es
Feedback
TheDeepThingsOfGod

TheDeepThingsOfGod

Ir al canal en Telegram

Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!

Mostrar más
1 810
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
Sin datos30 días
Archivo de publicaciones
Love unconditionally, then you will live perfectly. -Victor

ይቅርታ ማድረግ ሰው ማህበራዊ ፍጡር ነው ይህ ማለት የሚኖረውም በሕብረት ነው ማለት ነው። ቅዱሳት መጽሐፍት "በተቻለን መጠን በእኛ በኩል ከሰዎች ሁሉ ጋር በሰላም እንድንኖር እና ከፍቅር ውጭ እዳ እንዳይኖርብን" ያስተምሩናል---ሮሜ 12፥18፣ 13፥8--- ነገር ግን የተለያየ ማንነት፣ ፍላጎትና ዓለማ ከላቸው ሰዎች ጋር ስትኖሩ ደግሞ ግጭቶች እና በደሎች እንደሚኖሩ ግልጽ ነው። አንዳንድ ሰዎች ይበድሏችኋል ሌሎች ሰዎች ደግሞ በእናንተ ይበደሉ ይሆናል። ቃሉ እንደሚለው በእኛ በኩል በተቻለን መጠን እጃችንም ልባችንም ንጹሕ እንዲሆን መትጋት አለብን! ሰዎች ሲበድሉን ግን ምን እናድርግ? እኛም መልሰን የሚገባቸውን ዋጋ እንስጣቸው? ወይም በቂም ተሞልተን ይቅር ባለማለት እንኑር? በፍጹም አይሆንም! እኛ የክርስቶስ አእምሮ አለን። የሚበድሉንን ይቅር ማለት የክርስቶስ ባሕርይ ነው። ይቅር ማለት አታቁሙ በቀን ሰባት ጊዜ ሰባ እንኳ እየበደላችሁ ይቅርታ የሚጠይቅን ሰው ይቅር በሉት ይህንን ስታደርጉ ልባችሁን በሰላም ትጠብቃላችሁ፥ በዚህ ይቅር የማለት ሂደት ውስጥ ግን ማድረግ ያለባችሁ ነገር በተደጋጋሚ ለሚበድላችሁ ሰው እድል(opportunity, access) መከልከል ነው። ይቅር በሉ ነገር ግን እድል አትስጡ በዚህ ጥበብ እናንተንም በዳያችሁንም ታድናላችሁ፥ እራሳችሁን ከሃዘን በዳያችሁን ደግሞ ወደፊት ከሚፈጠር ጸጸት፤ ምክንያቱም በፊት ትሰጡት የነበሩ እድሎችን ስትነሱት እናንተን የሚበድልበትን አጋጣሚ እያጠበባችሁ ነው። አስተውሉ:- እድል(opportunity, access) የምትከለክሉት በተደጋጋሚ የሚበድልን ሰው እንጂ በአንድ ጊዜ አይደለም። Forgive but don't give access and opportunity. @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

ከጥንት ዘመን ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ከእግዚአብሔር ጋር አብረው በመስራት የዲያብሎስን ስራ ያፈረሱ፥ ዓለምን ያወኩና ስርዓቶችን የለወጡ ሰዎች ሁሉ የቃሉ እና የጸሎት ሰዎች ናቸው። የማይናወጥ የቃል እና የጸሎት ሕይወት ከሌለን ከእግዚአብሔር ጋር አብሮ ሰራተኛ ለመሆን የሚያበቃ ምንም ነገር የለንም ማለት ነው። “እኛ ግን በጸሎትና በቃሉ አገልግሎት እንተጋለን።””— ሐዋርያት 6፥4 @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

በኢየሱስ ክርስቶስ አምነን የእግዚአብሔር የፀጋ ስጦታ የተቀበልን ሁሉ የጸደቅነው እና ጻድቅ ተብለን የተጠራነው በመደብ ሰይሆን በመጀመሪያ በባሕርና በመቀጠልም በገቢር ነው።

በኢየሱስ እና በአዳም መካከል ያለው ተመሳሳይነት። 1️⃣“ከእንግዲህ በአንድ ሰው መተላለፍ የተነሣ ኵነኔ በሁሉ ሰው ላይ እንደ መጣ፣ እንዲሁም በአንዱ የጽድቅ ሥራ ለሰው ሁሉ ሕይወትን የሚሰጥ ጽድቅ ተገኘ።”— ሮሜ 5፥18 (አዲሱ መ.ት) አንዱ አዳም እግዚአብሔር የሰጠውን አንድ ተጻራሪ ትዕዛዝ በመተላለፉ(አታድርግ የተባለውን በማድረጉ) በሰዎች ሁሉ ላይ ኩነኔ መጣ /ኩነኔ:- በእግዚአብሔር ፊት ተቀባይነት የማጣት፥ ኃጢአተኛ ተብሎ የመቆጠር እና ኃጢአተኛ የመሆን ውጤት ነው/ ። በተመሳሳይ መልኩና በሌላው ጎን ኢየሱስ ክርስቶስ በሰራው አንድ የጽድቅ ስራ ለሰዎች ሁሉ (ለሚያምኑ ሁሉ) ሕይወትን የሚሰጥ ጽድቅ መጣ። /ጽድቅ ማለት: በእግዚአብሔር ፊት ትክክል መሆን፥ ጻድቅ ተብሎ መጠራት እና ጻድቅ መሆን/ 2️⃣“በአንዱ ሰው አለመታዘዝ ብዙዎች ኀጢአተኞች እንደሆኑ፣ በአንዱ ሰው መታዘዝ ደግሞ ብዙዎች ጻድቃን ይሆናሉ።” — ሮሜ 5፥19 (አዲሱ መ.ት) ሁለተኛው ተመሳሳይነት ይሄ ነው። በአዳም አንድ ያለመታዘዝ ስራ ሁሉም የእርሱ ትውልዶች (ልጆች) ኃጢአተኞች ሆኑ። በሌላው ጎን ነገር ግን በተመሳሳይ መልኩ በኢየሱስ ክርስቶስ አንድ የመታዘዝ ስራ /የጽድቅ ስራ: መስቀሉ፥ ሞቱና ትንሳኤው/ የሚያምኑ ሁሉ ይጸድቃሉ። የአዳም ልጆች ኃጢአተኛ ተብለው የተጠሩት በመደብ ብቻ ሰይሆን በባሕርና በገቢርም ነው። በተመሳሳይ መልኩ በኢየሱስ ክርስቶስ አምነው የእግዚአብሔር ስጦታ የሚቀበሉ ጻድቅ የሚባሉት በመደብ ብቻ ሰይሆን በባሕርና በገቢር ነው። የእግዚአብሔር ቃል እንስማ፥ በትህትና እንቀበል፥ በትጋት እናሰላስልና እንናገር በእምነትም እንታዘዝ! @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

March 6/2022 ~ Sunday. 🇵🇰 Pakistan I see millions getting saved in the nation of Pakistan. I see the kingdom of God advancing like never before. I see a powerful kingdom revival in the nation of Pakistan. Keep on praying for the nation of Pakistan! #MillionsAreComing! Hallelujah! Thank you Jesus!

Rapture! I see it is coming, are you prepared? የቤተክርስቲያን ንጥቀት! አይኖቼ አይተዋል፥ ተዘጋጅተሃል? ተዘጋጅተሻል?

A BREAK IN PRAYER IS A BREAK IN FAITH AND A BREAK IN FAITH IS A BREAK WITH GOD. -Prophet tb Joshua ጸሎት ማቋረጥ ከእምነት መቋረጥ ነው፥ ከእ
A BREAK IN PRAYER IS A BREAK IN FAITH AND A BREAK IN FAITH IS A BREAK WITH GOD. -Prophet tb Joshua ጸሎት ማቋረጥ ከእምነት መቋረጥ ነው፥ ከእምነት መቋረጥ ደግሞ ከእግዚአብሔር ጋር መቆራረጥ ነው። @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

የአብይ ጾም ሐዋሳ ውስጥ ፒያሳ በመባል በሚታወቀው መንገድ ላይ ከቤተሰቦቼ ጋር አመሻሽ ላይ ወክ እያደረግን ነበር፥ እናም በዚያ አከባቢ ያሉ ስጋና መጠጥ ቤቶች ከበፊቱ የተለየ ውጫዊ ውበት ተሰርቶላቸው ተመለከትኩ የሚበላው እና የሚጠጣው ሰዉም ብዛቱ በሰላሙ ቀን ከሚኖረው የተለየ ነው፥ ነፍስን የሚዋጉ ሙዚቃዎች በየቦታው ከፍ ባለ የድምፅ ማጉያ ተከፍተው አእምሮን ይረብሻሉ። ይሄንን ሁሉ እያስተዋልን ስንራመድ ለምን ለየት እንዳለ አጠገቤ የነበረውን ወዳጄን ጠየኩት፥ እርሱም "አብይ ፆምን እየተቀበሉ ነው" አለኝ። ምን?🤔 አዎ አብይ ፆምን እየተቀበሉ ነው። በጣም የሚያሳዝን ነው😥። ወዲያው "ሕዝቤ እውቀት ከማጣቱ የተነሳ ጠፍቷል" የሚለው የነብዩ ሆሴዕ ቃል ትዝ አለኝ፥ ትንሽ አለፍ እንዳልን "የአብይ ፆምን የመቀበል ዝግጅት" የሚል በትልቅ ባነር ተጽፎ የተለጠፈ አነበብኩ፥ የባህል አዳራሹ ውስጥ ነበር። ወደ ውስጥ ገብቼ ለመመልከት አልፈለኩም ምክንያቱም አከባቢው ሁሉ ከፍ ባለ ድምፅ ዘፈን ተከፍቶበት ይሸታል። የኃጢአት መንደር እንደሆነ ከሩቅ ማሽተት ይቻላል መጥፎ ጠረን አለው🤧። እንዴት ነው ሰው ጾምን በዘፈን፣ በጭፈራ፣ በስካር እና በሁሉም አይነት ኃጢአት የሚቀበለው? 🤔🤔🤔 የአብይ ጾምን የምትጾሙ እና ሌሎችም ይሄንን የምታነቡ ከወተት እርቆ ጠላ መጠጣቱ ምን ላይ ነው ትክክል የሚሆነው? ስጋ መመገብ አቁሞ የስጋን ሥራ ማድረጉ ምኑ ላይ ነው ጽድቁ? አረ ቆም ብላችሁ አስብ ወደ እግዚአብሔር ቃል እውነት ተመለሱ። ይልቅ ልምከራችሁ: በእነዚህ የአብይ ጾም ቀናት ከዚህ በኋላም ጠላና ቢራ መጠጣት አቁሙ እና ወተት ጠጡ!🤣😂 በደንብ ወተት ጠጡ! ወተት አእምሮን ያበለጽጋል😁 ስጋ መብላት አታቁሙ የሥጋን ስራ አቁሙ! @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

በእግዚአብሔር ፊት እውነተኛ መሆን! የእግዚአብሔር ልጆች ይሄንን ቃል ስሙ እና እንዴት በእግዚአብሔር ፊት እውነተኛ መሆን እንደምትችሉ ተማሩ! አገልጋይ ማርታ ~ ከካናዳ @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

ትሁት መሆንን ምረጡ! ትዕቢት ትልቅነት፥ ትህትናም ትንሽነት አይደለም። @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

“ወንድሞች ሆይ፥ ስለ እኛ ጸልዩ።” — 1ኛ ተሰሎንቄ 5፥25

“እኛ ግን ለጸሎትና ቃሉን ለማገልገል እንተጋለን።” — ሐዋርያት 6፥4 @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod
“እኛ ግን ለጸሎትና ቃሉን ለማገልገል እንተጋለን።” — ሐዋርያት 6፥4 @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

ለእኔ ድንቅ ነው! መጽደቅ ማለት ምን ማለት ነው? አንድ ሰው እንደ ወንጀለኛ ፍርድ ቤት ቢቀርብና ዳኛው ከወንጀል ነጻ ነህ ቢለው፥ ወንጀለኛ ተብሎ የቀረበው ሰው ጸደቀ እንላለን። መጽደቅ ማለት: ፍጹም በሆነው በእግዚአብሔር የፍርድ ዙፋን ፊት ቆሞ ከወንጀል ነጻ ነህ ወይንም ከወንጀል ነጻ ነሽ መባል ነው! ይህ እንዴት ልሆን ይችላል?“... ሥጋ ለባሽ በእግዚአብሔር ፊት እንዴት ጻድቅ ሊሆን ይችላል?” - ኢዮብ 9፥2 ኢዮብ የጠየቀውን ጥልቅ ሃሳብ እና ጭንቀት የሚገልጽ ጥያቄ በፊት እኔም ደጋግሜ እጠይቅ ነበር "እንደሰው ያለው በኃጢአት እና በዓመጽ የተሞላ ፍጡር ፍጹም በሆነው አምላክ ፋት እንዴት መጽደቅ ይችላል!?" አሁን አድጌ መልሱን ከቅዱሳት መጽሐፍት የተረዳው ቢሆንም አንዳንዴ በአድናቆት እጠይቃለሁ! ኢዮብን ይሄ ጥያቄ በታላቅ መደነቅና ጭንቀት እንደሞላው ግልጽ ነው: ምክንያቱም እርሱ መልስ ያላገኘለት ጥያቄ ነው። እግዚአብሔር ይመስገን እኛ መልስ አግኝተናል፥ በስጋ ከዳዊት ዛር የሆነው፥ በቅድስና መንፈስ ከሙታን በመነሳቱ ደግሞ የመለኮት ልጅ መሆን በሃይል የተረጋገጠው ኢየሱስ ክርስቶስ በሰራው የመስቀሉ ስራ የዘመናት ጥያቄ መልስ አግኝቷል። ሥጋን የለበሰ ሰው በእግዚአብሔር ፊት መጽደቅ (ከወንጀል ነጻ መሆን) የሚችልበት ብቸኛው መንገድ ይሄ ትሁት የናዝሬቱ ሰው የሰራውን ስራ ማመን ብቻ ነው😭 እፎይ! እርሱ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ ነው። ይሄ ትሁት የእግዚአብሔር በግ እኔ መቀጣት የነበረብኝን ቅጣት ተቀጣልኝ፥ መጎዳት የነበረብኝን ጉዳት ተጎዳልኝ፥ መገረፍ የነበረብኝን ግርፋት ተገረፈልኝ፥ መሰቀል የነበረብኝን ስቅለት ተሰቀለልኝ፥ መጠጣት የነበረብኝን መራራ ጽዋ ጠጣልኝ፥ ሞቴን ሞተልኝ! ይሄንን እውነት አምኖ የሚቀበል ሥጋ ለባሽ እግዚአብሔር ከወንጀሉ ሁሉ ነጻ እንደሆነ ተመልክቶ ይቀበለዋል። መጽደቅ ከወንጀል ነጻ መሆን፤ ትክክል ተደርጎ መቆጠር፤ ትክክል መደረግ ማለት ነው። በኢየሱስ ክርስቶስ ሞት መቀበር እና ከሙታን መነሳት የሚያምን ሁሉ በእግዚአብሔር ፊት ከወንጀሉ ነጻ ይሆናል፥ ትክክል እንደሆነ ይቆጠራል ወይም ትክክል ነህ ተብሎ በእግዚአብሔር ይጠራል፥ ትክክል ይደረጋል። ክብር ለሞተው ለተቀበረውና በሦስተኛው ቀን ከሙታን ለተነሳው ለኢየሱስ ክርስቶስ በቤተክርስቲያን በኩል ለዘላለም ይሁን። 👇👇SHARE&JOIN 👇👇 @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

ተዓምራቶች በሕይወታችሁ ያለመጠን ይበዛሉ🔥 አሜን! አሜን! አሜን! @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod
ተዓምራቶች በሕይወታችሁ ያለመጠን ይበዛሉ🔥 አሜን! አሜን! አሜን! @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

ቃላት ከቃሉ...👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod
ቃላት ከቃሉ...👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

☝️ “ቃልህ ለምላሴ ምንኛ ጣፋጭ ነው! ለአፌም ከማር ወለላ ይልቅ ጣዕም አለው።” — መዝሙር 119፥103

የሮሜ ጥናት ሮሜ 5፥15-17 በአዳምና በኢየሱስ መካከል ያለው ልዩነት(በንጽጽር) ከዚህ በፊት ባደረግነው ጥናት አዳም ልመጣ ላለው(ለክርስቶስ) አምሳሉ እንደሆነ ተመልክተናል--ሮሜ 5፥14 ---1ኛ ቆሮ 15፥45-47--- በዛሬው ጥናታችን በተከታታይ ቁጥሮች የተገለጹትን በአዳምና በኢየሱስ መካከል ያሉትን ልዩነቶች እንመለከታለን። ልዩነቶች ---ሮሜ ፥12፣15፣16፣17 ---በአዳምና በኢየሱስ መካከል ያሉ ልዩነቶች። 1) በመጀመሪያ ቁ.12 ለይ ያለውን ልዩነት እንመለከታለን-- የአዳም አንድ አለመታዘዝ በሁላችንም ላይ ውጤቱን ያስከተለ ቢሆንም እኛ ሁላችን በእርሱ ላይ የራሳችንን አለመታዘዝ ጨምረናል-- የአዳም አለመታዘዝ ኃጢአት ወደ ዓለም እንዲገባ አደረገ---በመቀጠልም የኃጢአት ውጤት ሞት ሆነ--ሞትም ለሰዎች ሁሉ ደረሰ። በተቃራኒው ኢየሱስ ክርስቶስ አንድ የጽድቅ ስራ፥ ጽድቅን ለሚያምኑ አስገኘ --የሚያምኑ ግን ይሄንን ጽድቅ ሙሉ ለማድረግ ወይንም የኢየሱስን ስራ ውጤት ለማግኘት የሚጨምሩት አንድም የጽድቅ ስራ የለም--ይሄ ጽድቅ በራሱ ፍጹም ነው--ምንም የማይጨመርበት ነው--በእምነት ብቻ የሚገኝ ነው። ✍️በአዳም ስራ ላይ ሁላችንም የራሳችንን ጨምረናል --በኢየሱስ ስራ ላይ ግን አንዳችንም የራሳችንን መጨመር አንችልም። 2) አዳም በሰራው አንድ መተላለፍ( አለመታዘዝ) ብዙዎች እንዲሞቱ አደረገ--ኢየሱስ ክርስቶስ የሰራው አንድ የጽድቅ ስራ (መታዘዙ) ለብዙዎች የተትረፈረፈ ስጦታን እና ፀጋን አስገኝቷል ያስገኛልም--ሮሜ 5፥15-- የእግዚአብሔር ስጦታና የሰው በደል በፍጹም የማይነጻጸር ነው--ሰው የቱንም ያህል በደለኛ ቢሆንም የእግዚአብሔር ነጻ ስጦታ ከሰው በደል የበለጠ ነው። 3) የአዳምን አንድ ያለመታዘዝ ስራ ተከትሎ በሁላችንም ላይ ኩነኔ (Condemnation) መጣ-- የኢየሱስ ክርስቶስ አንድ የጽድቅ ስራ ተከትሎ ጽድቅ (Justification) አያሌ መተላለፍን አልፎ መጣ---ሮሜ 5፥16-- ✍️የአዳም ስራ ኩነኔን ስያስከትል---የኢየሱስ ክርስቶስ ስራ ጽድቅን አስከትሏል። 4) በአዳም አንድ ያለመታዘዝ ስራ ሞት በሰው ዘር ሁሉ ላይ ጨቋኝ ንጉሥ መሆን ቻለ---በኢየሱስ ክርስቶስ አንድ የጽድቅ ስራ በማመን የተትረፈረፈ ፀጋና የጽድቅ ስጦታን የሚቀበሉ ሁሉ በዚህ ሕይወት ይነግሳሉ---ሮሜ 5፥17 ✍️የአዳም ስራ ሞትን አነገሠ ---የኢየሱስ ክርስቶስ ስራ አማኞችን በሕይወት አነገሠ። ኢየሱስ ክርስቶስ በሰራው የጽድቅ ስራ የሚያምኑ ሰዎች የተትረፈረፈ ፀጋ /abundant Grace/ ወይም ከበቂ በላይ የሆነ ፀጋን እና ጽድቅን እንደ ስጦታ ከእግዚአብሔር መቀበል ይችላሉ። በኢየሱስ ክርስቶስ ስራ ከሰይጣን ስልጣን ነጻ ወጥተናል ---ወደ እግዚአብሔር መንግስት ተጨምረናል ---ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር አብረን የምንገዛ ተደርገናል --ቆላ 1፥13፣ ኤፌ 2፥6--- 👇👇👇ቀጣይ👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

እውነተኛ የፍቅር አስተማሪ እና ለፍቅር የሞተ ሰው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ከእግዚአብሔር ፍቅር ተለይቶ የትኛውም አይነት ፍቅር ትርጉም የለውም።

#Valentine'sDay ሁላችሁም ስለዚህ Valentine's ቀን የተወሰነ እውቀት እንዳላችሁ እርግጠኛ ነኝ። ነገር ግን ስንቶቻችሁ ይሄንን በዓል በተመለከተ ሙሉ እውቀት አላችሁ? ይሄንን ቀን እና በዓል በተመለከተ እጅግ በጣም ብዙ ክርስቲያኖችን ጨምሮ ትክክለኛው እውቀት ስለሌላቸው በጥቅሉ "የፍቅር ቀን" ወይም "የፍቅረኛሞች ቀን" ነው በማለት ነው የሚገልጹት። ቀኑ በዘመናዊው ዓለም ፍቅረኛሞች ስጦታ የሚለዋወጡበት ቀን እና የፍቅር ጊዜ አብረው የሚያሳልፉበት ቀን እንደሆነም ይነገራል። እኛ በኢየሱስ ክርስቶስ የምናምን ግን ነገሮችን ሁሉ በጥንቃቄ መመርመር እና ከስህተት እራሳችንን የመጠበቅ ሃላፊነት አለብን። Valentine's day ስያሜውን ያገኘው Valentine ከተባለ የካቶሊክ ቤተ እምነት አባት ነው። ነገሩ እንደዚህ ነው ይህ Valentine የተባለ ሰው በዘመኑ የነበረው የመንግስት ስርዓት አንዳንድ ፖለቲካዊ ትርፎችን ለማግኘት ጋብቻን ይከለክላል፥ ይሁን እንጂ Valentine የተባለው ሰው የመንግስት አዋጅ ባለመቀበል በስውር ወንዶችንና ሴቶችን ያጋባ ነበር፥ በኋላም Valentine በዚህ ድርጊቱ ምክንያት በመንግሥት ተይዞ የመንግስትን ስርዓት ባለመታዘዝ ተፈርዶበት ተገደለ። ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ነበር ሰይጣንን እና ልጆች ይሄንን አጋጣሚ በመጠቀም ቀድሞ LUPERCALIA በመባል የሚታወቀውን የሮም በዓል በተንኮል ስሙን Valentine'sDay በሚል ቀይረው ያመጡት። ለምን በዓሉ Valentine'sDay ተባለ ለሚለው ጥያቄ የሚሰጠውም መልስ Valentine የተባለውን "ለፍቅር የሞተ" ሰው ለማሰብ ነው የሚል ነው። ይህም በዓሉን ክርስቲያናዊ በዓል ለማስመሰል ነው። LUPERCALIA የ Valentine's በዓል አባት ነው ማለት ይቻላል። የLUPERCALIA በዓል LUPERCUS በመባል የሚታወቀውን የሮም ጣኦት ለማምለክ የሚከበር በዓል ነበር። በዚህ በዓል ላይ ከሚደረጉት ነገሮች አንዱ በእጣ ሴቶችን እና ወንዶችን ማገናኘት፥ ኢ-ሞራላዊ የሆኑና ከጋብቻ ውጭ የሆኑ ግብረስጋ ግንኙነቶችን መፈጸም ጨምሮ ውሾችን LUPERCUS ለተባለው ጣኦት መስዋዕት አድርጎ ማቅረብ ነበር። Valentine'sDay ስሙን ለወጠ እንጂ የቀደመው የአባቱ የLUPERCALIA በዓል ባሕርያት የሚታዩበት ነው። ድንግል ሴቶች ባላቸው ላልሆነ ሰው ክብራቸውን በፈቃዳቸው የሚሰጡበት እና ለሰይጣን የሚሰውበት በዓል ነው። ክርስትያን በፍቅር ግንኙነት ውስጥ ለአጋሩ ፍቅሩን የሚገልጥበት ጤነኛ የሆነ መንገድ አለ። ስጦታ መለዋወጥ አይደለም ችግሩ ከበስተጀርባው ያለው ስውር እጅ ነው። ክርስቲያን ፍቅረኛማቾች የፍቅር ግንኙነታችሁን ዛሬ ValentinesDay እያሉ ዓለማዊያን በሚያከብሩበት መንገድ የምታከብሩ ከሆን ዓለምን እየመሰላችሁ እንደሆነ እውቁ፥ ዓለምን እየወደዳችሁም ጭምር ነው። ሌላ ቀን ምረጡ ለፍቅር አጋራችሁ በራሳችሁ መንገድ ስጦታ ስጡ እግዚአብሔር ቅዱስ ነውና ቅዱሳን ሁኑ። ተጨማሪ እውቀት ለማግኘት የራሳችሁን ጥናት አድርጉ። ይሄንን ከወቅን በኋላ በመንገዳቸው ብንሄድ የእግዚአብሔር ጠላቶች ሆነናል።“አመንዝሮች ሆይ፥ ዓለምን መውደድ ለእግዚአብሔር ጥል እንዲሆን አታውቁምን? እንግዲህ የዓለም ወዳጅ ሊሆን የሚፈቅድ ሁሉ የእግዚአብሔር ጠላት ሆኖአል።” — ያዕቆብ 4፥4 በመጨረሻም የምናደርገው እያንዳንዱን ነገር በእውቀት ይሁን፤ ፀጋ ይብዛላችሁ። 👇👇SHARE &JOIN👇👇 @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod