cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

ALMAN ISLAMIC CHANNEL2

ALMAN ISLAMIC CHANNEL ይህ ቻናል እስላማዊም አለማዊም የሆኑ አስተምህሮቶችን ለናንተ በሚመጥን መልኩ ቁም ነገር አዘል መልክቶችን በማስተላለፍ እናንተን ተጠቃሚ ማድረግ ነው። For any comment @Muhe1bot @Mameroshan2

Mostrar más
El país no está especificadoEl idioma no está especificadoLa categoría no está especificada
Publicaciones publicitarias
136
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
Sin datos30 días

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

እሷ (ፉአድ ሙና) . ይፈሳል እንባዋ ፣ ትማፀነዋለች ሀዘን ተቀልፃ፣ "ወዴት ነው ‘ምትሄደው?" ትጠይቀዋለች ድንጋጤ ለብሳ። አይመልስም እርሱ ፣ የያዘው ይዞታል ፣ ቃል አይወጣም ከአፉ፣ "ለማን ነው ‘ምትተወን?" አታውራ ቢለው ነው ለመልስ መስነፉ። በአስፈሪ በረሀ ፣ ጡት ያልጣለን ህፃን የሚያስተው ጭካኔ፣ ታሰላስላለች ፣ ከየት አመጣ ወኔ? "አላህ ነው ያዘዘህ?" አይኖቿ ዋተቱ ምላሹን ፍለጋ፣ "አዎ" ሲል መለሰ ፣ ልቧ ተረጋጋ! "እርሱማ ከሆነ ጥሎ አይጥለንም!" ስትል ተናገረች በኢማን ተውባ፣ የአላህ እርዳታ እንደሚደርስላት በፅኑ አስባ። . ትቷቸው ሲመለስ ልቡን ሊያረጋጋ ፣ ጌታውን ለመነ እጆቹን ዘርግቶ፣ በልጁ ስቅይት ፣ በሚስቱ ተማፅኖ አንጀቱ ተበልቶ። "ጌታችን ሆይ! ከቤትህ አቅራቢያ ፣ አንተን ይገዙ ዘንድ፣ አዝመራ ከሌለው ፣ ከሸለቆው ንዳድ፣ ትዕዛዝህን ብዬ ፣ ዘሮቼን አስቀመጥኩ፣ ፍላጎቴን ገደብኩ ፣ መሻትህን ፈፀምኩ። ጌታችን ሆይ! የሰዎችህን ልብ ፣ አስናፍቅ ወደነርሱ፣ ከፍሬህ ስጣቸው ፣ ያመስግኑህ ለሱ። ጌታችን ሆይ! ድብቁን ታውቃለህ ፣ የምንሰውረውን፣ ተለየሁ ከእነርሱ ፣ ጌታዬ አደራህን!" . ከሄደ በኋላ ስንቋም ተራገፈ ፣ ውሀም ለአመል ጠፋ፣ ጥሙ ጠበሳቸው ፣ ረሀቡም ከፋ። ስትሮጥ ከጋራው ላይ ፣ ሶፋና መርዋን ስትመላለሰው፣ ቃሏን አሟላላት ፣ ቃሉን የማይጥሰው። በመልዓኩ ክንፍ ፣ ሲቆፈር አፈሩ፣ "ዙሚ ዙሚ" አሰኛት ፣ ቀናላት ነገሩ። "ጥሎ አይጥለንም!" ተወዶ እምነቷ፣ ለዓለም ፈውስ ሆነ ፣ ሀጀር ትሩፋቷ። . ተጨማሪ ግጥሞችን ለማንበብ ቻናሉን ይቀላቀሉ! 👇 @mameroshan2
Mostrar todo...
#برنامج_العيد❤️ #مع_إذاعة_ياسمين😍 تابعو......... عيدكم مبارك تقبل الله منا ومنكم صالح الأعمال🎊🎊 #ልዩ_አዝናኝ_አስተማሪ 🎊የኢድ አልአድሀ አረፋ🎊በአል ፕሮግራም #ከያስሚን_ጋር እንዳያመልጥዎ ይከታተሉ ኢድ ሙባረክ ተቀበለሏህ ሚና ወ ሚንኩም ሳሊሀል አዕማል! @M3_Yasmina
Mostrar todo...
0.31 KB
0.32 KB
#የዒድ ሰላት አሰጋገድ ከአቢሰዒድ (ረ.ዐ) እንደተዘገበው ﻛﺎﻥ ﺭﺳﻮﻝ ﺍﻟﻠﻪ - ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ - ﻳﺨﺮﺝ ﻳﻮﻡ ﺍﻟﻔﻄﺮ ﻭﺍﻷﺿﺤﻰ ﺇﻟﻰ ﺍﻟﻤﺼﻠﻰ، ﻓﺄﻭﻝ ﺷﻲﺀ ﻳﺒﺪﺃ ﺑﻪ ﺍﻟﺼﻼﺓ، ﻭﺍﻟﺘﻜﺒﻴﺮ ﺳﺒﻌًﺎ ﻓﻲ ﺍﻟﺮﻛﻌﺔ ﺍﻷﻭﻟﻰ ﻭﺧﻤﺴًﺎ ﻓﻲ ﺍﻵﺧﺮﺓ ﻭﺍﻟﻘﺮﺍﺀﺓ ﺑﻌﺪﻫﻤﺎ ﻛﻠﺘﻴﻬﻤﺎ “የአላህ መልእክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ለዒድ አልፊጥር እና ለዒድ አልአድሃ ሰላት ወደ ሜዳ ይወጡ ነበር። መጀመሪያ የሚጀምሩትም በሰላት ነው። በመጀመሪያው ረከዓ ላይ ሰባት ጊዜ በሁለተኛው ረከዓ ደግሞ አምስት ጊዜ ተክቢራ የሚያደርጉ ሲሆን ተክቢራዎቹን ከጨረሱ በኋላ ቁርዓንን ያነቡ ነበር።” ከዓኢሻ (ረ.ዐ) እንደተዘገበው “በዒድ አልፊጥር እና ዒድ አልአድሃ ሶላት ላይ በመጀመሪያው ረከዓ ላይ -ከመክፈቻው ተክቢራ ውጪ- ሰባት ጊዜ በሁለተኛው ረከዓ ላይ ደግሞ -ከሩኩዑ ተክቢራ ውጪ- አምስት ጊዜ ተክቢራ ያደርጉ ነበር።” (አቡ ዳዉድ ዘግበውታል) አንድ ሰጋጅ ኢማሙ ተክቢራ በማድረግ ላይ እያሉ ከመሃል ላይ ቢደርስ ከኢማሙ ጋር ይከተላል። ያለፉትን ተክቢራዎች ቀዷ መክፈል አይገባውም። ምክንያቱም ተክቢራዎቹ ሱና እንጂ ዋጂብ አይደሉምና። በዒድ ሰላት ላይ የሚነበቡ ሱራዎች በሙስሊምና በሌሎች ዘገባዎች ደግሞ የአላህ መልእክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) በነዚህ የዒድ ሶላቶች ሱረቱል-አዕላ (ሰቢህ) እና የ “አል- ጋሺያህ” ምእራፎችን እንደሚያነቡ ይጠቁማሉ። ውዶቼ ኢዱል ሙባረክ🤗 @mameroshan2
Mostrar todo...
اسلام عليكم ورحمة وبركاته ⏩ የተከበራችሁና ወድ የ Alman islamic channel2 ቤተሰቦች🥰 እንኳን 1441ኛው ዒደል አድሃ በሰላም አደረሳችሁ ተቀበለላሁ ሚና ወሚነኩም 🥰 አላህ ዒዱ የሰላም የፍቅር የመተዛዘን የመከባበር እና የአላህ ምህረትና እዝነት የምናገኝበት ያድርግልን አላህ ይህ የበታተነንን ወረርሽኝ አጥፍቶልን በዒድ ሜዳ እንዲሁም በአላህ ቤቶች የምንሰባሰብ ያድርገን ሁላችንም ዱዓእ ከማድረግ አንዘናጋ አላህን ለመለመን የተዘረጉ እጆች ባዶ አይመለሱም ::🥰 @mameroshan2
Mostrar todo...
ዓረፋ‐ትልቁ የአላህ ቀን ============== ነገ ጠዋት ፀሀይ ስትፈነጥቅ አላህ የፈቀደላቸውና በምርጫው ከሌሎች የለያቸው ጥቂት ሑጃጅ የአላህ ባሮች ወደ ዐረፋ ሜዳ ያመራሉ። ዋነኛውን የሐጅ ስነስርዐት አካል "ዉቁፍን" ሊፈፅሙ።… በእርግጥ የተርዊያ ቀን የሚሰኘውን የዛሬውን ቀን ሚና ውስጥ በዒባዳና በዚክር አሳልፈዋል። : የዐረፋ ቀን ታላቁ የአላህ ቀን ነው። ኃጢኣት ይሰረዝበታል። በእለቱ ዱዓ ተቀባይነት ያገኛል። ከምንም ጊዜ በበለጠ የአላህ እዝነት ለባሮቹ ቅርብ ይሆናል። : የዐረፋ ቀን ዲን የተሟላበት ቀን ነው። በሙስሊሞች ላይ የአላህ ፀጋ የተሞላበት እለት ነው። የተውበት ቀን ነው። ምህረት የሚታደልበት ቀን ነው። ለአላህ የሚዋደቁበት የዱዓ ቀን ነው። የለቅሶና የተስፋ ቀን ነው። በርካታ ትሩፋቶቹ በሐዲስ ላይ ተጠቅሰዋል። በእለቱ መፈፀም ያለባቸው ተግባራት ተጠቁመዋል: ‐ : ⚀ የአመቱ ምርጥ ቀን ጃቢር [ረዐ] እንደዘገቡት ነቢዩ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል: ‐ «ከቀናት ሁሉ በላጩ የዐረፋ ቀን ነው።» ኢብኑ ሒባን ዘግበውታል። በሌላ ሐዲስ የአላህ መልክተኛ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል: ‐ «ከዐረፋ ቀን በላይ አላህ ዘንድ በላጭ የሆነ ቀን የለም። አላህ [በእዝነቱ] ወደ ቅርቡ ሰማይ ወርዳል። በሰማይ ፍጡራን ላይም በምድር ሰዎች [ልቅና] ይፎክራል።» : ⚁ መላኢካ የሚሰበሰብበት ቀን: የዐረፋ ቀንን ክብር ለማወቅ አላህ የማለበት ቀን መሆኑ ብቻ ይበቃል። አላህ እንዲህ ይላል: ‐ [وَشَاهِدٍ وَمَشْهُودٍ] «በተጣጅና በሚጣዱበትም፤ (እምላለሁ)፡፡» ከአቡሁረይራ [ረዐ] እንደተዘገበው: ‐ ነቢዩ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል: ‐ «[ሱረቱል ቡሩጅ ላይ] 'ወልየውሚል‐መውዑድ/በተቀጠረው ቀን' የተባለው የቂያማን ቀን ነው። አልየውሙል‐መሽሁድ/የሚጣዱበት ቀን ደግሞ የዐረፋ ቀን ነው። አልየውሙሽ‐ሻሂድ/የሚጣደው ቀን ደግሞ ጁሙዐ ቀን ነው።» ቲርሚዚ ዘግበውታል። ሱረቱል‐ፈጅር ላይም በድጋሚ አላህ የማለበት ቀን ነው። አላህ እንዲህ ይላል: ‐ [وَٱلشَّفْعِ وَٱلْوَتر] «በጥንዱም በነጠላውም።» በዚህ አንቀፅ አል‐ወትር/ነጠላ የተባለው የዐረፋ ቀን ነው። ዐብዱላህ ኢብኑ ዐባስ እንዲህ ብለዋል: ‐ «ጥንድ የተባለው [ዙልሒጃ 10 ወይም] የአድሓ ቀንን ነው። ነጠላ የተባለው የዐረፋ ቀን [ዙልሒጃ 9] ነው።» : ⚂ ዲን የተሟላበት ቀን: ቡኻሪና ሙስሊም ዑመር ኢብኑል ኸጣብን [ረዐ] ዋቢ በማድረግ እንደዘገቡት «አንድ አይሁድ ዑመርን እንዲህ አላቸው: «የሙእሚኖች አሚር ሆይ! በመፅሀፋችሁ ውስጥ ያለች አንዲት አንቀፅ አለች። በእኛ በአይሁዶች ላይ ወርዳ ቢሆን የወረደችበትን ቀን ዒድ አድርገን እንይዘው ነበር።» አለ። ዑመርም «የቷ አንቀፅ?» አሉ። ተከታይዋን አንቀፅ ጠቀሰላቸው: ‐ [اليوم أَكْمَلْتُ لَكُمْ دِينَكُمْ وَأَتْمَمْتُ عَلَيْكُمْ نِعْمَتِى وَرَضِيتُ لَكُمُ ٱلْإِسْلَٰمَ دِينًا] «ዛሬ ሃይማኖታችሁን ለናንተ ሞላሁላችሁ፡፡ ጸጋዬንም በናንተ ላይ ፈጸምኩ፡፡ ለእናንተም ኢስላምን ከሃይማኖት በኩል ወደድኩ፡፡» ዑመርም [ረዐ] እንዲህ አሉ: ‐ «ይህ የወረደበትን ቀን እና በነቢዩ [ﷺ] ላይ የወረደበትን ስፍራም አውቀነዋል። በጁሙዐ ቀን የዐረፋ ሜዳ ላይ ቆመው ሳለ የወረደ ነው።» : ዲን በዚያን ቀን ተሟላ የተባለው ሙስሊሞች ከዚያ በፊት ሐጅ አድርገው ስለማያውቁ ነው። ሐጅ ሲያደርጉ ዲኑ ያኔ ተሟላ። ምክንያቱም ሐጅ የኢስላም አንዱ መዐዘን ነው። በዚያን ዓመት ከሺርክ የፀዳው በኢብራሂም መንገድ ላይ የተመሰረተው የሐጅ ስነስርዐት ከነሙሉ ክብሩ ተግባራዊ ተደርጓል። ዲኑም ሙሉ ማእዘናቱ ተሟልቷል። : ⚃ ምርጡ ዱዓ: የአላህ መልክተኛ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል:‐ «ምርጥ ዱዓ የዐረፋ ቀን ዱዓ ነው። እኔና ሌሎች ነቢያት ከተናገርነው ሁሉ ምርጡ ንግግር "ላኢላሀ ኢልለላህ ወሕደሁ ላ ሸሪከ ለሁ ለሁል ሙልክ ወለሁል ሐምድ ወሁወ ዐላ ኩልሊ ሸይኢን ቀዲር" የሚለው ቃል ነው።» ቲርሚዚ ዘግበውታል። በዐረፋ ቀን የአላህን እዝነት እና ምህረት ለማግኘት ዚክርና ዱዓ ማብዛተረ ያስፈልጋል። በተለይም «ላኢላሀ ኢልለላህ» የእለቱ ምርጥ ዚክር ነው። : ⚄ ጾም: የአላህ መልክተኛ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል: ‐ «የዐረፋ ቀን ጾም ያለፈውን እና የሚመጣውን ዓመት ኃጢኣት ያስምራል ብዬ አምናለሁ።» ሙስሊም ዘግበውታል : ⚅ የዒድ ቀን ነው: የዐረፋ ቀን የዒድ ቀን ነው። ሙስሊሞች ከሚኮሩባቸው የበዓል ቀናቶቻቸው መሀል ይመደባል። የአላህ መልክተኛ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል: ‐ «የዐረፋ ቀን፣ የአድሐ ቀን እና የተሽሪቅ ቀናት ለሙስሊሞች የዒድ ቀናችን ናቸው። የመብልና የመጠጥ ቀናት ናቸው።» ቲርሚዚ እና አቡ ዳዉድ ዘግበውታል። : ⚆ የምህረት እና ከእሳት ነፃ የሚደረግበት: የአላህ መልክተኛ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል:‐ «አላህ ሰዎችን ከእሳት ነፃ የሚያደርግበት ከዐረፋ ቀን የበለጠ ቀን የለም። አላህ [በእዝነቱ] ወደ ምድር ይቀርባል። በመላኢካዎች ላይም ይፎክራል። 'እነዚህ ባሮቼ ከእኔ ውጪ ሌላን አይፈልጉም!' ይላል።» ሙስሊም ዘግበውታል። በዚህ እለት ከእሳት ነፃ መሆንና የአላህን ምህረት ማግኘት የሚሻ ሰው በአላህ እዝነት ለመታየት የሚያበቁትን ተግባራት ይፈፅም። ከሁሉም የመጀመሪያው ስራ ደግሞ ከኃጢኣት ነፍሱን መጠበቅ ነው። ሌሎች ተግባራት ተከታዮቹ ናቸው: ① ጾም ከሐጀኛ በስተቀር ሌላው ሰው ይጾማል። የዚህ ቀን ጾም የሁለት ዓመታት ኃጢኣት ያስምራል።ተክ ② ተክቢራ ተክቢራ የእለቱ ዓርማ ነው። በተለይም ከሱብሒ ሶላት ጀምሮ ከማንኛውም ሶላት በኋላ ተክቢራ ይደረጋል። ③ ማንኛውም ዚክርና ዱዓእ ቁርኣን መቅራት፣ ሶለዋት ማድረግ፣ ተክቢራ፣ ተስቢሕ፣ ተህሊል፣ ኢስቲግፋር ማድረግ። አንዳንዴ ለብቻ ቆይቶም በጀመዐ ዱዓና ዚክር ማድረግ የእለቱ ድምቀት ነው። እለቱ ጥቂት ተሰርቶ ብዙ የሚገኝበት በመሆኑ እንጠቀምበት! ቤተሰቦቻችንን እናንቃ! የምናውቀውን ሁሉ እናነሳሳ! @mameroshan2
Mostrar todo...
የበግ ያለህ (ፉአድ ሙና) . ከዘመናት በፊት ..... ሀጀር ልጅ ወለደች፣ ኢስማኢል ተባለ፣ ኢብራሂም ወደደው፣ ከልቡ ተኳለ። በጌታው ዙፋን ላይ፣ ልጁን ቢያደላድል፣ ከአምላኩ ፍቅር፣ ለልጁ ቢያካፍል፣ ፈተና መጣበት፣ "እረደው" ተባለ፣ ታዛዥ ነው ኢብራሂም፣ ትዕዛዝ ተቀበለ። የልብ ስስቱን፣ ስለጌታው ‘ረግጦ፣ ሊያርድ አጋደመው፣ መባባቱን ውጦ። ከልቡ ወስኖ፣ ቢላውን ቢሰድድ፣ "ቃልህን ሞልተሀል፣ ልጅህን አትረድ!" የሚል ትዕዛዝ መጥቶ፣ ኢስማኢል ተረፈ፣ በህፃኑ ፋንታ፣ ከሰማይ የመጣው በጉ ተሰየፈ። . ማለትን ሰምቼ ..... እኔ ያንቺ ሚስኪን፣ ልክ እንደ ኢብራሂም፣ አይተወኝም ብዬ፣ ሀራሙ ፍቅርሽን፣ በመግፋት አረድኩት፣ መንሰፍሰፌን ችዬ። እናልሽ የኔ አለም፣ ከሄድሽ በኋላ፣ በእዝነ ህሊናዬ እንባሽን እያየሁ፣ ልክ እንደ ኢብራሂም፣ "ቃልህን ሞልተሀል፣ አትለያት!" የሚል ትዕዛዝ ጠብቄያለሁ። ግን እንደዛ አልሆነም! . ከተውኩሽ በኋላ፣ አመታት አልፈውም፣ በናፍቆትሽ ውጋት እየተሰቃየሁ፣ ከአላፊ አግዳሚው ውስጥ፣ የቷ ናት "የኔ በግ"፣ እያልኩ አስሳለሁ። ዛሬም ተስፋ ሳልቆርጥ፣ ፍቅርሽ ከሞተበት፣ ከሜዳው ቆሜያለሁ፣ ጌታዬን አምኜ፣ "በግ" ይልካል ብዬ፣ እጠብቀዋለሁ። ተስፋ አልቆርጥም ከእርሱ፣ አይዘገይም መልሱ!! እ ጠ ብ ቀ ዋ ለ ሁ !!! . @mameroshan2
Mostrar todo...
በአይነቱ ለየት ያለ ምርጥ ፕሮግራም እጅግ በጣም በቅርብ ቀን with My talented Sista #yassu❤ ከእርሶ የሚጠበቀው ከታች ያለውን ሊንክ ጠቅ in TELEGRAM CHANNEL LINK @M3_yasmina Join Sure U will Enjoy!!
Mostrar todo...
| አስደሳች ዜና ለኢትዮጵያዊያን በሙሉ ✨ | ¦ አፍሪካ አካዳሚ ¦ 📲የትም ቦታ በመሆን ፕሮግራሙን ይተከታተሉ 🤗 💡አፍሪካ አካዳሚ ከአፍሪካ ቲቪ ጋር በመተባበር ልዩ ዲናዊ የርቀት ትምህርት ስልጠና በአማርኛ ቋንቋ *"አቂዳ ኮርስ"* በሚል ርዕስ የተውሂድ ትምህርት ማዘጋጀቱን ሲያበስር በታላቅ ደስታ ነው🎉 ሁሉም ሙስሊም ማወቅ ያለበት [ *አቂዳ ኮርስ ¹* ] ከታላቁ ቁርኣን የመጨረሻዎቹ የሶስቱ ክፍሎች ማብራሪያ ኪታብ የተወሰደ በክቡር ሼኽ ሙሐመድዘይን ዘህረዲን የሚቀርብ፣ *ፕሮግራሙን ለየት የሚያደርጉ ነገሮች፡* 💸ያለ ምንም ክፍያ የነፃ ስልጠና! 📆የፕሮግራሙ ጊዜ ለ6️⃣ ቀናት ብቻ የሚቆይ ነው። *አቀራረቡ* 🧭በየቀኑ ለ1 ሰዓት የሚቀርብ ሲሆን፣ 🧾ፕሮግራሙን ካጠናቀቁ ነፃ የምስክር ወረቀት። ⏳በየቀኑ ትምህርቱን መረዳትዎን ለመገምገም ጥያቄዎች የሚቀርቡ ይሆናል። 📉🎥 ትምህርቶቹን በፈለጉት ጊዜ በቪዲዩ በድምፅ እና በፅሁፍ PDF ሊከታተሉ ይችላሉ። 🟥ሥልጠናው የሚጀመርበት ቀን፡ ዙልሂጃህ. 15 /12/1441ሂጅራ ወይም 05/08/2020 እ'ኤ'አ' ይሆናል። የአቂዳ ኮርስ መመዝገቢያ ቅፅ፡ 📎[https://forms.gle/wFZaYhqMPocXDYAA8] ከተመዘገቡ ቡኋላ ወደ አፍሪካ አካዳሚ ሥልጠና ለመግባት ይህን የቴሌግራም ሊንኩን ይጫኑ፤📍 📎https://t.me/Africa_Academy1 ⏱ጊዜዎን ተሻምተው በዚህ መሰል ፕሮግራም ይሳተፉ፣ በአላህ እገዛ ትክክለኛ አቂዳን ተረድተው ይመረቁ። 🔁ለሌሎችም እንዲደርስ የፕሮግራሙን ማስታወቂያ ሼር ያድርጉ🌹
Mostrar todo...
የፊቅሁል ዒባዳት ስልጠና #2 መመዝገብያ ቅጽ

ግብፃዊው ዶክተር መሀመድ ኤም ይባላል “የድሆች ዶክተር” እ.ኤ.አ. በ1967 ከህክምና ትምህርት ቤት ተመርቆ በ 99.3 ነጥብ የመጀመሪያ ደረጃን አሸነፈ… መሐመድ ኤም የታመሙ ድሆችን በ50 ክሊኒኮች በነፃ ያክማል በነፃ ከማከም አልፎ ተርፎም መድሃኒት ለመግዛት ገንዘብም ይሰጣቸዋል ፡፡ የመክፈል አቅም ላላቸው ህመምተኞች 10 ፓውንድ (ከአንድ ዶላር በታች) ብቻ ይቀበላል። በመቶዎች የሚቆጠሩ ህመምተኞች በየቀኑ በትህትና ያክማል ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን ሰዎች ለማከም መሐመድ ከ 9 ሰዓት እስከ 10 ሰዓት ይሠራል ፡፡ ዶክተር ሞሃመድ ኤም ምንምእንኳን 80 ዓመቱ ቢሆንም በእግሩ ነው የሚጓዝ መኪናም ሆነ የሞባይል ስልክ የለውም ስለታሪኩ የሰማ ሀብታም መኪና ገዝቶ ሸለመው ነገር ግን መኪና የሸለመው ሀብታም በአመቱ ሊዘይረው ሲመጣ መኪናዋን ሽጦ ብሩን ለደሀ በሽተኛች አከፋፍሏል መሀመድ እንዲህ ይላል እኔ የአባቴ ዱዓ ነው ዶክተር ያደረገኝ ከደሀ ገንዘብ ስለማልቀበል አልደህይም አላህ ይባርክልኛል!! አቦ አላህ ይባርክልህ!! JOIN US 👇👇👇 @mameroshan2
Mostrar todo...
Elige un Plan Diferente

Tu plan actual sólo permite el análisis de 5 canales. Para obtener más, elige otro plan.