es
Feedback
TheDeepThingsOfGod

TheDeepThingsOfGod

Ir al canal en Telegram

Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!

Mostrar más
1 810
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
Sin datos30 días
Archivo de publicaciones
ከዚህ ቻናል የተጠቀማችሁ ሁሉ ታዘዙኝ ይሄንን ፖስተር ወደላችሁበት ግሩፕ ሁሉ ሼር አድርጉ!

የሮሜ መጽሐፍ ጥናት በጽሑፍ ወይስ በድምፅ ይቅረብ? በጽሑፍ የምትሉ አንድን በድምፅ የምትሉ ሁለትን ተጫኑ።

የሮሜ መጽሐፍ ጥናት በጽሑፍ ወይስ በድምፅ ይቅረብ? በጽሑፍ የምትሉ አንድ በድምፅ የምትሉ ሁለት ተጫኑ።

የሮሜ መጽሐፍ ጥናት በወንጌል የተገኘውን ድነት እና ጽድቅ በመረዳት በእውነት እውቀት እንዲታነጽ ለምትፈልጉት ሰው ሁሉ አጋሩ። ሰዎች ወደዚህ ጥናት እንድመጡ እና እንዲድኑ ሼር በማድረግ መንገድ ሁኑ፥
የሮሜ መጽሐፍ ጥናት በወንጌል የተገኘውን ድነት እና ጽድቅ በመረዳት በእውነት እውቀት እንዲታነጽ ለምትፈልጉት ሰው ሁሉ አጋሩ። ሰዎች ወደዚህ ጥናት እንድመጡ እና እንዲድኑ ሼር በማድረግ መንገድ ሁኑ፥ ተባርካችኋል! @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

የሮሜ መጽሐፍን ለማስጠናት ዝግጅቴን እየጨረስኩ ነው፥ የሮሜ መልእክት መሰረታዊ የወንጌል እውነት የተተነተነበት ቢሆንም እጅግ የጠለቀ መንፈሳዊ እውነትም ተካቶበታል። በምናጠናበት ጊዜ በመጽሐፉ ውስጥ ያረፉት ዘላለማዊ ቃላት መንፈሳችንን የሚያበሩ እንደሆኑ ሁሉ የማሰብ አቅማችንንም የሚፈትኑ ናቸው፥ ስለዚህ እነዚህን ቅዱስ ቃላት ለእናንተ በፀጋው ለመፍታት ስጀምር እጅግ በደስታ የተሞላው ቢሆንም እርዳታ እንደሚሻ አገልጋይም ነኝ ፥ ስለዚህ የቃሉን ደጆች እንዲከፍትልኝ በጸሎታችሁ እንድትደግፉኝ እጠይቃለሁ፥ የመንፈስ ቅዱስ ሕብረት ከእናንተ ጋር ይሁን። @TheDeepThingsOfGod

የሮሜ መጽሐፍ ጥናት share share share 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit
የሮሜ መጽሐፍ ጥናት share share share 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ቅዱሳት መጽሐፍትን በጥንቃቄ ታሪካዊ አውዳቸውን ጠብቆ ማስተማር፥ መማር እና ማመን ከመንፈስ ቅዱስ እና ከሃይል የሚያርቅ የሚመስላቸው ጴንጤዎች መኖራቸውን ስመለከት እጅግ አዝናለሁ። መንፈስ ቅዱስ እራሱ የእውነት መንፈስ ነዉ፥ የሚንቀሳቀሰው ከእውነት ጋር ነዉ። ፍጹም ወደሆነው ወደ እግዚአብሔር እውነት በንጹሕ ልብ የምንመለስ ከሆነ በቤተክርስቲያን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ የመንፈስ ቅዱስ እንቅስቃሴ እንደምናስተናግድ እርግጠኛ ነኝ። @TheDeepThingsOfGod

ሌሎች መልእክቶችን በማጥናት ወደላይ ማነጽ እንድንችል ከመሰረቱ መጀመር የግድ ስለሆነ የሮሜን መጽሐፍ በጥልቀት በማጥናት ከመረዳት እና ከማድረግ እንጀምራለን፥ እግዚአብሔር እውነቱን ይገልጥልናል።

ሰላም የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች እንዴት ቆያችሁ? እኔ በክርስቶስ ፀጋ ሻሎም ነኝ። እንደ ክርስቶስ ደቀመዝሙር መጽሐፍ ቅዱስን ማጥናት ስላለብን ከአዲስ ኪዳን መልእክቶች የትኛውን መጽሐፍ ለስጠናችሁ? የምናደርገው ሰፊና ጥልቅ ጥናት ነው፥ በዚህ ጥናት ብዙዎቻችሁ እንደምትታነጹ አምናለሁ። የትኛውን መልእክት እናጥና?

“በእውነትህ ቀድሳቸው፤ ቃልህ እውነት ነው።” — ዮሐንስ 17፥17

የአንዳንዱ ሰው አካሄድ...😭 ጸሎት ያለ ንጹሕ ልብ! ጾም ያለ ንጹሕ ልብ! ተከታታይ ትምህርት ያለ ንጹሕ ልብ! ትንቢት ያለ ንጹሕ ልብ! ስብከት ያለ ንጹሕ ልብ... የለ ንጹሕ ልብ ማንም እግዚአብሔርን ማየት አይቻልም። በጾም ጸሎት፥ በስብከት፥ በተከታታይ ትምህርት እና በትንቢት ማየት ያልቻልነውን እግዚአብሔርን በንጹሕ ልብ ማየት እንችላለንና ንጹሕ ልብ ይኑረን፥ የቀና መንፈስ በውስጣችን ይፈጠር፥ የዚያን ጊዜ በመገኘቱ እንኖራለን መንፈሱም በእኛ ይኖራል። @TheDeepThingsGod

ቤተክርስቲያን ውስጥ እና በዓለም ሁሉ እየሆነ ያለውን በማየት የእግዚአብሔር ምክር እና በቅዱሳን ነቢያት የተነገረው ሁሉ እየተፈጸመ መሆኑን መመልከት እንድትችሉ የክብር አባት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ ማስተዋል ይስጣችሁ፥ ምን ማድረግ እንዳለባችሁ እንድታውቁ ደግሞ ጥበብና የመለየት ችሎታ ይስጣችሁ።

የ 12 ኛ ክፍል የማጠቃለያ ፈተና ተፈታኝ የሆናችሁ የእግዚአብሔር ልጆች እግዚአብሔር ማስተዋል እንድትችሉ አእምሮአችሁን ይክፈትላችሁ፥ በድል መጨረስ ይሁንላችሁ!

የክርስቲያን ሕይወት -ሕንጻ መጽሐፍ ቅዱስ የተለያዩ ተምሳሌታዊ የሆኑ መንገዶችን በመጠቀም የክርስቲያን ሕይወት ምን እንደሚመስል ያስተምራል። ለምሳሌ:- መጽሐፍ ቅዱስ የክርስቲያንን ሕይወት ከወታደር ጋር በማነጻጸር የክርስቲያን ሕይወት በመንፈሳዊ ውጊያዎች የተሞላ በመሆኑ አንድ ክርሲቲያን እንደወታደር የራስ ቁር በሆነው በእግዚአብሔር ቃል አስተሳሰቡን መጠበቅ፥ የመንፈስ ሰይፍ በሆነው የእግዚአብሔር ቃል የጠላትን ፍላጻ ማክሸፍ እና ጠላትን ማጥቃት፥ ጋሻ በሆነው እምነት ደግሞ ራሱን እንዲጠብቅ፥ በወንጌል ተጫምቶ እንዲቆም ያስተምራል። ይህ አንዱ ንጽጽራዊ በሆነ መንገድ የቀረበ ምሳሌያዊ ትምህርት ነው። መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ክርስቲያን ሕይወት ለማስተማር ከሌሎች ምሳሌዎች በበለጠ በተደጋጋሚ የተጠቀመው ሕንጻን ነዉ። ሕንፃ በጥቅሉ ሁለት ዋና ዋና ክፍሎች አሉት ፥ የመጀመሪያው መሰረት (foundation) ስሆን ሁለተኛው ደግሞ በመሠረቱ ላይ የሚገነባው ሕንፃ (building) ነዉ። የክርስቲያን ሕይወትም ልክ እንደ ሕንጻ ነው። መሰረት አለው እርሱም ክርስቶስ ነው። በዚህ መሰረት ላይ የሚገነባው ሕንፃ ደግሞ ክርስቲያን ነዉ። ይህንን ከቅዱሳት መጽሐፍት እንመልከት:- “እናንተ ግን፥ ወዳጆች ሆይ፥ ከሁሉ ይልቅ በተቀደሰ ሃይማኖታችሁ ራሳችሁን ለማነጽ እየተጋችሁ በመንፈስ ቅዱስም እየጸለያችሁ፥” — ይሁዳ 1፥20 በዚህ ያንብቡ ክፍል ይሁዳ ክርሲቲያን ራሱን ከሁሉ በላይ ቅዱስ በሆነው ሃይማኖት ላይ ራሱን ማነጽ እንዳለበት ያስተምራል፥ ይህንንም የሚያደርግበት አንዱ መንገድ 'በመንፈስ መጸለይ' እንደሆነ ያስረዳል። አስታውስ/ሽ:- እራሳችንን በመሠረቱ ላይ የማነጽ ኃላፊነት ለእያንዳንዱ ክርስቲያን የተሰጠ ነዉ። ጥያቄ : - እንደ ክርሲቲያን እራስህን/ እራስሽን መሰረቱ ላይ ለማነጽ ምን እያደረክ / እያደረግሽ ነው? @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

መታዘዛችን በተፈጸመ ጊዜ አለመታዘዝን ሁሉ ለመበቀል የበቃን እንሆናለን፥ በሰማይ ላለው አባታችን ያለው መታዘዛችን ፍጹም ስሆን በምድር ላይ ያለውን አለመታዘዝ ሁሉ ለመበቀል የበቃን እንሆናለን።

“መታዘዛችሁም በተፈጸመች ጊዜ አለመታዘዝን ሁሉ ልንበቀል ተዘጋጅተናል።” — 2ኛ ቆሮ 10፥6

ጸሎት ለኢትዮጵያ። የኢትዮጵያ ጠላቶች የኢትዮጵያን መጨረሻ አያዩም ኢትዮጵያ የእነርሱን መጨረሻ ታያለች፥ ኢትዮጵያ አትፈርስም የጦርነትና የረሃብ ምድር አትሆንም ነገር ግን የሪቫይቫልና የተሐድሶ ማእከ
ጸሎት ለኢትዮጵያ። የኢትዮጵያ ጠላቶች የኢትዮጵያን መጨረሻ አያዩም ኢትዮጵያ የእነርሱን መጨረሻ ታያለች፥ ኢትዮጵያ አትፈርስም የጦርነትና የረሃብ ምድር አትሆንም ነገር ግን የሪቫይቫልና የተሐድሶ ማእከል ትሆናለች። ክፉዎች መሳሪያቸው ይክዳቸው፥ ህጻናትንና እናቶችን ለመድፈር ለማዋረድና ለመግደል የሚሄዱበት እግራቸው አይታዘዛቸው የሚቆሙባት ምድር ትዋጣቸው። እግዚአብሔር ይነሳ ጠላቶቹም ይበተኑ፥ እንዳልነበሩ ይሁኑ። “በአንቺ ላይ የተሠራ መሣሪያ ሁሉ አይከናወንም፤ በፍርድም በሚነሣብሽ ምላስ ሁሉ ትፈርጂበታለሽ። የእግዚአብሔር ባሪያዎች ርስት ይህ ነው፥ ጽድቃቸውም ከእኔ ዘንድ ነው፥ ይላል እግዚአብሔር።” — ኢሳይያስ 54፥17 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ትዝታዬ ቃልህ ይሁን -ቤተልሔም😍 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

በዚህ መዝሙር ፀጋ ይብዛላችሁ~ፀሎቴ ጋ። ~ዘማሪት ህሊና ዳዊት @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

....ከሁለተኛው ጽሑፍ የቀጠለ ኢየሱስን ልክ እንደ ሐዋሪያት ማወቅ የምንችልባቸው ሦስት ምክንያቶች:- የመጀመሪያው ኢየሱስን ለሐዋሪያቱ የገለጠው እግዚአብሔር አብ መሆኑ ነው። ጴጥሮስ አይደለም ኢየሱስ ማን ነው የሚለው ጥያቄ መልስ ላይ የደረሰው፥ አብ ገልጦለት ነው፥ መጽሐፍ እግዚአብሔር አብ በጊዜ ያልተገደበ ዘላለማዊ መሆኑን ያስተምራል እርሱ አይለወጥም ትላንት ኢየሱስን ይገልጠው ከነበር ዛሬም ይገልጠዋል፥ እርሱ ራሱ እንደዚህ ብሏልና ““እኔ እግዚአብሔር አልለወጥም፤” — ሚልክያስ 3፥6 ሁለተኛው ምክንያት እግዚአብሔር አብ ኢየሱስን ለሐዋሪያት የገለጠው በመንፈስ ቅዱስ መሆኑ ነው። የጴጥሮስ የማሰብ አቅም አይደለም፥ መንፈሳዊ መገለጥ ነዉ። መጽሐፍ ቅዱስ መንፈስ ቅዱስ ዘላለማዊ መንፈስ እንደሆነ ያስተምራል፤ እንደዚህ ተብሎ ተጽፎልና፥ “ነውር የሌለው ሆኖ በዘላለም መንፈስ ራሱን ለእግዚአብሔር ያቀረበ የክርስቶስ ደም እንዴት ይልቅ ሕያውን እግዚአብሔርን ልታመልኩ ከሞተ ሥራ ሕሊናችሁን ያነጻ ይሆን?” — ዕብራውያን 9፥14 (የዕብራውያን ጻፊ በዚህ ስፍራ ኢየሱስ እንዴት የራሱን ደም ለእግዚአብሔር እንዳቀረበ እያስረዳ መንፈስ ቅዱስን የዘላለም መንፈስ በማለት ይጠራዋል) መንፈስ ቅዱስ ዘላለማዊ መንፈስ ነው፥ በጊዜ የሚታጠር መንፈስ አይደለም። 3-ሦስተኛው እግዚአብሔር አብ በመንፈስ ቅዱስ ለጴጥሮስ የገለጠለት ዘላለማዊውን ኢየሱስን ነዉ። "አንተ ክርስቶስ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ ነህ" እነዚህ ቃላት ሙሉ በሙሉ የኢየሱስን ዘላለማዊ ማንነት የሚገልጹ ናቸው። ስለዚህ ስምዖን ወይም ሐዋሪያቱ በመገለጥ ያወቁት የኢየሱስን ዘላለማዊ ማንነት እንጂ፥ የቆዳ ቀለም፥ የቁመት፥ የክብደት ወይንም የቋንቋ ወይም የአለባበስ ጉዳይ አይደለም፥ ዘላለማዊ ኢየሱስ ነው የተገለጠላቸው። ኢየሱስን የገለጠው ዘላለማዊ እግዚአብሔር አብ የዘላለም መንፈስ በሆነው በመንፈስ ቅዱስ ነው፥ የተገለጠውም ኢየሱስ አይሁዳዊው፥ በእብራይስጥ ቋንቋ የሚናገረው፥ ቀሚስ የሚለብሰው... ወዘተ ኢየሱስ ሰይሆን ዘላለማዊ ኢየሱስ እርሱም "ክርስቶስ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ" ነዉ። የሚገልጠው ዘላለማዊ (እግዚአብሔር አብ) የሚገለጥበት መንገድ ዘላለማዊ (መንፈስ ቅዱስ) የሚገለጠው ዘላለማዊ (ኢየሱስ ክርስቶስ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ) በእነዚህ ሦስት ምክንያቶች ዛሬ እንኳ ኢየሱስን ሐዋሪያት ባወቁት ልክ ማወቅ ይቻላል። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit