es
Feedback
ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ

ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ 

Ir al canal en Telegram

ስለቴክኖሎጂ አዳዲስ መረጃዎች እና ሶፍትዌር የሚያገኙበት ቻናል፡፡ 🕳Professional Hack Tips and tricks 💡Cracked Softwares 🌎 ዘመኑ የቴክኖሎጂ ነው ከዘመኑ ጋር አብረው ይዘምኑ YouTube channel https://youtube.com/c/MkTechZoneETH

Mostrar mĂĄs

📈 Análisis del canal de Telegram ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ 

El canal ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ  (@computer_android_tricks) es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 11 983 suscriptores, ocupando la posición 17 269 en la categoría Educación y el puesto 2 838 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 11 983 suscriptores.

SegĂşn los Ăşltimos datos del 04 marzo, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los Ăşltimos 30 dĂ­as la variaciĂłn de miembros fue de -107, y en las Ăşltimas 24 horas de 0, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificaciĂłn: No verificado
  • Tasa de interacciĂłn (ER): El promedio de interacciĂłn de la audiencia es 0%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener N/A% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicaciĂłn recibe en promedio 0 visualizaciones. En el primer dĂ­a suele acumular 0 visualizaciones.
  • Reacciones e interacciĂłn: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicaciĂłn es 0.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
“ስለቴክኖሎጂ አዳዲስ መረጃዎች እና ሶፍትዌር የሚያገኙበት ቻናል፡፡ 🕳Professional Hack Tips and tricks 💡Cracked Softwares 🌎 ዘመኑ የቴክኖሎጂ ነው ከዘመኑ ጋር አብረው ይዘምኑ YouTube channel https://youtube.com/c/MkTechZoneETH”

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (Ăşltimos datos recibidos el 05 marzo, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analĂ­tica demuestra que la audiencia interactĂşa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categorĂ­a EducaciĂłn.

11 983
Suscriptores
Sin datos24 horas
-337 dĂ­as
-10730 dĂ­as
Archivo de publicaciones
🖍#COVID-19 - ጠቅለል ያለ መረጃ‼️ 📌በኢትዮጵያ በኮቪድ-19 ከተያዙ መካከል አንድ ሰው ሙሉ ለሙሉ መዳኑ ተገለጸ፡፡ 📌 የ101 ዓመቱ ጣሊያናዊ አዛውንት ከኮሮናቫይረስ ዳኑ፡፡ 📌 ለኮሮና
🖍#COVID-19 - ጠቅለል ያለ መረጃ‼️ 📌በኢትዮጵያ በኮቪድ-19 ከተያዙ መካከል አንድ ሰው ሙሉ ለሙሉ መዳኑ ተገለጸ፡፡ 📌 የ101 ዓመቱ ጣሊያናዊ አዛውንት ከኮሮናቫይረስ ዳኑ፡፡ 📌 ለኮሮናቫይረስ እየተዘጋጀ ያለው መድሃኒት ወደ ቀጣይ ፍተሻ ማለፉ ተነገረ፡፡ 📌 በኬንያ በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች ቁጥር 38 ደረሰ፡፡ 📌 በደቡብ ኮሪያ በኮቪድ-19 የተያዙ በርካታ ሰዎች ከበሽታው ዳኑ፡፡ 📌 የአፍሪካ ኅብረት ዋና ጸሐፊ ከኮሮናቫይረስ ነጻ መሆናቸው ተረጋገጠ፡፡ 📌 በአዲስ አበባ 41 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን መንገድ በጸረ ተዋህሲያን መድሃኒት ሊረጭ ነው፡፡ 📌 የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር በምዕራብ ኦሮሚያ ያለው የኢንተርኔት መቋረጥ እንዲቆም ጠየቀ፡፡ 📌 የኮሮናቫይረስ መነሻ የሆነችው የቻይና ከተማ በከፊል ለእንቅስቃሴ ክፍት ሆነች፡፡ 📌 የጋናው ፕሬዝዳንት ደሞዛቸውን በኮቪድ-19 ለተያዙ ድሆች ለመስጠት ቃል ገቡ፡፡ 📌 ዚምባብዌ ከሰኞ ጀምሮ እንቅስቃሴ ልትገድብ ነው፡፡ 📌 ሩሲያ የሰዎችን እንቅስቃሴ ማገድ ልትጀምር ነው፡፡ 📌 ቱኒዚያውያን ሕክምና ባለሙያዎቻቸውን ለመታደግ በፋብሪካ ውስጥ ራሳቸውን ለይተዋል፡፡ 📌 ሶማሊያ ከኮሮናቫይረስ ጋር በተያያዘ ለጫት ታወጣው የነበረን 3 ሚሊዮን ዶላር አዳነች፡፡ 📌 በስፔን በኮቪድ-19 የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከ5 ሺህ አለፈ፡፡ ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━ ☞ሼር በማድረግ ሃላፊነቶን ይወጡ!!!

#ኮሮና_ቫይረስ😭😭 የመተንፈሻ ማሽን እጥረት ስለኢትዮጵያ ኮሮና ቫይረስን አስመልክቶ ሳስብ በጣም ያስጨንቀኛል።በሽታው የመተንፈሻ አካልን (ሳንባን) የሚያጠቃ በመሆኑ ተጠቂዎች በሽታውን የመከላከል አቅማቸው ደካማ ከሆነ የመተንፈስ ችግር ይገጥማቸዋል። ታዲያ በዚህ ጊዜ የመተንፋሻ ስርዓታቸውን ሙሉ በሙሉ ተክቶ የሚሰራ ሰው ሰራሽ መሳሪያ ወይም mehanical ventilator የሚባል ማሽን መጠቀም ግዴታ ይሆንባቸዋል ማለት ነው ።አሁን ችግሩ የሚመጣው የዚህ ማሽን እጥረት መኖሩ ነዉ። እዚህ አሜሪካ ከባድ የኮሮና ቫይረስ ጥቃት የደረሰባት የኒዮርክ ከተማ ከንቲባ ለፌዴራል መንግስቱ 30,000 mechanical ventilators ቢጠይቅም መንግሥት ማቅረብ የቻለው 4,000 ብቻ ነው ። የፍላጎትና የአቅርቦት (demand and supply) አለመመጣጠኑን ከዚህ መገንዘብ ይቻላል። ይህ እንግዲህ ወደ 19 ሚሊዮን ለሚጠጋ የኒዮርክ ህዝብ ነው። ታዲያ የኢትዮጵያ ሁኔታ እጅጉን የሚያሳዝን ነው ይኸውም ለመቶ አስር ሚሊዮን ህዝብ አጠቃላይ በአገር አቀፍ ደረጃ ያሉን mechanical ventilators ብዛት ከ200 አይበልጥም መባሉን ከጤና ባለሙያዎች ስሰማ ስጋቴን እጥፍ ድርብ አደረገብኝ። ኢትዮጵያዬ ፈጣሪ በምህረት ዓይኑ ይይሽ፣ ከዚህ ፈተና ምስኪን አማኝ ህዝብሽን ፈጣሪ ይጠብቅልሽ። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━ ☞ሼር በማድረግ ሃላፊነቶን ይወጡ!!!

ጥሎብን ነው መሰል ነጭ የሰራውን ወይም እሞክራለው ያለውን ምንም ነገር ቀድመን ማድነቅና ማምለክ እንወዳለን:: የራሳችን ሰው እየሞከርኩኝ ነው እየሰራው ነው ተስፋ አለው የሚለውን ከመደገፍና በርታ እ
ጥሎብን ነው መሰል ነጭ የሰራውን ወይም እሞክራለው ያለውን ምንም ነገር ቀድመን ማድነቅና ማምለክ እንወዳለን:: የራሳችን ሰው እየሞከርኩኝ ነው እየሰራው ነው ተስፋ አለው የሚለውን ከመደገፍና በርታ እስኪ ሞክር ከማለት ይልቅ ነጭ ያልሰራውን ያልሞከረውን አለም ያቃተውን ማለት የራሳችንን ሰው ማንቋሸሽና ማጣጣል ይቀናናል ይሄ እራሱ የቻለ አንድ መድሀኒት የሚያስፈልገው በሽታ ነው:: የማያልፍልንም እንዲህ እርስ በእርስ ስለምንጠላለፍ ነው! በርቱ ጥሩ ነው ምን ላግዝ ማንን ገደለ?? በመድሀኒቱ ዙሪያ የተለያየ ሙከራ እያደረጋችሁ የምትገኙ የሀገሬ ልጆች ኢትዮጵያዊያን ተመራማሪዎች በርቱ ጥረትችሁን ቀጥሉ ! ፕ/ር አክሊሉ ለማ በ1928 ዓ.ም. በጅጅጋ ከተማ ተወለዱ። የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ካገኙ በኋላ በአሜሪካ አገር ከሚገኘው ጆን ሆብኪንስ ዩኒቨርሲቲ የዶክትሬት ዲግሪያቸውን ተቀብለዋል። አክሊሉ ለስራ ጉብኝት ወደ ሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል በሚዘዋወሩ ጊዜ ሰዎች በዕንዶድ የሚያጥቡበት አካባቢ ብዙ ቀንዳውጣዎች ሞተው በማየታቸው እንደመነሻ ሃሳብ በመውሰድ ከዶ/ር ለገሠ ወልደዮሐንስ ጋር በመተባበር ብልሃርዚያ ለተባለው በሽታ አምጪ ለሆነው የቀንድ ዓውጣ ለሰላሳ ዓመታት ተመራምረው "እንዶድ 44" የተባለ ማጥፊያ መድሀኒት አግኝተዋል። ለዚህም ውጤታቸው "Right Livelihood Award" ሽልማት እና የአሜሪካ የፈተራ ውጤት ባለቤትነት መረጋገጫ አግኝተዋል። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━ ☞ሼር በማድረግ ሃላፊነቶን ይወጡ!!!

#AFRICA በአፍሪካ 46 ሀገራት የኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] ተጠቂዎች ቁጥር 3,778 ደርሷል። 109 ሰዎች በቫይረሱ ሞተዋል። በተጠቂዎች ቁጥር ደቡብ አፍሪካ የቀዳሚውን ስፍራ ይዛለች በሀገሯ 1
#AFRICA በአፍሪካ 46 ሀገራት የኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] ተጠቂዎች ቁጥር 3,778 ደርሷል። 109 ሰዎች በቫይረሱ ሞተዋል። በተጠቂዎች ቁጥር ደቡብ አፍሪካ የቀዳሚውን ስፍራ ይዛለች በሀገሯ 1,170 ደርሷል። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━ ☞ሼር በማድረግ ሃላፊነቶን ይወጡ!!!

#በመላው_ዓለም በመላው ዓለም የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች ቁጥር 607,239 ደርሷል። 27,674 ሰዎች በቫይረሱ እንደሞቱ የተመዘገበ ሲሆን 134,288 ሰዎች ደግሞ አገግመው ከሆስፒታል ወጥተዋል። ከፍ
#በመላው_ዓለም በመላው ዓለም የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች ቁጥር 607,239 ደርሷል። 27,674 ሰዎች በቫይረሱ እንደሞቱ የተመዘገበ ሲሆን 134,288 ሰዎች ደግሞ አገግመው ከሆስፒታል ወጥተዋል። ከፍተኛ የተጠቂ እና ሟቾች የተመዘገበባቸው፦ • አሜሪካ - 104,256 ተጠቂዎች - 1,704 ሟቾች • ጣልያን -86,498 ተጠቂዎች፣ - 9,134 ሟቾች • ቻይና - 81,394 ተጠቂዎች ፣ - 3,295 ሟቾች • ስፔን - 65,719 ተጠቂዎች - 5,138 ሟቾች ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━ ☞ሼር በማድረግ ሃላፊነቶን ይወጡ!!!

#በስፔን ተጨማሪ 832 ሰዎች ሞቱ! ስፔን በ24 ሰዓት ውስጥ በኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] 832 ሰዎች መሞታቸውን ሪፖርት አድርጋለች። አጠቃላይ የሟቾች ቁጥርም 5,690 ደርሷል። በተጨማሪ በ24 ሰ
#በስፔን ተጨማሪ 832 ሰዎች ሞቱ! ስፔን በ24 ሰዓት ውስጥ በኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] 832 ሰዎች መሞታቸውን ሪፖርት አድርጋለች። አጠቃላይ የሟቾች ቁጥርም 5,690 ደርሷል። በተጨማሪ በ24 ሰዓት 6,529 ሰዎች በቫይረሱ መጠቃታቸውን ተከትሎ 72,248 ደርሰዋል። ምንጭ፦ የስፔን ጤና ሚኒስቴር ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━ ☞ሼር በማድረግ ሃላፊነቶን ይወጡ!!!

#COVID19 የተባበሩት መንግሥታት 'የሰብዓዊ መብቶች' ከፍተኛ ኮሚሽነር በምዕራብ ኦሮሚያ ያለው የኢንተርኔት መቋረጥ እንደሚያሳስበው ገለፀ። ለረዥም ጊዜ ኢንተርኔትና ስልክ ማቋረጥ በተለይ ደግሞ እ
#COVID19 የተባበሩት መንግሥታት 'የሰብዓዊ መብቶች' ከፍተኛ ኮሚሽነር በምዕራብ ኦሮሚያ ያለው የኢንተርኔት መቋረጥ እንደሚያሳስበው ገለፀ። ለረዥም ጊዜ ኢንተርኔትና ስልክ ማቋረጥ በተለይ ደግሞ እንደ ኮቪድ-19 ያለ ወረርሽኝ ባለበት ሰዓት ስለበሽታው የሚሰጡ መረጃዎችን ዜጎች እንዳያገኙ ያደርጋል በማለት ባለስልጣናት እንዲሁም የሕክምና ባለሙያዎች ትክክለኛ መረጃዎችን ለመስጠት እንዲችሉ አገልግሎቶቹ ክፍት እንዲሆኑ ጠይቋል። ኮሚሽኑ በድረገፁ ላይ ባወጣው መግለጫ እንዳለው ኢትዮጵያ ከታህሳስ 28/2012 ዓ/ም አንስቶ በምዕራብ ኦሮሚያ ከተሞች ከደህንነት እና ፀጥታ ጋር በተገናኘ የኢንተርኔትና የስልክ አገልግሎት መቋረጡን በመግለጽ፤ ይህም በአካባቢው የሚኖሩ ዜጎች መረጃ እንዳያገኙ፣ እንዲሁም ከወዳጅ ዘመዶቻቸው ጋር እንዳይገናኙ ማድረጉን ገልጿል። መግለጫው ኢንተርኔት የምታቋርጠው ኢትዮጵያ ብቻ አለመሆኗን በመጥቀስ ሁሉም አገራት በፍጥነት ኢንተርኔትና ስልክ ማቋረጣቸውን እንዲያቆሙ ጥሪ አቅርቧል። ምንጭ፦ ቢቢሲ ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━ ☞ሼር በማድረግ ሃላፊነቶን ይወጡ!!!

የመጀመሪያዋ በኮቪድ-19 የተያዘችው #ድመት! ይህ የSkyNews ዘገባ በዓለማችን የመጀመሪያዋ የኮሮና ቫይረስ ተጠቂ 'ድመት' ቤልጂየም ውስጥ እንደተገኘች ይገልፃል። ድመቷ በኮሮና ቫይረስ የተለከፈችው በባለቤቷ እንደሆነም ነው የሚያስረዳው። Rest in home🏠 or rest in peace⚰ ምርጫው የራሳችን ነው!! ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

#ግርታ የፈጠረው የኮሮና ማከሚያ መድሀኒት በኢትዮጵያ የሀገር በቀል እውቀትን ከዘመናዊ ሳይንስ ጋር በማቀናጀት የኮሮና ቫይረስን ለማከም የሚያስችል መድሀኒት በምርምር ላይ እንደሚገኝ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ቬሪፋይድ ባልሆነ የፌስቡክ ገጹ ማስታወቁ ይታወቃል። ከትላት ጀምሮ ሲናፈስ የነበረውና በሃገር ውስጥና ከሃገር ውጪ ከሚገኙ የተለያዩ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ጋር በመሆን እየካሄደ ነው የተባለው የኮሮና ማከሚያ መድሀብት ብዙዎችን ግር አሰኝቷል ። ይህንን ተከትሎ ሚንስትር መ/ቤቱ በጉዳዩ ላይ ተከታዩን መግልጫ ሰጥቷል ከላይ 👆🏾 ያለው ቪድዮ ላይ መግለጫውን ይመልከቱ። ሚኒስትር መስሪያ ቤቱ ሌሎች ተጨማሪ የምርምር ሂደት መረጃዎችን በተመለከተ በቀጣይ እንደሚያስታውቅም ገልጿል። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

ስለ #ኮቪድ-19 (COVID-19) ቫይረስ ወቅታዊ መረጃ ▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃ ከቅድስት ማርያም ዩኒቨርስቲ የኮሮና ቫይረስ መከላከል ግብረ ሀይል ከጆን ሆፕኪንስ ዩኒቨርስቲ (John Hopkins University) የተገኘ መረጃን በመጠቀም ስለ ኮቪድ-19 (COVID-19) ቫይረስ ወቅታዊ መረጃ --------- ❶. ቫይረሱ ሕይወት የሌለውና በስብ(Fat) የተሸፈነ ነው፡፡ ❷. በአይን፣ በአፍንጫ ወይም ወደ አፍ ሴሎች ሲገባ ባሕርያቸውን በመቀየር የማይፈለጉና አጥፊ ሴሎችን ያራባል፡፡ ❸. ቫይረሱ ሕይወት ያለው ባለመሆኑና የፕሮቲን ሞሊኪዩል በመሆኑ የሚሞት ሳይሆን በራሱ ጊዜ የሚሟሽሽ ነው፡፡ ❖ የሚጠፋበትም ጊዜ የሚወሰነው በአካባቢው ባለው የሙቀትና የአየሩ እርጥበት መጠን እንዲሁም ቫይረሱ ባረፈበት ቁስ ዓይነት ነው፡፡ ❹. ቫይረሱ የውጫዊ አካሉ የተሸፈነበት ስብ ባይኖር ኖሮ በቀላሉ የሚፈረካከስ ነው። ለዚህም ነው ሳሙናና ሳሙና ነክ የሆኑ ማጽጃዎች ሁነኛ የመከላከያ ዘዴ ናቸው የሚባለው፡፡ ❖ምክንያቱም በሳሙና በሚጸዳበት ጊዜ የሚፈጠረው አረፋ የቫይረሱን ስብ ስለሚያጠፋው ነው፡፡ እጅን ሲታጠቡ ለ20 ሴኮንዶች መቆየት አለበት የሚባለውም ብዙ አረፋን መፍጠር ስለሚያስችል ነው፡፡ አረፋው የቫይረሱ ሽፋን የሆነውን ስብ ስለሚያሟሟው ፕሮቲን ሞሊኪዩሉ ተበታትኖ ይፈረካከሳል፡፡ ❺. ሙቀት ስብን ያቀልጣል፣ በመሆኑም ሲታጠቡ ከ25ዐc በላይ የሞቀ ውሃ ቢጠቀሙ፣ ልብሶችም ሆነ ሌሎች ቁሶችን ሲያጥቡ በዚህ የሙቀት ደረጃ ቢሆን በቀላሉ አረፋ የሚያወጣ በመሆኑ የበለጠ የቫይረሱን ስብ የማቅለጥ ኃይል ይኖረዋል፡፡ ❻. አልኮል ወይም ቢያንስ 65% የሆነ የአልኮል ድብልቅ የቫይረሱን ስብ ያቀልጣል፡፡ ❼. ቫይረሱን ምንም ዓይነት ፀረ ባክቴሪያ የሆኑ መድሐኒት አያጠፋውም፤ ምክንያቱም እንደ ባክቴሪያ ሕይወት ያለው ባለመሆኑ፡፡ ❽. ቫይረሱ ግዑዝ በመሆኑ ከሰው አካል ውጭ ሲገኝ የመፈረካከሻ ጊዜው እንዳረፈበት ቁስ ዓይነት ይወሰናል፡፡ ጨርቅነት ባላቸው ቁሶች ለ3 ሰዓታት፣ በመዳብና በእንጨት ላይ ለ4 ሰዓታት፣ በካርቶን ላይ ለ24 ሰዓታት፣ ብረት ነክ በሆኑ ዕቃዎች ለ42 ሰዓታት እንዲሁም በፕላስቲክ ላይ ለ72 ሰዓታት የመቆየት ባሕርይ አለው፡፡ ❖ለዚህም ነው ጨርቅነት ያላቸውን ቁሶች ማራገፍ ተገቢ የማይሆነው፣ ምክንያቱም ከ3 ሰዓታት ባነሰ ጊዜ በራሱ የሚጠፋው ቫይረስ ጨርቁ ሲራገፍ በዓየር ላይ በመሆን ወደ አፍንጫ የመግባት አጋጣሚ ያገኛልና ነው፡፡ Rest in home🏠 or rest in peace⚰ ምርጫው የራሳችን ነው!! ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

#Coronavirus የቡድን 20 ሀገራት የአለም ኢኮኖሚን ለመታደግ የሚውል 5 #ትሪሊዮን ዶላር ቃል ገቡ። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

"ቻይናን እናከብራታለን!" - ዶናልድ ትራምፕ #Coronavirus የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው ፕሬዘዳንት ሺ ጂፒንግ ጋር በጣም ጥሩ ንግግር አድርገናል ብለዋል። 'ከፕሬዘዳ
"ቻይናን እናከብራታለን!" - ዶናልድ ትራምፕ #Coronavirus የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው ፕሬዘዳንት ሺ ጂፒንግ ጋር በጣም ጥሩ ንግግር አድርገናል ብለዋል። 'ከፕሬዘዳንት ሺ ጂፒንግ ጋር ብዛት ያለውን የዓለማችንን አካባቢ እያዳረሰ ሳላለው ስለኮሮና ቫይረስ በደንብ አድርገን በዝርዝር ተወያይተናል' ያሉት ዶናልድ ትራምፕ፤ 'ቻይና በወረርሽኙ ብዙ አሳልፋለችና ቫይረሱን በሚገባ ጠንቅቃ ተረድታዋለች፤ አሁን አብረን በቅርበት እየሰራን ነን፣ እናከብራታለን' ሲሉ ተደምጠዋል። ባለፉት ገለፃዎቻቸው ግን ፕሬዝዳንት ትራምፕ ለቻይና ያን ያህል አክብሮት አልነበራቸውም። የወረርሽኙን አያያዟን ሲያንቋሽሹ ቫይረሱንም 'የቻይናው ቫይረስ' ብለው ሲጠሩ ነበር። በዩናይት ስቴትስ በከባዱ በተጠቃችው ኒውዮርክ የኮሮና ቫይረስ ተጠቂ ከ45,000 አልፏል። በየቀኑ የተያዦቹ ቁጥር ቢያንስ በ3,000 ገደማ እየጨመረ መሆኑን ነው ባለስልጣናት የሚገልፁት። ምንጭ፦ የአሜሪካ ድምፅ ሬድዮ ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

#በጣልያን ተጨማሪ 919 ሰዎች ሞቱ! ጣልያን ውስጥ በ24 ሰዓት ተጨማሪ 919 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] ሞተዋል። አጠቃላይ የሟቾች ቁጥርም 9,134 ደርሷል። በሀገሪቱ በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎች ቁጥርም 86,498 የደረሱ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ 5,909 ኬዝ በ24 ሰዓት ነው የተመዘገበው። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

#የእንግሊዙ የጤና ኃላፊ በኮሮና ቫይረስ ተይዘዋል! የእንግሊዝ የጤና ኃላፊ የሆኑት ማት ሀንኮክ በኮኖና ቫይረስ መጠቃታቸውና እራሳቸውን ለይተው መቀመጣቸውን በይፋዊ የትዊተር ገፃቸው አሳውቀዋል። Re
#የእንግሊዙ የጤና ኃላፊ በኮሮና ቫይረስ ተይዘዋል! የእንግሊዝ የጤና ኃላፊ የሆኑት ማት ሀንኮክ በኮኖና ቫይረስ መጠቃታቸውና እራሳቸውን ለይተው መቀመጣቸውን በይፋዊ የትዊተር ገፃቸው አሳውቀዋል። Rest in home🏠 or rest in peace⚰ ምርጫው የራሳችን ነው!! ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━━

🖍ኢትዮጵያ የባህል መድሀኒት አግኝታለች‼️ ለኮሮና ተዋህሲ ባህላዊ መድሃኒት ኢትዮጵያ አግኝታለች በማለት የሳይንስና የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በፌስ ቡክ ገፁ አሳወቋል ። ምርምሩ የኮሮና ቫይረ
🖍ኢትዮጵያ የባህል መድሀኒት አግኝታለች‼️ ለኮሮና ተዋህሲ ባህላዊ መድሃኒት ኢትዮጵያ አግኝታለች በማለት የሳይንስና የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በፌስ ቡክ ገፁ አሳወቋል ። ምርምሩ የኮሮና ቫይረስ በዓለም ላይ መከሰቱ ከተሰማ ጊዜ ጀምሮ ከተለያዩ በሃገር ውስጥና ከሃገር ውጪ ከሚገኙ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ጋር በመሆን ሲካሄድ የቆየ ሲሆን ተደጋጋሚ የምርመር ሂደት አልፎ ወደ ምርት እና ቀጣይ የእንስሳት ፍተሻ እና ክሊኒካል ፍተሻ ስራዎች እንዲሸጋገር ተደርጓል። መድሃኒቱ የመከላከል አቅም የሚጨምር፣ መርዛማነት የሌለው እና አዋጭነቱ የተረጋገጠ ነው፡፡ የምርምር ሂደቱ ተጠናቅቆ ወደ ምርት ለመግባት ዝግጅት እየተደረገ ሲሆን ዝርዝር መረጃዎችን በተመለከተ ዛሬ መግለጫ ይሰጣል፡፡ VIA ተስፋዬ ጌትነት ፣ MIT-Ethiopia ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

🖍አስርቱ ˝የመ˝ ሕጎች - ለኮሮና‼️ 👉መታጠብ (በሳሙና / በሳኒታይዘር ) 👉መጉመጥመጥ (ውሀ ለብ አርገህ በትንሽ ጨው) 👉መጥረግ (በአልኮል ) 👉መራራቅ (ስትቆሙ/ስትቀመጡ ) 👉መታቀብ (
🖍አስርቱ ˝የመ˝ ሕጎች - ለኮሮና‼️ 👉መታጠብ (በሳሙና / በሳኒታይዘር ) 👉መጉመጥመጥ (ውሀ ለብ አርገህ በትንሽ ጨው) 👉መጥረግ (በአልኮል ) 👉መራራቅ (ስትቆሙ/ስትቀመጡ ) 👉መታቀብ (ከመጨባበጥ /ከንክኪ ) 👉መተው (ስብሰባ/ህዝብ የሚበዛበት ቦታ 👉መቀመጥ (ቤትህ /ሆቴል ውስጥ ) 👉መመገብ (በሽታ ለመቋቋም ) 👉መከታተል (መረጃን ከታማኝ ምንጭ ) 👉መፀለይ (ወደ ፈጣሪ ) ✅VIA የዶክተር አለ 8809 #SHARE ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

#BREAKING #ሙሳ ፋኪ መሀማት ራሳቸውን ለይቶ ማቆያ አስገቡ! የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ መሀማት ራሳቸውን ለይቶ ማቆያ ማስገባታቸውን በትዊተር ገጻቸው ገልፀዋል። ሊቀመንበሩ ራ
#BREAKING #ሙሳ ፋኪ መሀማት ራሳቸውን ለይቶ ማቆያ አስገቡ! የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ መሀማት ራሳቸውን ለይቶ ማቆያ ማስገባታቸውን በትዊተር ገጻቸው ገልፀዋል። ሊቀመንበሩ ራሳቸውን 'ለይተው ለማቆየት' የወሰኑት አንድ የኮሚሽኑ ሰራተኛ በቫይረሱ መያዛቸው መረጋገጡን ተከትሎ ነው፡፡ ሌሎች ባልደረቦቻቸውም ራሳቸውን እንደለዩ ገልጸዋል፡፡ ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━