቡ።

የአንድ አለም ስርዓት (ONE WORLD ORDER) በፈረንጆቹ የዘመን አቆጣጠር በሚቀጥለው ዓመት የሚከፈተው የአንድ ዓለም ኃይማኖት መቀመጫ በ UAE አቡዳቢ፥ በምስሉ እንደምታዩት ሦስት ህንጻዎች አሉ
የአንድ አለም ስርዓት (ONE WORLD ORDER) በፈረንጆቹ የዘመን አቆጣጠር በሚቀጥለው ዓመት የሚከፈተው የአንድ ዓለም ኃይማኖት መቀመጫ በ UAE አቡዳቢ፥ በምስሉ እንደምታዩት ሦስት ህንጻዎች አሉት። አንዱ ሕንጻ የእስልምናን መስኪድ፥ ሁለተኛው የአይሁድን ሙኩራብ እና ሦስተኛው ሕንጻ ቤተክርስቲያንን የሚወክል ይሆናል፥ ነገር ግን በቤተክርስቲያኑ ሕንጻ ላይ የመስቀል ምልክት መጠቀም የማይቻል እንደሆነ እና የትኛውንም እስላም በፍጹም ወደ ክርስትና ለመመለስ ምንም አይነት ስራ የማይሰራ መሁኑን እ.እ.አ በ 2019 የተፈራረሙት Document of Human Fraternity for world peace የሚለው ኪዳን ያሳያል። ንጉሣችን እና አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቶሎ ተመልሶ ይመጣል።

ሰይጣን የአንድ አለም መንግስትን ለመመስረት ዝግጅቱን ሁሉ አጠናቆ ወደስራ በገባበት በዚህ ወቅት እግዚአብሔርን የሚፈራ፥ ቅዱሳት መጽሐፍትን የሚያነብ እና ሁሉን የሚችል አምላክ እስትንፋስ ማስተዋልን የሚሰጠው አገልጋይ መሪ ለኢትዮጵያ ከእግዚአብሔር መሰጠቱ እግዚአብሔር በዘመን መጨረሻ በኢትዮጵያ ለመስራት የወደደው የከበረ ነገር እንዳለ የሚያሳይ ነዉ፥ ስለዚህ እንደ ቤተክርስቲያን እንንቃ አጥብቀን እንጸልይ እግዚአብሔርን እንወቅ እንበርታ፥ ለመንግስቱም ትልልቅ ስራዎች እናድርግ። ንጉሣችን እና አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቶሎ ተመልሶ ይመጣል።

ዛሬ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው የተሾሙት ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ቃለመሃላ ፈፅመዋል። የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች ጠቅላይ ሚንስትሩ በተሾመበት በዛሬው ቀን፥ እግዚአብሔር ጥበብና ማስተዋል፥ በባህር ዳር
ዛሬ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው የተሾሙት ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ቃለመሃላ ፈፅመዋል። የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች ጠቅላይ ሚንስትሩ በተሾመበት በዛሬው ቀን፥ እግዚአብሔር ጥበብና ማስተዋል፥ በባህር ዳር እንዳለም አሸዋ የልብ ስፋት እንዲሰጠው ጸልዩለት መልካም ቃል ተናገሩበት፥ አብረውት ለሚሰሩ ሹሞችም ጭምር። “እንግዲህ እግዚአብሔርን በመምሰልና በጭምትነት ሁሉ ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር፥ ልመናና ጸሎት ምልጃም ምስጋናም ስለ ሰዎች ሁሉ ስለ ነገሥታትና ስለ መኳንንትም ሁሉ እንዲደረጉ ከሁሉ በፊት እመክራለሁ።” — 1ኛ ጢሞቴዎስ 2፥1-2 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

የፍጥረትን ሩጫ የሚያለመልም ጸሎት-አንድ:-🔥 ቅዱስ አባት ሆይ ፈቃድህ ሁልጊዜ ፍጹም፥ በጎና ልብን ደስ የሚያሰኝ እንደሆነ በቃልህ አውቃለሁ፥ ስለዚህ አባት ሆይ ፈቃድህ በሰማይ እንደሆነች እንዲሁ በምድር ትሁን፥ አባት ሆይ ፈቃድህ በሰማይ እንደሆነች እንዲሁ በእኔ ላይ ትሁን፥ በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አሜን። ከላይ ያለውን ጸሎት በእውነት ከጸለያችሁ አሁን ደግሞ በመንፈስ(በልሳኖች) ያለማቋረጥ በመጸለይ ከመልሳችሁ ጋር ተገናኙ፥ ራሳችሁን እንደ ጸሎታችሁ አንጹ። “እናንተ ግን ወዳጆች ሆይ፤ እጅግ ቅዱስ በሆነው እምነታችሁ ራሳችሁን ለማነጽ ትጉ፤ በመንፈስ ቅዱስም ጸልዩ።” — ይሁዳ 1፥20 አሜን!

🔥የእግዚአብሔር ራዕይ🔥 እኛ ለራሳችን ሕይወት ያለን ራዕይ እጅግ በጣም ትንሽ ነዉ፥ ነገር ግን እግዚአብሔር ለእያንዳንዳችን እጅግ ትልቅ እና ድንቅ ራዕይ አለው። እግዚአብሔር ለኛ ያለው ራዕይ እኛን በራሱ ሕይወት ማኖር፥ በኛ ውስጥ መኖሪያውን አድርጎ በመንፈሱ መኖር፥ በቃሉ ብርሃንና ውሃ እያጠበ እና እየለወጠ የልጁን የክርስቶስን መልክ በእኛ መቅረጽ ነዉ። እግዚአብሔር ለእኛ ያለው ራዕይ የዓለም የሰይጣን እና የኃጢአት ባሪያ ሆነን በፍርሃት እንድንኖር ሰይሆን የመንግስቱ ሰራተኞች እንድንሆን እና በጽዮን ያለውና ነጻ ለማውጣት እጅግ የበረታው ሰራዊቱ አባላት እንድንሆን ነዉ፥ ይህም የሰይጣንን መንግስት እንድንዋጋ እና እንድናፈርስ የሰማይን መንግስት ደግሞ እንድናሰፋ ነዉ። ይህንንም ጦርነት እንድንዋጋ አብረውን የሚጋደሉ ትክክለኛ ወታደሮች ይሰጠናል፥ ለመንፈሳዊ እድገታችን እና ድላችንም ትክክለኛ በሆነ ቦታ ያኖረናል። ይሄ ሁሉ እንዲሆን ከእኛ የሚጠበቀው ነገር "ፈቃድህ በሰማይ እንደሆነች እንዲሁም በምድር ትሁን" ማለት ነዉ። እናም ጽዋውን ለመጠጣትና በጥምቀቱም ለመጠመቅ የግዴታ ፈቃደኞች መሆን ይኖርብናል፥ የራሳችንን ሕልሞች፥ ግቦች፥ መሻቶች እና ራዕዮች መጣል ይጠበቅብናል፥ ይህ ኪሳራ ይመስላል ነገር ግን በምላሹ ክርስቶስንና መንግስቱን ካገኙ ምንም ቢሰጡ ኪሳራ አይደለም። “ደግሞ መንግሥተ ሰማያት በእርሻ ውስጥ የተሰወረውን መዝገብ ትመስላለች፤ ሰውም አግኝቶ ሰወረው፥ ከደስታውም የተነሣ ሄዶ ያለውን ሁሉ ሸጠና ያን እርሻ ገዛ።” — ማቴዎስ 13፥44 〽️ 🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 〽️ @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

የቃሉን ስልጣንና ሃይል በሕይወታችሁ ይገለጥ፥ እግዚአብሔር የቃሉን ደጆች ይክፈትላችሁ፥ በብርሃን ጎርፍ ተጥለቅለቁ በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም፥አሜን።
የቃሉን ስልጣንና ሃይል በሕይወታችሁ ይገለጥ፥ እግዚአብሔር የቃሉን ደጆች ይክፈትላችሁ፥ በብርሃን ጎርፍ ተጥለቅለቁ በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም፥አሜን።

“ዘመኑ ቀርቦአልና የሚያነበው፥ የትንቢቱን ቃል የሚሰሙትና በውስጡ የተጻፈውን የሚጠብቁት ብፁዓን ናቸው።” — ራእይ 1፥3

EndTimeEvents! Mighty EUPHRATES River Drying Up! ትንቢቶች እየተፈጸሙ ነዉ፥ አሁን ይሄንን በምጽፍበት ጊዜ ከታች የምታነቡት ስለ ታላቁ ኤፍራጥስ መድረቅ የተነገረው ራዕይ
EndTimeEvents! Mighty EUPHRATES River Drying Up! ትንቢቶች እየተፈጸሙ ነዉ፥ አሁን ይሄንን በምጽፍበት ጊዜ ከታች የምታነቡት ስለ ታላቁ ኤፍራጥስ መድረቅ የተነገረው ራዕይ ተፈጽሟል። ታላቁ የኤፍራጥስ ውንዝ ለማመን በሚያስቸግር መልኩ ደርቋል፥ ይህም የሆነው በቶሎ ነዉ። YouTube ገብታችሁ መመልከት ትችላላችሁ። “ስድስተኛውም ጽዋውን በታላቁ ወንዝ በኤፍራጥስ ላይ አፈሰሰ፤ ከፀሐይም መውጫ ለሚመጡ ነገሥታት መንገድ እንዲሰናዳላቸው ውኃው ደረቀ።” — ራእይ 16፥12 የተባረከው ንጉሥ ጌታችንና አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቶሎ ይመጣል፥ እንዘጋጅ። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

የእግዚአብሔር ሃይል ኢየሱስ ክርስቶስን ከሙታን ያስነሳ፥ ለሙታን ሕይወትን የሚሰጥ ነዉ።

እንመለስ! Call to return! የእግዚአብሔርን ቃል ያገኙ አባቶች "እርሱ ሊልቅ እኔ ግን ላንስ ይገባል" ብለው በዘመናቸው ሁሉ መከራ የተቀበለውን የሞተውን እና ከሙታን የተነሳውን ኢየሱስ ክርስቶስን አስከብረው ሩጫውን በድል እንዳልፈጸሙ፥ የአሁኑ ትውልድ አገልግሎትን ሲያስብ ኢየሱስን ማክበር ሰይሆን ለራሱ መክበርን መፈለጉን ስመለከት የቱን ያክል ከእግዚአብሔር ቃል እንደራቅን እመለከታለሁ። ወደ እግዚአብሔር ቃል እስካልተመለስን ድረስ እውነተኛ እና ቀጣይ የሆነ የመንፈስ ቅዱስ እንቅስቃሴን መለማመድ አንችልም፥ ምክንያቱም መንፈስ ቅዱስ የእውነት መንፈስ ነዉ ከውሸት ጋር አብሮ አይሰራም። እግዚአብሔር ወደ ቃሉና ወደ መንፈሱ እየጠራን ነዉ፥ ወደቀደመው ፍቅር ተመለሱ እያለን ነዉ፥ የቀና መንፈስና ንጹሕ ልብ ልኖረን ያስፈልጋል። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ቃሉን የማነበው እስከ መች ነው?? .... በቀንም በማታ የማስበው አነባንቤ ብቻ የማላልፈው የእግዚአብሔርን ቃል የማነበው . . . ህይወቴን እስኪቀይረው ነው ገብቶኝ በኑሮዬ እስክኖረው!!! (( 🐛........🦋)) ~Repost@Bety

this is how it ends.... የቤተክርስቲያን ንጥቀት “እንግዲህ ሊመጣ ካለው ከዚህ ሁሉ ለማምለጥ፥ በሰው ልጅም ፊት ለመቆም እንድትችሉ ስትጸልዩ ሁል ጊዜ ትጉ።” — ሉቃስ 21፥36

#BePrepared! #Watch&Pray! The rapture is going to be the greatest sermon! የቤተክርስቲያን ንጥቀት በራሱ ለዓለም ትልቅ ስብከት ይሆናል።

ክርሲቲያን ለማያምኑ ሰዎች ያለውን ፍቅር የሚገልጥበት የመጀመሪያው እና ትልቁ መንገድ ወንጌልን ማጋራት ነዉ። በጌታ ያልሆነ ባልንጀራዬ ከእኔ ወዳጅነት በላይ የኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝነት ያስፈልገዋል፥ የኢየሱስ ሞትና ትንሳኤ እንጂ እኔ የምጋብዘው ማኪያቶ ከኃጢአትና ከዘላለም ሞት አያድነውም። -victor