es
Feedback
TheDeepThingsOfGod

TheDeepThingsOfGod

Ir al canal en Telegram

Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!

Mostrar más
1 810
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
Sin datos30 días
Archivo de publicaciones
"Time for everything- time for prayer and time to RETURN HOME after the service." ትላንትና ባገለገለው የመጨረሻ አገልግሎቱ ነቢዩ ወደ ተባረከው ጌታችን
"Time for everything- time for prayer and time to RETURN HOME after the service." ትላንትና ባገለገለው የመጨረሻ አገልግሎቱ ነቢዩ ወደ ተባረከው ጌታችን ከመሄዱ ከሰዓታት በፊት የተናገረው ቃል ነበር:- "ለሁሉም ጊዜ አለው- ለመጸለይ ጊዜ አለው፣ ከአገልግሎት በኋላም ወደ ቤት ለመመለስ ጊዜ አለው።" ይህ ስለ ራሱ ወደ ጌታ መሄድ የተናገረው የመጨረሻ ትንቢት ነዉ፤ ለእኛ ግን አገልግሎቱና ሕይወቱ ሁልጊዜም ትንቢት ነዉ። ለእርሱ ሕይወት ክርስቶስ ነበር፣ ሞትም ቢሆን ጥቅሙ ነዉ፤ ለእኛ ግን ትልቅ ሃዘን ነዉ ይህም ቢሆን ለእግዚአብሔር ሉዓላዊነት በመገዛት ስለ ሁሉም እግዚአብሔርን ይባረክ እንላለን። ልቤ እጅግ ተሰብሯል! የተባረከው ጌታ በነቢዩ ወደ ቤት መመለስ ያዘኑትን ሁሉ እንዲያጽናና እየጸለይኩ ነዉ።

When a child of God is obedient, demons should respect him. ~Prophet makandiwa

This is powerful! Do you believe in the Holy Ghost? ~When He touches you don't let him go! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

የምትቀበለው የእግዚአብሔር ቃል መጠን፤ በሕይወትህ የምትገልጠውን የእግዚአብሔርን ባሕርይ መጠን ይወስናል። ~ቢሾፕ ዴቪድ ኦዮዴፖ @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTh
የምትቀበለው የእግዚአብሔር ቃል መጠን፤ በሕይወትህ የምትገልጠውን የእግዚአብሔርን ባሕርይ መጠን ይወስናል። ~ቢሾፕ ዴቪድ ኦዮዴፖ @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

~ዘማሪት ~አይዳ አብርሃም ~የመዝሙር ግብዣ~ስላንተ sʜᴀʀᴇ ◈ JOIN ◈ @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ዮሐንስ 7 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ³⁷ ከበዓሉም በታላቁ በኋለኛው ቀን ኢየሱስ ቆሞ፦ ማንም የተጠማ ቢኖር ወደ እኔ ይምጣና ይጠጣ። ³⁸ በእኔ የሚያምን መጽሐፍ እንዳለ፥ የሕይወት ውኃ ወንዝ ከሆዱ ይፈልቃል ብሎ ጮኸ። ³⁹ ይህን ግን በእርሱ የሚያምኑ ሊቀበሉት ስላላቸው ስለ መንፈስ ተናገረ፤ ኢየሱስ ገና ስላልከበረ መንፈስ ገና አልወረደም ነበርና።

የተጠሙ ብቻ መንፈስ ቅዱስን መቀበል ይችላሉ። Only the thirsty receive the Holy Spirit.

#ራስን_የመግዛት_መንፈስ #TheSpiritOfSelf-control ራስን የመግዛት መንፈስ ትክክለኛ ያልሆነውን ነገር ባለማድረግ ብቻ ሰይሆን ትክክለኛ የሆነውን ነገር በማድረግም ነዉ የሚገለጠው። ትክክለኛ ያልሆነውን ነገር የሚያደርግ እና ትክክለኛ የሆነውን ነገር ለማድረግ የሚፈራ ሰው ሁለቱም አንድ ናቸው፤ ራሳቸውን እየገዙ አይደለም። ትክክለኛ የሆነውን ነገር አለማድረግ በራሱ ስህተት ነዉ። የእግዚአብሔር ልጆች ራስን የመግዛት መንፈስ ከእግዚአብሔር ተቀብላችኋል ስለዚህ ትክክለኛ ያልሆነውን ነገር እንደማታደርጉ ሁሉ ትክክለኛ የሆነውን ነገር ለመናገር እና ለማድረግ ከአንበሳ ይልቅ ደፋሮች ሁኑ። አትፍሩ! 👇👇👇ተቀላቀሉ👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

“እንዲሁም ደግሞ መንፈስ ድካማችንን ያግዛል፤ እንዴት እንድንጸልይ እንደሚገባን አናውቅምና፥ ነገር ግን መንፈስ ራሱ በማይነገር መቃተት ይማልድልናል፤” — ሮሜ 8:26 “Likewise the Spirit also helpeth our infirmities: for we know not what we should pray for as we ought: but the Spirit itself maketh intercession for us with groanings which cannot be uttered.” — Romans 8:26 (KJV)

እንግዳ ነገር አለ ፊቴ እንግዳ ነገር አለ ፊቴ የእግዚአብሔርን ማዳን በአይኔ የማይበት በዙፋኑ በላው የተቀጠረ እለት ይሄኛው ያኛው ያረጀው ያልፍና ሁሉን አድስ አድስ አድስ ያደርግና አይን ያላየው ጆሮ ያልሰማው በሰው ልብ ከቶ ያልታሰበው ጌታ ለሚወዱት ብሎ ያዘጋጀው። #አሜን! 🖐😭 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

1ኛ ጢሞቴዎስ 4 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁷ ነገር ግን ለዚህ ዓለም ከሚመችና የአሮጊቶችን ሴቶች ጨዋታ ከሚመስለው ተረት ራቅ። እግዚአብሔርን ለመምሰል ግን ራስህን አስለምድ። ⁸ ሰውነትን ለሥጋዊ ነገር ማስለመድ ለጥቂት ይጠቅማልና፤ እግዚአብሔርን መምሰል ግን የአሁንና የሚመጣው ሕይወት ተስፋ ስላለው፥ ለነገር ሁሉ ይጠቅማል። ⁹ ይህ ቃል የታመነ ሁሉም እንዲቀበሉት የተገባ ነው፤ ¹⁰ ይህን ለማግኘት እንደክማለንና፥ ስለዚህም እንሰደባለን፤ ይህም ሰውን ሁሉ ይልቁንም የሚያምኑትን በሚያድን በሕያው አምላክ ተስፋ ስለምናደርግ ነው። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

Demons respect the Glory in your life not your dressing style. #Rebel against the Devil! አጋንንት በሕይወታችሁ ያለውን የእግዚአብሔርን ክብር እንጂ
+3
Demons respect the Glory in your life not your dressing style. #Rebel against the Devil! አጋንንት በሕይወታችሁ ያለውን የእግዚአብሔርን ክብር እንጂ ልብሳችሁን አያከብሩም።

እውነተኛ መስታወት እውነተኛ መስታወት ሰው ምን እንደሚመስል የሚያሳይ ብቻ ሰይሆን ምን መምሰል እንዳለበትም ጭምር የሚያሳይ ነዉ። እንደዚህ አይነት መስታወት አለን? ምን እንደምመስል ብቻ ሰይሆን ምን መምሰል እንዳለብኝም የሚያሳየኝ መስታወት አለ? አዎ! በሚገባ አለ፤ ነገር ግን ይሄ መስታወት ቁሳዊ መስታወት አይደለም፡ መንፈሳዊ መስታወት ነዉ። ይህ መስታወት ለሰው አያዳላም፤ ሰውን እየመረጠ አያከብርም: ሰው የሆነውን ያንኑ ያሳየዋል። የረከሰውን አያጸድቅም፣ የጸደቀውንም አያረክስም፤ ይህ መስታወት እውነተኛ ነዉ። ይህንን መስታወት ከሌሎች መስታወቶች ሁሉ የሚለየው አንዱ ነገር ሰው ምን መምሰል እንዳለበትም ጭምር ማሳየት መቻሉ ነዉ፤ ይህ መስታወት የእግዚአብሔር ቃል ነዉ። በዚህ መስታወት ፊት በመቆም ራሳችሁን እንድታዩና ምን መምሰል እንደሚገባችሁ እንድታውቁ ግብዣዬ ነዉ። Join 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ገነቴ ነህ~ኢየሩሳሌም ነጊያ @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

THE BIBLE IS YOUR VISA THAT GIVES YOU ACCESS TO THE REALM OF LIGHT. -Victor. “We have also a more sure word of prophecy; whereunto ye do well that ye take heed, as unto a light that shineth in a dark place, until the day dawn, and the morning star arise in your hearts:” — 2 Peter 1፥19 (KJV) @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

መንፈስ ቅዱስ እንደዚህ አለኝ፡- የልጆቼን ታሪክ ከታች ወደ ላይ እለውጣለሁ። ሕይወታቸውን ከውስጥ ወደ ውጭ እለውጣለሁ። በመንፈስ ቅዱስ ሃይል መነካት የሚፈልግ አሁኑኑ በእምነት #አሜን በማለት ይጻፍ፤ እናም በልሳን መጸለይ ይጀምር። #አሜን The Spirit Of God Said:- I will change your story downside-Up, I will change your life from inside-out. If you want to be impacted by the power of the Holy Spirit, type a big #Amen by faith and pray in the spirit now. #Type_Amen!

THE WORD OF GOD IS THE CODE OF LIFE. #Victor @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

....በእግዚአብሔር መንግስት ውስጥ የማይሻር አሻራ ያላቸው እና የሰይጣንን መንግስት ክፉኛ የጎዱ ሰዎች ሁሉ የቃል እና የመንፈስ ሰዎች ናቸው.... አንዳንዶቻችን ከመሰለን የእነርሱን የአገልግሎት ቪድዮዎች በማየት ብቻ እነርሱ ለክርስቶስ የፈጠሩትን ተጽእኖ መፍጠር የሚቻል አይደለም፤ እነርሱ የተከተሉትን መንገድ መከተል አለብን! እኛም የቃሉና የመንፈሱ ሰዎች መሆን ይጠበቅብናል። ጀነራል Smith Wigglesworth የግዴታ በየ 25 ደቂቃው አንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ምዕራፍ ያነብና ያሰላስል ነበር፤ ይሄንን ለብዙ አስርት አመታት ከማድረጉ የተነሳ ከመጽሐፍ ቅዱስ ውጭ ሌላ ነገር ማውራት አይችልም ነበር😭፤ አፉ በተከፈተ ቁጥር የእግዚአብሔር ቃል እንደተሳለ ሰይፍ ከአንደበቱ ይወጣ ነበር፤ ሰዎች እርሱ ባለበት ከመጽሐፍ ቅዱስ የተለየ ነገር ከተናገሩ ወደ ንስሃ ጸሎት ይመራቸው ነበር። ጀነራል Kenneth E. Hagin ግልጽ የሆነ አገልግሎት ከመጀመሩ በፊት አድስ ኪዳንን መቶ ሐምሳ (150) ጊዜ አንብቧል😭። የእግዚአብሔር ቃል ከራስ ጸጉር እስከ እግር ጥፍሩ ተቆጣጥሮት ነበር፤ እነዚህ ሰዎች ይተነፍሱ የነበረው የእግዚአብሔርን ቃል ነበር ማለት ይቻላል። ለዚህ ነው አንደበታቸውን በከፈቱ ቁጥር የሚፈጅ እሳት በፊታቸው ይሄድ የነበረው🔥። ለምሳሌ እነዚህን የእምነት አባቶች ጠቀስኩ እንጂ ሁሉም በእግዚአብሔር ምክር የቆሙ ሰዎች የመንፈሱና የቃሉ ሰዎች ናቸዉ። የሃይላቸው ሚስጥር ይህ ነዉ። 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

“እግዚአብሔርን ሁል ጊዜ በፊቴ አድርጌአለሁ፤ እርሱ በቀኜ ስላለ አልናወጥም።” — መዝሙር 16፥8 (አዲሱ መ.ት) የሚያናውጣችሁን ሰይሆን እግዚአብሔርን በፊታችሁ ስታደርጉት፤ አንደበታችሁን በእምነት ከፍታችሁ እግዚአብሔር በቀኜ ነዉ፣ እርሱ ሃይሌ ነዉ ስለዚህ አልናወጥም ትላላችሁ። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ችግርህን እወቅ ማለት ችግርህን አሰላስል ማለት አይደለም። ችግርን ማወቅ መፍትሔን ለማግኘት የመጀመሪያው ቁልፍ ነዉ፤ ችግርን በልብ ይዞ ማብሰልሰል፣ ማሰላሰል፣ ማውራት ግን እዚያው ተክሎ የሚያኖር ችንካር ነዉ። ችግርን ነቅሶ መለየት ከዚያም መፍትሄው ላይ ማተኮር። መፍትሔውን ማሰብ፣ ማሰላሰልና ማውራት፤ መፍትሔውን ወደ ውስጥ ለማስረጽ የሚቻለውን ሁሉ ማድረግ ትክክለኛው ድርጊት ነዉ። ችግራችሁን እወቁ ነገር ግን ችግራችሁን እያሰላሰለችሁ በጸጸት መንደድና መጨነቅ ትልቅ ስህተት ነዉ። የእግዚአብሔርን ቃል አሰላስሉ። ከእግዚአብሔር ጋር የታረቃችሁበትን የክርስቶስን መስቀል አስቡ። 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit