es
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Ir al canal en Telegram

📈 Análisis del canal de Telegram የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

El canal የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 14 356 suscriptores, ocupando la posición 6 146 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 357 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 14 356 suscriptores.

Según los últimos datos del 23 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 507, y en las últimas 24 horas de 14, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 25.68%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 13.08% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 3 681 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 875 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 28.

📝 Descripción y política de contenido

No se ha proporcionado la descripción del canal.

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 24 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

14 356
Suscriptores
+1424 horas
+1027 días
+50730 días
Archivo de publicaciones
ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ዘተናገረ በበዓለ ርእሰ ዐውደ ዓመት ዘዕሥራ ምእት ዐሠርቱ ወሰብዓቱ ዓመተ ምሕረት በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፤ ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትገኙ፤ የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፤  በሕመም ምክንያት በየፀበሉና በየሆስፒታሉ ያላችሁ፤ እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤት የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት በሙሉ፡፡ ሁለመናችንን በሐዲስ ምግብና እየመገበ የሚጠብቀን አምላካችን እግዚአብሔር እንኳን ከዘመነ ዮሐንስ 2016 ዓ.ም. ወደ ዘመነ ማቴዎስ 2017 ዓ.ም. በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ!! ‹‹ሐድሱ መንፈሰ ልብክሙ፤ የልባችሁን መንፈሳዊ አእምሮ አድሱ›› (ኤፌ. ፬÷፳፫)፤ በገሃዱ ዓለም በግልጽ እንደምናስተውለው ከሞላ ጎደል የማያረጅ የለም የማይታደስም የለም፤ መታደስ ባይኖር ኖሮ ሕይወታውያን ፍጡራን በሕይወት መቀጠል አይችሉም ነበር፤ የዘመን መታደስም የሥነ ፍጥረት አንዱ አካል ነው፤ እኛ ሰዎችም የሕዳሴው መሪዎች ሆነን የተሾምንባትን ምድር በየጊዜው በልማት እንድናድሳት እግዚብሔር አዞናል፤ የሃይማኖት ትልቁ ተስፋም መታደስ ላይ የተመሠረተ ነው፤ ዘመንም እንደ ሌላው ያረጃል፤ ይታደሳልም፤ “ወናሁ እገብር ኵሎ ሐዲሰ እነሆ ሁሉን አዲስ አደርጋለሁ” የሚለው የእግዚአብሔር ቃልም የዚህ አስረጅ ነው፤ በዚህ ሕገ እግዚአብሔር መሠረት እነሆ አሮጌውን ዘመን የምንሸኝበት አዲሱን ዘመን ደግሞ የምንቀበልበት ምዕራፍ ላይ ነን፤ የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት፡- ፍጥረታትን በማደስ ሕይወትን የማስቀጠል ሥልጣን በዋናነት የእግዚአብሔር ብቻ መሆኑ ለጥያቄ የሚቀርብ አይደለም፤ ይሁን እንጂ ሰውም ሥነ ፍጥረትን በማደስና በማጐስቈል ረገድ ያለው ሚና ቀላል አይደለም፤ ይህም ሰው በምድር ላይ እንዲሠለጥን ወይም ፍጥረትን እንዲገዛና እንዲመራ በፈጣሪ ከተሰጠው ሥልጣን የሚመነጭ ነው፤ ዛሬም ዓለማችን በመታደስ ያይደለ በማርጀት ላይ የምትገኘው ከሰዎች ድርጊት የተነሣ እንደሆነ እንገነዘባለን፤ የአየሩ መለወጥ፣ የበረዶው መቅለጥ፣ የሙቀቱ ማሻቀብ፣ የዝናሙ ማጥለቅለቅ፣ የባሕሩ መናወጥ ወዘተ. እየተፈጠረ ያለው ኃላፊነት ከጐደለው የሰው አጠቃቀም የተነሣ እንደሆነም ተደጋግሞ እየተነገረን ነው፤ እኛም በዓይናችን እያየን ነው፤ ከዚህ በተለየ ደግሞ በተወሰነ ደረጃም ቢሆን ሰው ምድረ በዳውን ወደ ሐመልማለ ገነት ሲቀይር የሚስተዋልበት ሌላ ገጽታ አለ፤ ይህ የሚያሳየው ሰው በሥነ ፍጥረት ላይ የማደስና የማጐስቈል ብሎም የማጥፋት ሚና ያለው መሆኑን ነው፤ ሰውም እንደሌላው ሥነ ፍጥረት የሚያረጅም የሚታደስም ነው፤ ይህም በብዙ አቅጣጫ ሊከሠት ይችላል፤ ሰዎች በተናጠልም ሆነ በጋራ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ሁለቱንም ማለትም ማርጀትና መታደስን ሊያስተናግዱ ይችላሉ፤ ሰዎች በመንፈሳዊ፣ በኢኮኖሚያዊ በማኅበራዊና በመልካም አስተዳደር ወዘተ. የላቀ ዕድገትን ሲያስመዘግቡ በመታደስ ላይ እንደሆኑ ይታወቃል፤ የዚህ ተቃራኒ የሆነውን ይዘው እየተጓዙ ከሆነ ደግሞ ተቃራኒውን ወይም ማርጀትን እያስተናገዱ እንደሆነ ይታወቃል፤ ነገር ግን የእግዚአብሔር ፈቃድ ሰዎች በመንፈሳቸውም ሆነ በአእምሮአቸው፣ በነፍሳቸውም ሆነ በአካላቸው በመታደስ እንዲኖሩ እንጂ እርጅና እንዲጫጫናቸው አይፈልግምና “የልባችሁን መንፈስ አድሱ” በማለት ያስተምረናል፤ የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት! የክርስትና ሃይማኖት የመጨረሻው ግብ የፍጥረት መታደስ ነው፤ ይህም ማለት የሃይማኖቱ አስተምህሮ መዳረሻ ከሞት በኋላ ትንሣኤ ከዚያም ፍጻሜና እንከን የሌለው ጣዕመ ሕይወት አለ ብሎ ሰውን ለዘላለማዊ ሕዳሴ ማብቃት ነው ማለት ነው፤ ከዚህ አንጻር የሰው የመጨረሻ ዕድሉ ማርጀት ሳይሆን መታደስ እንደሆነ እንገነዘባለን፤ እግዚአብሔር የሰውንና የፍጥረታትን መታደስ የሚሻው በሰማያዊው ዓለም ብቻ ሳይሆን በምድራዊው ዓለምም ጭምር ነው፤ ለዚህም ነው በየወቅቱ የሥነ ፍጥረትን ውበት እያደሰ የሚመግበን፤ አሁን ትልቁ ጥያቄ የሚሆነው እኛስ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ለመታደስ ተዘጋጅተናል ወይ? የሚለው ነው፤ ዛሬ እያንዳንዳችን ይህንን ጥያቄ አንሥተን ኅሊናችንን በጥልቀት መጠየቅ አለብን፤ በዚህም ሳናበቃ መልሱን በትክክል ማግኘት አለብን፤ በሁለንተናችን ለመታደስም ቈራጥ ውሳኔ በራሳችን ላይ ማሳለፍ አለብን፤ አዲሱ ዘመን አዲስና ብሩህ የሆነ የደስታ ሕይወት ሊያጐናጽፈን የሚችለው በዚህ መንፈስ ተቀብለን ስንጠቀምበት ነው፤ የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት! እኛ ኢትዮጵያውያን ለብዙ ዘመናት የታደሱ ያይደሉ በርካታ ዓመታት ተጭነውን አልፈዋል፤ ቀድሞ እንበልጣቸው ከነበሩ አህጉር በታች ሆነንም በርካታ ዓመታትን አስቈጥረናል፤ የእርስ በርስ ግጭት፣ ረኃብ፣ ጦርነት፣ ድህነት፣ ኋላ ቀርነት የመልካም አስተዳደር እጦት በዓለም ፊት ልዩ መለያችን ሆኖአል፤ ዛሬም ከዚህ አልተላቀቅንም ብቻ ሳይሆን እንዲያውም አጠናክረን ለማስቀጠል ውል የገባን እስክንመስል ድረስ እየቀጠልንበት እንገኛለን፤ በእውነቱ እንዲህ የመሰለ ልምድ ልናፍርበትና ንስሐ ልንገባበት እንጂ ልናስቀጥለው አይገባም፤ በተፈጥሮ የታደለች ሁሉንም አሟልታ የምትገኝ ኢትዮጵያን የመሰለች ሀገር ይዘን ከሰው በታች ሆነን ስንገኝ በስንፍናችሁ ከምንባል በቀር የሀብተ ጸጋ እጥረት አለባችሁ የሚለን አናገኝም፤ ስለዚህ አሁንም ለኢትዮጵያውያን ልጆቻችን በአጽንዖት የምናስተላልፈው መልእክት ኢትዮጵያ ለኢትዮጵያውን አይደለም ለዓለም የሚተርፍ ሀብተ ጸጋ አላትና ለኔ ለኔ በመባባል የሕዝባችንን ሰቆቃው አናስረዝም፤ ኢትዮጵያ የሁሉም ኢትዮጵያውያን ናት የሚለውን ጥሬ ሓቅ በደምብ አላምጠን መዋጥ አለብን፣ ከዚያም በእኩልነትና በአንድነት ሀገራችንን እናድስ፤ ከሌሎች በደባል የሚመጡ ነገሮችን ሳይሆን የሀገሪቱ በሆኑ ዕሤቶች እንመራ፤ ለበርካታ ዓመታት የተሸከምነው ደባል የአስተዳደር ስልት ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር የሚጣጣም ሆኖ አልተገኘም፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከምንም ከማንም በላይ በፈጣሪው እንደሚመካ እሱንም አጥብቆ እንደሚያምን ልኂቃኖቻችን ተገንዘቡልን፤ እኛ ኢትዮጵያውያን ከሦስት ሺሕ ዓመታት በላይ ባስቆጠረ ታሪካችን ከእግዚአብሔር ተለይተን አናውቅም፤ በዚህም ተጠቃሚዎች እንጂ ተጐጂዎች የሆንበት ጊዜ የለም፤ በለመደው እምነት ባህልና ዕሤት ሕዝቡን ብንመራው ሁሉም ነገር ቀላል ይሆንልናል፤ ከዚህ ውጭ እንምራህ ብንለው ግን ያጋጠመንን ችግር ማስቀጠል ነው የሚሆነው፤ ስለዚህ የሁሉም መነሻ ማለትም የክፋትም ሆነ የደግነት መነሻ ውሳጣዊ አእምሮአችን ነውና እሱን በማደስ በአዲሱ ዓመት አገራችንን እንድናድስ በዚህ አጋጣሚ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡

ተለቀቀ ልዩ የአዲስ ዓመት ዝማሬ አበባ አየሽ ወይ https://youtu.be/WFvxRL8dJHg

እንኳን ለቅዱስ ሩፋኤል በዓል በሰላም አደረሳችሁ! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook
እንኳን ለቅዱስ ሩፋኤል በዓል በሰላም አደረሳችሁ! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ሚኒስትሪ ተፈታኞች የምርቃትና የሽልማት መርሓ ግብር ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት በ02/13/2016 ዓ.ም አካሄደ፡፡ ----------------------------------------------- የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት በ2016 ዓ.ም የሚኒስትሪ ፈተና  ከ2000 በላይ ተማሪዎች የፈተነ ሲሆን፤ ይህ  የሚኒስትሪ ተፈታኞች የምርቃትና የሽልማት መርሓ ግብር ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳምና ሥራ አመራር መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ጠባቂ ፡ ክቡር መልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ገብረ መድኅን ንጉሤ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፡ የሀገረ ስብከቱ የየመምሪያ ክፍል ኃላፊዎች ፡ የአድባራት አስተዳዳሪዎች ፡ አበው ካህናት ፡ የአንድነቱ ከፍተኛ አመራሮች ፡ ከልዩ ልዩ ወረዳዎችና አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት የተውጣጡ የደረጃ ተማሪዎችና አመራሮች በተገኙበት በአዳማ ደብረ ታቦር ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ መሰብሰቢያ አዳራሽ ተካሐዷል፡፡ መርሐግብሩ በብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ መሪነት በጸሎተ ወንጌል የተጀመረ ሲሆን የዝማሬ አገልግሎት በአዳማ ናዝሬት ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ቤተ ክርስቲያን ፈለገ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ዘማሪያን የቀረበ ሲሆን በዲ/ን ፍስሐ ታደሰ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ም/ሰብሳቢና የትምህርት ክፍል ኃላፊ በአዲስ መልክ እየተተገበረ በሚገኘው ሥርዓተ ትምህርት ዙሪያና ስለ አፈጻጸሙ ዝርዝር ሪፖርት ቀርቧል፡፡ በመቀጠልም የአንድነቱ ተቀዳሚ ም/ሰብሳቢ ኢንጅነር ዓለም አንተ አበጀ የሰንበት ት/ቤት መዋቅር በሚል ርዕሰ ጉዳይ ሰንበት ት/ቤት አወቃቀር የሰንበት ት/ቤት ተልዕኮ የሰንበት ት/ቤት አስፈላጊነት ምን እንደሚመስልና የሰንበት ት/ቤት መዋቅር በቤተ ክርስቲያን ላይ መዘርጋቱ ያለው ፋይዳ ምን እንደሚመስል ዘርዘር ያሉ ገለጻዎችን አቅርቧል፡፡ በመቀጠልም  ሚኒስትሪ ባስፈተኑ የሁሉም አጥቢያ ሰ/ት/ቤት የደረጃ ተማሪዎች ፣ በየወረዳ ቤተ ክህነት የደረጃ ተማሪዎች እና እንደ ሀ/ስብከት ለደረጃ ተማሪዎች በብፁዕ አባታችን አቡነ ጎርጎርዮስ በወጣት ከተማ ደረጀ  የአንድነቱ ፀሐፊ አቅራቢነት የካርድና ሽልማት የተሰጠ ሲሆን ሲሆን ክቡር መልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ገብረ መድኅን ንጉሤ የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ትምህርተ ወንጌል ሰጥተዋል፡፡ በመጨረሻም ብፁዕ አባታችን አባታዊ መልእክት ያስተላለፉ ሲሆን በመልእክታቸው " የሀገረ ስብከታችን ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ታቅፋችሁ ከሁሉም አቅጣጫ የተሰባሰባችሁ ወጣቶች በዚህ ልክ በመሰባሰባችሁ ታላቅ ደስታ ይሰማኛል፡፡ ይኽ ለመጀመሪያ ጊዜ የሆነ ታላቅ ሥራና አዲስ ራዕይ በመሆኑ እንኳን ደስ አላችሁ " ያሉ ሲሆን " የሰንበት ት/ቤት አገልግሎት የፈቃደኝነትና ራስን ሰጥቶ የማገልገል ሕይወት ነው፡፡ የቤተክርስቲያን ጉዳይ ይመለከተኛል በማለት የተሠለፋችሁ ተረካቢዎች ናችሁ፡፡ በዚኽ ዘመን ወጣቱ የት እንደሚውል ምን እንደሚፈጽም አሰላለፉ ከወዴት እንደሆነ ታውቁታላችሁ ወጣቶችን ሁሉም ይሻማቸዋል ሁሉም ይፈልጋቸዋል እናንተ ግን እግዚአብሔር ይሻለናል በማለት በዚህ አገልግሎት በመሰማራታችሁ ልባዊ ምስጋናዬን አቀርባለሁ ፡፡ እንኳንም በዚህ መልክ አገኘኋችሁ ደስታዬ ወደር የለውም፡፡ልጆች ሰንበት ትምህርት ቤት በማደጋቸው ከልጆች መባረክ ባሻገር ቤተሰቦቻቸውም ይባረካሉ፡፡ " በማለት በጸሎተ ቡራኬ መርሐግብሩ ፍጻሜውን አግኝቷል፡፡ መረጃው የም/ሸ/ሀ/ስብከት ሰ/ት/ቤቶች አንድነትና  የሐመረ ተዋሕዲ ሚዲያ ነው፡፡ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በሀገረ አሜሪካ የነበራቸውን ሐዋርያዊ አገልግሎት አጠናቅቀው ወደ
+5
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በሀገረ አሜሪካ የነበራቸውን ሐዋርያዊ አገልግሎት አጠናቅቀው ወደ መንበራቸው በዛሬው ዕለት ተመልሰዋል። በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት የመምሪያ ሐላፊዎች ፣ የደብራት አስተዳዳሪዎች እንዲሁም ቁጥራቸው በርከት ያሉ የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች ተገኝተው አቀባበል አድርገዋል። የቀጨኔ ደብረ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም እና ትጉኀን ቅዱስ ገብርኤል ሊቃውንት እንዲሁም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ልዩ ያሬዳዊ ቃለ እግዚአብሔር አቅርበዋል። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

የቅዱስ ፓትርያርኩን አቀባበል መርሐ ግብር በነገው እለት ማለዳ በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ለማከናወን የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ሥራ ተጠናቀቀ። የአቀባበል መርሐ ግብሩን በተያ
+3
የቅዱስ ፓትርያርኩን አቀባበል መርሐ ግብር በነገው እለት ማለዳ በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ለማከናወን የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ሥራ ተጠናቀቀ። የአቀባበል መርሐ ግብሩን በተያዘለት መርሐ ግብር መሰረት በድምቀት ለማከናወን የገዳሙ አስተዳዳሪ ፣ዋና ጸሐፊና የሰበካ ጉባኤ አባላት ያደረጉት የቅድመ ዝግጅት ሥራ በሚገባ ተጠናቋል። ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ነገ ጶጉሜን ፪ ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም ከማለዳው አንድ ሰዓት ላይ አዲስ አበባ አየር ማረፊያ ይደርሳሉ። ከማለዳው አንድ ሰዓት ከሰላሳ ላይም በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የባህርዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ለብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የጠቅላይ ቤተክህነትና የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሥራ ኃላፊዎች ፣የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች፣ምዕመናንና ምዕመናት በተገኙበት ደማቅ አቀባበል ይደረግላቸዋል። ስለሆነም በሰዓቱ በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በሚከናወነው የአቀባበል መርሐ ግብር ላይ ኦርቶዶክሳዊያን በሙሉ እንድትገኙ ከወዲሁ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። የቅዱስነታቸው በረከትና ረድኤት ከሁላችን ጋር ይሁን። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን              ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

በሮቤ እና አካባቢዋ ወረዳ ቤተ ክህነት ስር በሚገኙ ሰ/ት/ቤቶችና የሰበካ ጉባኤ አባላት በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ትግበራ ዙሪያ ውይይት ተደረገ። እንደ ባሌ ሃገረ ስብከት አዲሱን ሥርአተ ትምርት ለመተግበር በየወረዳወች የግንዛቤ መስጫና የምክክር መርሐ ግብራት እየተዘጋጀ ይገኛል። በዛሬው እለት በሮቤ ፈለገ ብርሃን ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ስብከተ ወንጌል አዳራሽ የሃገረ ስብከቱ የሰ/ት/ቤቶት ማደራጃ መምሪያ ኃላፊ ቀሲስ ፍቃዱ፤ የሮቤ እና አካባቢዋ ወረዳ ቤተ ክህነት ጸሐፊ ቀሲስ ያሬድ እና በስርአተ ትምህርቱ ላይ ስልጠና በመውሰድ ግንዛቤ የሰጡት ዲ/ን ዮናስ በወረዳ ቤተክህቱ ስር ከሚገኙ የየአድባራት ኃላፊዎች፤ የሰበካ ጉባኤ አባላት፤ ሰ/ት/ቤቶች እና ከማኅበረ ቅዱስ አባላት ጋር ውይይት አድርገዋል። ለተሰበሰቡ አባላት  መልዕክት ያስተላለፉት የባሌ ሃገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምርያ ኃላፊ ቀሲስ ፍቃዱ አዲሱ ሥርዓተ ትምህር እየጠፋ ያለውን ትውልድ ከስር መሰረቱ በማስተማር የማዳን ስራ ነውና ሁሉም የቤተ ክርስቲያን አካላት የእራሴ ነው ብለው በጋራ መስራት አለባቸው ብለዋል። በዚህ የመጀመርያ ዙር ውይይት ላይ በአጭር ግዜ ውስጥ ከአንደኛ እስከ አራተኛ ክፍል የመማር ያመጻሕፍቶች እንዲገዙ እና በቀጣይ ለየአድባራቱ ሰበካ ጉባኤ አባላት፤ ስብከተ ወንጌል ኃላፊዎች እና ሰ/ት/ቤት አባላትና መምህራን እንዱሁም ለተማሪ ቤተሰቦች በሥርአተ ትምህርቱ ዙሪያ የግንዛቤ ማሰጨበጫ እና ስልጠና በመስጠት በ2017ዓ.ም ሥርአተ ትምርቱን ለመተግበር የሚያስፈልጉ የሰለጠኑ መምህራን ምደባ፤ የመጽሐፍ ስረጭት እና የመማርያ ቦታ በማዘጋጀት ለማስጀመር ውሳኔ ላይ ተደርሷል። በተጨማሪም አስቀድመው ሥርአተ ትምህርቱን በተመለከተ ግንዛቤ የወሰዱና ብቁ መምህራን ያሏቸው የሮቤ ደብረ ኃይል ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ሰ/ት/ቤት እና የሮቤ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን ሰ/ት/ቤት ቅድመ ሁኔታወችን በማመቻቸት በ2017ዓ.ም መስከረም 18/19 1ኛ, 4ኛ, እና 7ኛ ክፍል ትምህርት ለመጀመር በምዝገባ ላይ መሆናቸው ታውቋል። ባሌ ሮቤ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

በጅማ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ሥርዓተ ትምህርት የ2016 ዓ.ም ሁለተኛ ሴሚስተር የማጠቃለያ (ፋይናል) ፈተና በሁሉም ሰንበት ት/ቤቶች እየተሰጠ ይገኛል። የጅማ ሰንበት ት/ቤቶች አ
+7
በጅማ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ሥርዓተ ትምህርት የ2016 ዓ.ም ሁለተኛ ሴሚስተር የማጠቃለያ (ፋይናል) ፈተና በሁሉም ሰንበት ት/ቤቶች እየተሰጠ ይገኛል። የጅማ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ትምህርት ክፍል ኃላፊ መምህር ያለው ሀሪንጎ እንደገለጹት በ2016 ዓ.ም በሁለት ሴሚስተር ተከፋፍሎ ሲሰጥ የነበረው የሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት የሁለተኛ መንፈቅ ዓመት ማጠቃለያ ፈተና (2nd Semester final exam) ዛሬ ነሐሴ 25 መሰጠት የጀመረ ሲሆኑ ፈተናው በነገው ዕለትም እንደሚቀጥል ገልጸዋል። የክፍሉ ኃላፊ አክለውም እንደገለጹት በ2016 ዓ.ም በጅማ ሀገረ ስብከት በሥርዓተ ትምህርቱ መሠረት የ1ኛ ፣ የ3ኛ ፣ የ4ኛ ፣ የ5ኛ ፣ የ6ኛ እና የ7ኛ ክፍል ትምህርቶች ሲሰጡ ቆይተው ለማጠቃለያ ፈተና መብቃታቸውን አስታውቀዋል። ይህንን የሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ትግበራ በዘላቂነት ለማስቀጠል ሀገረ ስብከቱ ለሰንበት ት/ቤት አገልግሎት ተገቢውን ትኩረት በመስጠት በበጀት ጭምር ሊያግዝ እንደሚገባ የገለጹት ትምህርት ክፍሉ በዘንድሮው ዓመት የሥርዓተ ትምህርቱ ትግበራ በአንደኛ መንፈቅ ዓመት ማጠቃለያ ፈተና (1st Semester final exam) ላይ ከተደረገው የወረቀት ድጋፍ በቀር ሌላ ተጨማሪ የበጀት ድጋፍ ሊደረግ ባለመቻሉ አንድነቱ ለከፍተኛ እንግልት መዳረጉን ገልጸዋል። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

ጌታችን "እስከሞት ድረስ የታመንክ ሁን የሕይወትንም አክሊል እሰጥሃለው ።" ብሎ የተናገረው ቃል የሕይወት አክሊል የተባለች መንግሥተ ሰማያት የምትሰጠው ከሥጋ ሞት በኋላ መሆኑን ይመሠክርልናል፡፡ (ራእይ 2፥9) "የጻድቅ ሰው ሞቱ በእግዚአብሔር ዘንድ የከበረ ነው " መባሉም የጻድቅ ሰው ዕለተ ሞት የክብር አክሊል የመቀዳጀቱ ማብሠሪያ ቀን በመሆኑ ነው ፡፡ ጌታችንም "እስከ መጨረሻው (እስከ ዕለተ ሞቱ) የሚጸና እርሱ ይድናል (መንግሥተ ሰማያትን ይወርሳል)።" ማለቱ ይህን ያጠነክርልናል፡፡ (ማቴ 24፥12) ቅዱሳን የዚህን ዓለም ተጋድሎ ፈጽመው ፈተናውን አሸንፈው መከራውን አልፈው በሞተ ሥጋ ሲወሰዱ በፍጡር ሚዛን የማይለካ በፍጡር አንደበት ተዘርዝሮ የማያልቅ ከፍጡር ሕሊና በላይ የሆነ ክብርን ይቀዳጃሉ ፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞን "ጻድቃን ድል ባደረጉ ጊዜ ብዙ ክብር አለ።" ብሎ እንደተናገረ፡፡ (ምሳ 28፥12) ጠቢቡ ቅዱሳን ከሥጋ ሞታቸው በኋላ የሚጠብቃቸውን የክብር መጠን በቁጥር ሳይገድብ "ብዙ ክብር" ማለቱን ልብ ማለት ይገባል፡፡ በዚህ ዓለም ያለን ሰዎች በሕይወታችን ታላቅ ዋጋ የምንሰጣቸው ነገሮች ባለጠግነትን ምድራዊ ሹመትና ሽልማትን ስምና ዝናንና እንዲሁም ከደመና በታች የሚቀሩ ስኬቶችን ነው፡፡ ለእግዚአብሔር ቅዱሳን ግን ታላቁ ምኞታቸው ከዚህ ዓለም በሰማዕትነት ሞት አልፈው ከክርስቶስ ጋር መኖር ነው። (ፊልጵ 1፥27-29 ፤ 3፥10-13) ይህን የሚያስመኛቸውም ዕለተ ሞታቸው የድል አክሊልን የሚቀዳጁበት ቀን በመሆኑ ነው፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ተጋድሎውንም ከፈጸመ በኋላ ለደቀ መዝሙሩ ለጢሞቴዎስ "በመሥዋዕት እንደሚደረግ የእኔ ሕይወት ይሠዋልና መልካሙን ገድል ተጋድያለሁ ሃይማኖትን ጠብቄያለሁ ሩጫውን ጨርሻለሁ ለወደፊትም የጽድቅ አክሊል ተዘጋጅቶልኛል ያንም ጻድቅ ፈራጅ የሆነው ጌታ ለእኔ ያስረክበኛል ደግሞም መገለጡን ለሚወዱት ሁሉ እንጂ ለእኔ ብቻ አይደለም።" ማለቱም የዚህ ዓለም የቅዱሳን ተጋድሎ ፍጻሜ የጽድቅ አክሊል መንግሥተ ሰማያት መሆኑን ያስተምረናል። (2ጢሞ4፥6) “እግዚአብሔርን በመተማመን የሚጠባበቁ ግን ኃይላቸውን ያድሳሉ፤ እንደ ንሥር በክንፍ ይወጣሉ፤ ይሮጣሉ፥ አይታክቱም፤ ይሄዳሉ፥ አይደክሙም።” (ኢሳ 40፥31) ከጻድቁ በዓለ ዕረፍት በረከት ያሳትፈን!! ቢትወደድ ወርቁ ነሐሴ 23 ቀን 2016 ዓ ም.

+ የጻድቅ ሰው ሞቱ በእግዚአብሔር ዘንድ ክቡር ነው! + መዝ 115(116)፥6) እንኳን አደረሰን!! (ለወዳጆችዎ ቃለ እግዚአብሔር ያጋሩ) ጻድቁ ረጅሙን የዚኽ ዓለም ጉዞ በድል ያጠናቀቁበት ዋዜማ በመኾኑ ጽሑፉን አረዘምኩ። ላረዘምኩባችኹ "ይቅርታ" እየጠየቅኹ "ዘለግ" ወዳለው ጽሑፍ ልዝለቅ:- ቤተክርስቲያናችን ቅዱሳት መጻሕፍትን መሠረት በማድረግ የቅዱሳን አበውና እማትን በዓለ ዕረፍት ስብሐተ እግዚአብሔርን በማቅረብ በዓሉ የሚከበርለትን ጻድቅ ገድል በማንበብና ተጋድሎውን በማሰብ ምዕመናንም የጻድቃንን ጎዳና እንዲከተሉ በማስተማር ታከብራለች፡፡ ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት እንደተናገረውም "የጻድቅ ሰው ሞቱ በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው።" እያለች ትሰብካለች፡፡ (መዝ 115፥15) ቅዱሳን ከልደታቸውም ቀን ይልቅ ወደ ፈጣሪያቸው የሄዱበት የዕረፍታቸው ቀን እጅግ የከበረና ገናና ነው፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞን ይህን በተመለከተ ሲናገር "ከመወለድ ቀን የሞት ቀን ይሻላል።" ይላል። (መክ 7፥2) ጠቢቡ በግልጽ እንደተናገረ ቅዱሳን ሰዎች ከተወለዱበት ቀን የሞቱበት ቀን ይሻላል ይበልጣልም ፡፡ ለምን? ቢሉ የልደታቸው ቀን ወደ ተጋድሎ የገቡበት ቀን ሲሆን የሞታቸው ቀን ደግሞ ተጋድሎን የፈጸሙበትና የድል አክሊልን ለመቀበል የሚዘጋጁበት ቀን በመሆኑ ነው፡፡ ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት እንደመሠከረው የደጋግ ሰዎች ሞት በእግዚአብሔር ዘንድ እጅግ የከበረ ነው ፡፡ ክብራቸውንም በቃላት ተናግረን በብዕር (ብርዕ) ጽፈን ልንፈጽመው እንደማንችል መረዳት ይኖርብናል ፡፡ ዓለም የራሱ የሆነውን ሰዎች ዕረፍት ቀን በደመቀ ሥነ ሥርዓት ያከብራል ፡፡ እግዚአብሔርም በሕይወታቸው ሁሉ እርሱን እያመለኩ ለእርሱ እየተገዙ ፈቃዱን እየፈጸሙና የዚህ ዓለም ተጋድሏቸውም በሞተ ሥጋ የተቋጨ ወዳጆቹን ዕረፍት በማያልፍና ቃላት በማይገልጡት ክብር ያከብራል፡፡ የጻድቅ ሰው ሞቱ በእግዚአብሔር ዘንድ የከበረ ነው ለምን ተባለ? ☞ የሥጋ ሞቱ ሕያው መሆኑ የሚገለጥበት በመሆኑ በክርስትና ሃይማኖት መሠረታዊ አስተምህሮ መሠረት ሞት የሰው ልጅ የጉዞ ፍጻሜ አይደለም ፡፡ ከሞት በኋላ ዘላለማዊ ሕይወት ከመቃብር በኋላም ትንሣኤ አለና ፡፡ ሰው ከሞት በኋላ ለሚገጥመው ሕይወትና ለሚያገኘው ጸጋ ለሚወርሰው የማያልፍ ርስት የሚፈተነው በዚህ ዓለም በሚኖረው ቆይታ ነው ፡፡ ጌታችን በወንጌል "በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ ነገር ግን አይዟችሁ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ።" ሲል ቅዱስ ጳውሎስ ደግሞ "ወደ እግዚአብሔር መንግሥት በብዙ መከራ ልንገባ ያስፈልገናል።" ማለቱ ይህ ዓለም ለደጋግ ሰዎች የመከራና የኋዘን ምክንያት መሆኑን ያሳየናል፡፡ (ዮሐ 16፥33፣ የሐዋ 14 ፥22) ቅዱስ ጴጥሮስም የእምነታችንን ፍጻሜ እርሱም የነፍሳችንን መዳን (መንግሥተ ሰማያትን መውረስ) የምናገኘው በዚህ ዓለም የሚገጥመንን ፈተና፣ መከራና ኃዘን በድል ከተወጣን በኋላ መሆኑን ደጋግሞ መስክሯል። (1ጴጥ 4፥14 2ጴጥ 1፥5-9) ይህ ዓለም የተጋድሎ ዓለም መሆኑን የተረዳ ሰው ደጋግ ሰዎች ነፍሳቸው ከሥጋቸው የሚለይበት በሥጋ ሞት ከዚህ ዓለም የሚወሰዱበት ቀን ሕያዋን መሆናችው የሚታወቅበት ቀን መሆኑን ለመረዳት አይቸገርም ፡፡ በዚህ ዓለም ስንኖር የነፍስ ከእግዚአብሔር ለመለየት መንሥኤ በሆነ ኃጢአት የመያዛችን ዕድል ሰፊ ነው ፡፡ ስለሆነም በአምልኮተ እግዚአብሔር ጸንቶ በምግባር ቀንቶ ለኖረ ሰው ዕለተ ሞቱ ወደ ኃጢአት ከሚያንደረድሩ ክፉ ምኞቶች ጋር የሚያደርገው ትግል የሚያበቃበትና ጽድቅ በተባለች የእግዚአብሔር መንግሥት በሕይወት ለዘላለም እንደሚኖር የሚታወቅበት ቀን ነው፡፡ ጌታችን በወንጌል "ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳን ሕያው ነው።" ብሎ መናገሩ ይህን የሚያጸናልን ነው፡፡ (ዮሐ 11፥25) "ቢሞት እንኳን" ሲል በሥጋ ሞት ቢወሰድ እንኳ ማለቱ ግልጽ ነውና፡፡ ጌታችን በዚህ ስፍራ ብቻ ሳይሆን ደጋግሞ እርሱን አምነውና ትእዛዛቱን በመፈጸም አስደስተውት በበጎ ምግባርም ተሸልመው በሥጋ ሞት ያለፉ እንደነ አብርሃም ያሉ ደጋጎች ዳግም ሞትን እንደማያዩና ሕያዋን እንደሆኑ መስክሯል ፡፡ "እውነት እውነት እላችኋለሁ ቃሌን የሚጠብቅ ቢኖር ለዘላለም ሞትን አያይም" እንዲል። (ዮሐ 8፥51) ☞ የዚህ ዓለም ተጋድሎው የሚያበቃበት በመሆኑ ቅዱሳት መጻሕፍት እንደሚመሠክሩት እውነተኛ ክርስቲያኖች በዚህ ዓለም ከሰይጣን ክፉ ከሆነ የዓለም ምኞት ከሥጋ ፈቃድና እና ከክፉ ሀሳቦች ጋር የማያቋርጥ ተጋድሎ አለባቸው፡፡ ሐዋርያው "መጋደላችን ከደምና ከሥጋ ጋር አይደለምና ነገር ግን በዚህ ዓለም ካሉ ከክፋት መንፈሳውያን ሠራዊት ጋር ነው እንጂ።" ብሎ እንደተናገረ፡፡ (ኤፌ 6፥12-16) ተጋድሎ አንዱ እውነተኛ የክርስትና ሕይወት መገለጫ ነው ፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ለደቀ መዝሙሩ ለጢሞቴዎስ "መልካሙን የእምነት ገድል ተጋደል።" በማለት የመከረውም ምክር ይህንኑ ያስገነዝበናል ፡፡ (1ጢሞ 6፥12) ክርስቲያኖች በዚህ ዓለም ከርኩሳን መናፍስትና ከሠለጠኑባቸው ሰዎች ጋር ስለ ክርስቶስ የሚያደርጉት ተጋድሎ የክብር አክሊል የሚያገኙበት ጉዞ ነው ፡፡ በተጋድሎ ጸንቶ መኖር እንደሚገባ ሐዋርያው ሲያስተምር "ወዳጆች ሆይ ስለምንካፈለው ስለ መዳናችን ልጽፍላችሁ እጅግ ተግቼ ሳለሁ ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለተሰጠ ሃይማኖት እንድትጋደሉ እየመከርኳችሁ እጽፍላችሁ ዘንድ ግድ ሆነብኝ።" ይላል (ይሁዳ 1፥3) የክርስትና ሃይማኖት የተጋድሎ ሕይወት የሞላበት መንገድ ነው የሚባለውም ለዚሁ ነው ፡፡ ክርስቲያናዊ ሕይወትን ያለ ተጋድሎ ማሰብ ጉዞውን ሳይጀምሩ ከመንገድ መቅረትን በመሐል መደነቃቀፍንና ፈጣሪያችን ልዑል እግዚአብሔርን ወደ ማማረር ያደርሳል። (ያዕ 5፥9) ሐዋርያት በመልእክቶቻቸው "ይሁን እንጂ መጥቼ ባያችሁ ወይም ብርቅ በአንድ ልብ ስለወንጌል ሃይማኖት አብራችሁ እየተጋደላችሁ በአ ንድ መንፈስ እንድትቆሙ ስለ ኑሯችሁ እሰማ ዘንድ ለክርስቶስ ወንጌል እንደሚገባ ኑሩ ...በእኔ ያያችሁት አሁንም በእኔ እንዳለ የምትሰሙት ያው መጋደል ደርሶባችኋልና። " በማለት ያስተማሩን ትምህርት የክርስትናን መንገድ የሚከተል ሰው መከራ መንገዱ፤ መስቀል ምርኩዙ፤ እግዚአብሔር መሪው፤ ወንጌል መመሪያው፤ መንግሥተ ሰማያት ዓላማው መሆኑን ያስገነዝበናል፡፡ (ፊልጵ 1፥27-30) ቅዱሳን አባቶቻችንና እናቶቻችን የዕረፍታቸው ቀን በእግዚአብሔር ዘንድ የከበረ ነው "ከተወለዱበትም ቀን የሚሞቱበት ቀን ይሻላል" የተባለውም ከሥጋ ሞታቸውም በኋላ ዳግመኛ ወደማያለቅሱበት፣ ወደማይራቡበት፣ ወደማይጠሙበት፣ ዕንባቸውም ሁሉ ወደሚታበስበት ዓለም ስለሚጓዙ ነው፡፡ ዮሐንስ ወንጌላዊ በራእዩ የተመለከታቸው አንድስ እንኳ ሊቆጥራቸው አይችልም የተባለላቸው ነጫጭ ልብስ ለብሰው የተገለጡት እነዚያ ቅዱሳን እነማን እንደሆኑ "እነዚህ ከታላቁ መከራ የመጡ ናቸው ልብሳቸውንም አጥበው (ንስሐ ገብተው) በበጉ ደም አነጹ (በሥጋ ወደሙ ታተሙ) ስለዚህ በእግዚአብሔር ዙፋን ፊት አሉ ሌሊትና ቀንም በመቅደሱ ያመልኩታል ከእንግዲህ ወዲህ አይራቡም አይጠሙም ፀሐይም ትኩሳትም ሁሉ ከቶ አይወርድባቸውም በዙፋኑ መካከል ያለው በጉ እረኛቸው ይሆናልና ወደ ሕይወትም ውኃ ምንጭ ይመራቸዋልና እግዚአብሔር ዕንባዎችን ሁሉ ከዓይናቸው ያብሳል።" ተብሎ ተነግሮታል። (ራዕይ 7፥14-17) ☞ የድል አክሊል የሚቀዳጁበት ቀን በመሆኑ

የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት 2ሺ የሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎችን የሚኒስትሪ ፈተና መፈተኑን ገለጸ ፡፡ ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በኩል እየተተገበረ የሚገኘው አዲሱ ሥርዓተ ትምህርትን በደረጃ 2000 (ሁለት ሺ ) የአራተኛና የስምንተኛ ክፍል ተማሪዎችን መፈተኑን ገልጿል፡፡ የምሥራቀ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጽ/ቤት እንደገለጸው በልዩ ልዩ አድባራት ትምህርቱን በሚገባ ሲከታተሉ ለቆዩ ተማሪዎች የዓመቱን የማጠቃለያ ፈተና ሲሰጥ የቆየ ሲሆን ለአራተኛና ለስምንተኛ ክፍል ተማሪዎች በስድስቱ ወረዳ ቤተ ክህነቶች በትናንትናው ዕለት ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ በተመሳሳይ ሰዓት መሰጠቱን የገለጸ ሲሆን ኹሉም ባለድርሻ አካላት ለተግባራዊነቱ እስከመጨረሻ ሊተጉ እንደሚገባ አሳስቧል፡፡ በዕለቱም በቢሾፍቱ መፈተኛ ጣቢያ መጋቤ ሐዲስ ቆሞስ አባ ኃይለ ገብርኤል የሀገረ ስብከቱ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ኃላፊ ፡ መልአከ ብሥራት ቀሲስ ሲሳይ ደምሴ የቢሾፍቱና አካባቢው ዋና ሥራ አስኪያጅ ፡ መጋቤ ጥበብ መ/ር እውነቱ የወረዳ ቤተ ክህነቱ ዋና ፀሐፊ ፡ በልዩ ልዩ የመፈተኛ ጣቢያዎች ደግሞ የአድባራት አስተዳዳሪዎች ፡ የሀገረ ስብከቱ አንድነት አመራሮችና መምህራን ተገኝተዋል፡፡