cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

የያሲኔ ወዳጅ 🇪🇹PAGE🇪🇹

እኔ የያሲኔ ወዳጅ ለኢስላም ማድረግ ከሚገባኝ የገዘፈ ግዴታ ቅንጣት በመፍጨርጨር ላይ ነኝ ዓላማችን ያውቀነውን ማሳወቅ ነው 🍀 Comment ☞ @Nemira_1 ለአስተያየት መስጫ @Nemira_1 በሀሳብ ለመደገፍ 👉 @Nemira_1 ወይም☞ @NemiraBot

Mostrar más
El país no está especificadoEl idioma no está especificadoLa categoría no está especificada
Publicaciones publicitarias
15 214
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
Sin datos30 días
Archivo de publicaciones
በጎንደር አክራሪ ፋኖ በግፍ የተገደለው ወንድማችን አንገቱን ደፍቶ የኖረ፣ ትንሽ ትልቁን ያከበረ፣ አንደበቱ ፈፅሞ ክፉ ያልተናገረ የአላህ ሠው ነበር። አስተዳደጉ፣ አስተሳሰቡ፣ አኗኗሩ፣ በሀይማኖትና በጎሳ ዘረኛ ያላደረገው - ጻዲቅ። Ahmed Maru በክፉ አይታማም። ታታሪ፣ ከሁሉም ጋር ተግባቢ፣ ድሀን ቀላቢ ነው። ሠርቶ አደር ነው። ለጋሥ ነው። ቸር ነው። ሠው ነው። የማክሰኞ ዕለት ጭለማ እርሱንም በላው። ደጉን ሠው ቀጠፈው። አላህ ይቀበልህ ወንድሜ፣ ኢናሊላህ ወኢና ኢለይሂ ራጅዑን! #የጎንደርጭፍጨፋ #GondarMassacre #ሙስሊምጠልነት #ፋኖ #ማኅበረቅዱሳን #የአማራብሄርተኝነት #Gonder #ጎንደር
Mostrar todo...
አሳዛኝ ዜና ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጅኡን ታላቁ ዋርካ ፣ የኢልሙ ገበሬ ፣ ሃፊዘል ቁርዓኑ ፣ የልማት አርበኛው ፣ የመድረኩ ፈርጥ ፣ የበጎ ስራዎች አምባሳደር የነበረው ኢማም ሙሳ ያሲን ወደ ማይቀርበ ቤቱ ተሸጋግሯል። ሁላችንም ዱኣ እናድርግለት። እንደሚታወቀው በአለም አቀፍ ደረጃ በሚባል መልኩ ውጭ ሀገር ሄዶ መታከም እንዲችል ለህክምናው ወጪ ይሆን ዘንድ ገንዘብ እየተሰበሰበ የነበረ ሲሆን በዛሬው እለት 3.4 ሚሊዮን መድረሱ ይታወቃል። ቀጣይ ሂደቱን ኮሚቴው ተወያይቶ ለሚዲያ እስኪያሳውቅ ድረስ ሁላችሁም ለታላቁ ሰው ዱዓ ታደርጉለት ዘንድ በአለህ ስም ተጠይቃችዋል። አላህ ጀነተል ፍርደውስ ይወፍቅህ በጀነተም ከታላላቆች ጎን እንዲያደርግህ የዘውትር ዱኣችን ነው ።
Mostrar todo...
አላሁ አክበር ሼር ሼር ሀጂ ሰኢድ ያሲን ለማን ይተካው ፕሮጀክት 10ሚሊዮን ለመስጠት ቃል ገቡ አላሁ አክበር ወቅታዊ መረጃ እንዲደርሶ የቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉ https://t.me/joinchat/AAAAAEOPTe77tGqV25jc9w የዩቲውብ አድራሻችን Subscribe ይበሉ https://www.youtube.com/channel/UCTqmDhnSdDAfJ9eNyrqzHsA
Mostrar todo...
መዛሚር ሊቃ #1 (እንዳንቱ #2) "የላቀ መወሳት" በሚል መሪ ቃል ጥር 22 እሁድ ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ በአምባሳደር ሲኒማ በአላህ ፍቃድ ይካሄዳል ትኬት በሞባይል ባንኪንግ 📌 1000238309658 (CBE) ወደዚህ የንግድ ባንክ አካውንት ክፍያ ይፈፅሙ 📌 0944289444 ስክሪን ሾት (screenshot) በቴሌግራም ይላኩልን 1 ትኬት 200 ብር በዕለቱ የሞባይል ባንኪንግ ደንበኞችን ብቻ የሚያስተናግዱ ኻዲሞች ይኖራሉ ለበለጠ መረጃ 0944289444 #ሊቃ #መዛሚርሊቃ #Liqa #mezamirliqa
Mostrar todo...
አስደሳች ዜና ላይክክ ጀግናው ዛኪር ናይክ ወደ ቀድሞ ንፅፅር ስራ ተመልሷል አልሃምዱሊለህ እንኳን ደስ አለን ጀግናው ወደ ሚምበሩ ተመልሰዋል! ለአመታት በእገዳ ምክኒያት ሰፊው ህዝብ የሚታደምበትን የንፅፅር ስራዎች እንዳይሰሩ ተከልክለው የነበሩት ዶ/ር ዛኪር ናይክ ለሰፊው ህዝብ ይፋ በሚሆኑበት የውይይትና የንፅፅር ፕሮግራማቸው ተመልሰዋል። Ibra ta ሼር ላይክ #ZakirNaik #ዶክተርዛኪርናይክ ወቅታዊ መረጃ እንዲደርሶ የቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉ https://t.me/joinchat/AAAAAEOPTe77tGqV25jc9w የዩቲውብ አድራሻችን Subscribe ይበሉ https://www.youtube.com/channel/UCTqmDhnSdDAfJ9eNyrqzHsA
Mostrar todo...
ያሳዛናል አላህዬ ድረስ የሸዋሪቤቷ ታዳጊ ኢክራም ለ7መደፈሯን በዛሬው እለት ሶይፉ ሾ ላይ ገለፀች ያሳዝናል በጣም ሁላችንም ተረባርበን እህታችንን አለንልሽ ልናላት ይገባል በተለይ የስነልቦና ባለሞያዎች ከጎና ልትሆኑ ይገባል አብሽሪ እህቴ ሁሉም የአላህ ውሳኔ ነው #EBSEkram ወቅታዊ መረጃ እንዲደርሶ የቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉ https://t.me/joinchat/AAAAAEOPTe77tGqV25jc9w የዩቲውብ አድራሻችን Subscribe ይበሉ https://www.youtube.com/channel/UCTqmDhnSdDAfJ9eNyrqzHsA
Mostrar todo...
"ይሄን ጉዳይ በግልፅ አውግዞ ተገቢውን አስተማሪ ቅጣት እንዲያገኝ ከማድረግ ይልቅ የመሸፋፈን፣ ለግለሰቡ መከላከል መሞከር ወይም ይከፋፍለናል የሚለው ሀሳብ ተቀባይነት የለውም" ኡስታዝ #አህመዲን_ጀበል ወቅታዊ መረጃ እንዲደርሶ የቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉ https://t.me/joinchat/AAAAAEOPTe77tGqV25jc9w የዩቲውብ አድራሻችን Subscribe ይበሉ https://www.youtube.com/channel/UCTqmDhnSdDAfJ9eNyrqzHsA
Mostrar todo...
"ይሄን ጉዳይ በግልፅ አውግዞ ተገቢውን አስተማሪ ቅጣት እንዲያገኝ ከማድረግ ይልቅ የመሸፋፈን፣ ለግለሰቡ መከላከል መሞከር ወይም ይከፋፍለናል የሚለው ሀሳብ ተቀባይነት የለውም" ኡስታዝ #አህመዲን_ጀበል ወቅታዊ መረጃ እንዲደርሶ የቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉ https://t.me/joinchat/AAAAAEOPTe77tGqV25jc9w የዩቲውብ አድራሻችን Subscribe ይበሉ https://www.youtube.com/channel/UCTqmDhnSdDAfJ9eNyrqzHsA
Mostrar todo...
በመዲናችን አዲስ አበባ የተደረገ የጭካኔ ጥግ የፍትህ ያለህ አሳዛኝ ድርጊት #ገደሉት_እኮ😭😭😭 #አውሬዎች_ናችሁ😭😭😭 ልጄን አገኛለሁ ብለው 16ቀን ሙሉ በተስፋ የተንከራተቱ እናትና አባት አሁን ከመሸ ሞቱን ተረዱ😭 #ያሳዝናል😭 ፀባየ ሰናዩ አቤልን አውሬዎቹ ለስራ ብለው ጠርተውት ተሬ ላይ የመጨረሻ ስልኩን ከእህቱ ጋር ተደዋውሎ በጊዜ ቤት እንደሚመጣ ነግሯት ቢለያዩም ወንጀለኞቹ ለሆዳቸው ሲሉ ለ3 አንቀው በጩቤ ገደሉት😭 ዝምተኛው አቤላ ሲጠሩት እሺ ብሎ በትህትና ሄዶላቸው ህይወቱን በጭካኔ ነጥቀው ጫካላይ ለአውሬ ሰጡት😭 ከብዙ የፖሊስና ጓደኞቹ ድካም በኋላ ህይወቱ ባይገኝም ወንጀለኞቹ ተይዘው ለቀናት ምርመራ ተደርጎ አምነው ዛሬ ገድለው የጣሉበት ቦታ ጠቁመው ከ16ቀናት በኋላ የተረፈው አስክሬን ተገኝቷል😭 Henok fekadu
Mostrar todo...
በፖሊስ አሰቃቂ ድብደባ ለደረሰባት ሰሚራ በዛሬው ጁመአ መኖሪያ ቤት ተበረከተላት አልሃምዱሊላህ የአላህ ስራ ታላቅ መልካም ጁመአ
Mostrar todo...
ወሎ ትጣራለች ! ! ! አዎ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በተከሰተው ጦርነት ሳቢያ በወገኖቻችን ላይ የደረሰው ጉዳት እጅግ ከባድ ነው ። * ረጂ የነበረው ወሎ ! * ደግ ገራገር የነበረው ወሎ ! * መህረባ /መርሀባ እያለ እንግዳ ተቀባይ የነበረው ወሎ ! * ትልቅ ትንሹን ሸሆቹ እያለ ሰው አክባሪ የነበረው ወሎ ! ★አሁን ግን በገጠመው ጦርነት ምክንያት ተራበ ፣ ተጠማ ፣ ታረዛ ፣ ከቀዪው ተፈናቀለ ለተረጂነት ተጋለጠ ‼ ያ አላህ ይህ ፈተና ወዳንተ መመለሺያ ፣ የመተዛዘኛ ፣ የመደጋገፊያ የመረዳጃ ፣ የእድገት አድርግልን አሚን ።
Mostrar todo...
በፖሊስ የተደበደችው ሰሚራ አልሃምዱሊላህ ሁሉም ነገር ለኸይር ሆኖ ሥራ ጀምራለች በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ የተጀመረው በቀን 1 ጊዜ መመገብ ያልቻሉ ዜጎች የዕለት ጉርስ እንዲያገኙ በተከፈተው የተስፋ ብርሐን የምገባ ማዕከል 6ኛ ቅርንጫፍ ውስጥ ስራ ጀምራለች። …..*****….. #Ethiopia
Mostrar todo...
የነብዩ ሰ. ዐ ወ ክብር ለማጉደፍ በውሻ ምስል የሳላቸው ቆሻሻው ግለሰብ በመኪና አደጋ ሞተ || አልሃምዱሊላህ https://youtu.be/mHKHn8iFsko
Mostrar todo...
የውድ ነብያችን(ሰዓወ) ጠላት በሞት ተወገደ ከሞት ለማምለጥ በፖሊስ ሲጠበቅ የቆየው ከነጠባቂ ፖሊሶቹ ሞተ የውዱን ነብይ ክብር ለማጉደፍ በማሰብ በ2007 በውሻ ምስል ላይ የሳቸው ምስል ነው በሚል የካርቶን ምስል ሰርቶ የአለምን ሙስሊም አስቆጥቶ የነበረው ስዊዲናዊው ግለሰብ በመኪና አደጋ ህይወቱ አልፏል:: ላርስ ቪልክስ የተባለው ይህ ግለሰብ ይህን የካርቶን ምስል ሰርቶ ካሰራጨ ቡኃላ በደረሰበት ውግዘት ለደህንነቱ ሲባል በፖሊስ ጥበቃ ስር ህይወቱን ሲመራ የቆየ ሲሆን በሲቭል ፖሊሶች መኪና በሁለት ሲቭል ፖሊሶች ታጅቦ በመኪና እየየጓዘ በነበረበት ወቅት ከትልቅ መኪና ጋር ተጋጭቶ በ 75አመቱ ህይወቱ አልፏል:: በሰራው ወንጀል ስጋት ከሞት ለማምለጥ በፖሊስ ሲጠበቅ ቢቆይም ከነጠባቂ ፖሊሶቹ ሞት በመኪና አደጋ ጠልፎ ወስዶታል:: ይህን ሙጅሪም ግለሰብ የእጁን አላህ ይሰጠው ዘንድ ዱዓችን ነው! Abu Dawd Osman
Mostrar todo...
ከ6 ሰዓታት በላይ ተቋርጠው የቆየቱ ፌስቡክ፣ ዋትስአፕ፣ ኢንስታግራም እና ሜሴንጀር አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል። ፌስቡክ ለተፈጠረው ችግር ይቅርታ ከመጠየቅ ውጭ እስካሁን ችግሩ በምን ምክንያት እንደተፈጠረ ማብራሪያ አልሰጠም። በፌስቡክ መቋረጥ በ5 ሰዓታት ውስጥ ብቻ የማርክ ዙከርበርግ የግል ሃብት በ7 ቢሊዮን ዶላር ዝቅ ማለቱን ብሉምበርግ ዘግቧል። የፌስቡክ መተግበሪያዎች መቋረጥን ተከትሎ በትዊተር ፕላትፎርሙ ላይ ከፍተኛ የሆነ የተጠቃሚዎች ቁጥር ተመዝግቧል።
Mostrar todo...
እጅግ በጣም የሚያሳዝኑት የወሎ ተፈናቃዎች ያሉበት አሳዝኝ ሁኔታ ከቦታው ከ Kila ጋር የተደረገ ቆይታ https://youtu.be/Mzx3xPqy7MY
Mostrar todo...
ፌስቡክ፣ ዋትስአፕ፣ ኢንስታግራም እና ሜሴንጀር መተግበሪያዎች መስራት አቁመዋል። በፌስቡክ ስር የሚገኙት መተግበሪያዎቹ በተለያዩ የዓለም ሀገራት መስራት አቁመዋል። ኢትዮጵያ ውስጥም አገልግሎቶቹ ተቋርጠዋል። መተግበሪያዎቹ በበርካታ አገራት መቋረጣቸውን ዓለም ዐቀፉ የኢንተርኔት አገልግሎት ተቆጣጣሪ ተቋም ኔትብሎክስ አሳውቋል። ችግሩ በምን ምክንያት እንደተፈጠረ ፌስቡክ እስካሁን ያለው ነገር የለም።
Mostrar todo...
የአፋር ክልል የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ሃለፊ የነበሩት ወ/ሮ ዛራ ሁመድ የኢፌዲሪ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ምክትል አፈ-ጉባዔ ሆነው ተመርጠዋል።
Mostrar todo...
ዶ/ር ዐቢይ ጠ/ሚ ሆነው ተሾሙ። ዶክተር ዐቢይ አህመድ አሊ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ተሹመዋል።
Mostrar todo...
የሴቶች፣ ሕጻናትና ወጣቶች ሚኒስትሯ በገዛ ፍቃዳቸው ሥራቸውን መልቀቃቸውን አሳወቁ የሴቶች፣ ሕጻናትና ወጣቶች ሚኒስትር ፊልሳን ዐብዱላሂ መሐመድ በገዛ ፍቃዳቸው ኃላፊነታቸውን መልቀቃቸውን አሳውቀዋል። ወይዘሮ ፊልሳን ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በጻፉት የሥራ መልቀቂያ ደብዳቤ፣ ሥራውን ከተቀበሉበት ወቅት ጀምሮ የነበረውን ሁኔታ አንስተዋል። ሆኖም ሚኒስትሯ ሥነ ምግባርን የሚጥሱ ሁኔታዎች መተማመንን እንደሚጥሱ ከመጥቀስ ውጭ ሥራቸውን ለምን እንደለቀቁ በይፋ አልገለጹም። ወይዘሮ ፊልሳን ዐብዱላሂ መሐመድ የሴቶች፣ ሕጻናትና ወጣቶች ሚኒስትር ሆነው ያገለገሉት ከመጋቢት 3፣ 2012 ጀምሮ ነው። 🔴 መረጃው ያደረሰን Amba Digital - አምባ Amba Digital - አምባ ዲጂታል
Mostrar todo...
#መሞትማ ሁሉም ነፍስ ይሞታል! ይህ ሰው የሞተው ግን ለአራት ወር የአላህን ቃል ለማሰማት ከሞቀው ቤቱ በራቀበት አላህ ቀርቦት ነው! 'ኹሩጅ' ላይ እያለ ድካም በቃህ እረፍ ተብሎ ነው! ኢላሂ! እንደዚህ ዓይነት ሞት! © tofiq bahru
Mostrar todo...
#መሞትማ ሁሉም ነፍስ ይሞታል! ይህ ሰው የሞተው ግን ለአራት ወር የአላህን ቃል ለማሰማት ከሞቀው ቤቱ በራቀበት አላህ ቀርቦት ነው! 'ኹሩጅ' ላይ እያለ ድካም በቃህ እረፍ ተብሎ ነው! ኢላሂ! እንደዚህ ዓይነት ሞት! © tofiq bahru
Mostrar todo...
#መሞትማ ሁሉም ነፍስ ይሞታል! ይህ ሰው የሞተው ግን ለአራት ወር የአላህን ቃል ለማሰማት ከሞቀው ቤቱ በራቀበት አላህ ቀርቦት ነው! 'ኹሩጅ' ላይ እያለ ድካም በቃህ እረፍ ተብሎ ነው! ኢላሂ! እንደዚህ ዓይነት ሞት! © tofiq bahru
Mostrar todo...
አንደሉስ የቁርኣን ሂፍዝ ማዕከል ሲያስተምራቸው የነበሩ ተማሪዎችን በዛሬው እለት በድምቀት አስመረቀ። በቄራ ሰላም መስጂድ ውስጥ የሚገኘው አንደሉስ መድረሳ ማዕከል በመጀመሪያ ዙር የአዳር የቁርአን ሂፍዝ ትምህርት ለ2 ተከታታይ አመታት ሲያስተምራቸው የነበሩትን ተማሪዎች እንዲሁም በክረምት ኮርስ ለ1ወር የተማሩትን ተማሪዎች ታላላቅ አሊሞች፣ዳኢዎች፣ኡስታዞች እንዲሁም ታዋቂ ሰዎች በተገኙበት በድምቀት አስመርቋል።
Mostrar todo...
ታላቅ የሂፍዝ ተማሪዎች የምርቃት ፕሮግራም እሁድ መስከረም 09 /2014 ከጠዋቱ 3: 00 ጀምሮ በቄራ ሰላም መስጂድ ውስጥ የሚገኘው አንደሉስ መድረሳ ማዕከል በመጀመሪያ ዙር የአዳር የቁርአን ሂፍዝ ትምህርት ለ2 ተከታታይ አመታት ሲያስተምራቸው የነበሩትን ተማሪዎች እንዲሁም በክረምት ኮርስ ለ1ወር የተማሩትን ተማሪዎች ታላላቅ አሊሞች፣ዳኢዎች፣ኡስታዞች እንዲሁም ታዋቂ ሰዎች በተገኙበት በድምቀት ያስመርቃል። በዚህ ታላቅ ፕሮግራም ላይ እንድትገኙ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል
Mostrar todo...