es
Feedback
ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem

ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem

Ir al canal en Telegram

የዘመናችንን ቀለም ያሳያሉ ያልናቸውን የዚህ ትውልድ የስነ ግጥም ውጤቶችን እንጋራ - እናጋራ። ለማካፈል የፈለጋችሁትን በGitem_Sitem ፣ gitemsitem@gmail.com የጸሃፊ ስም እና ርዕስ አክላችሁ ላኩልን። We are all about sharing this generation's poetry. Please email us your pieces gitemsitem@gmail.com

Mostrar más
1 721
Suscriptores
+224 horas
-47 días
-1530 días
Archivo de publicaciones
°ሠው ሙሉ ትዝታ° ያይቆብ ነኝ -አታላዩ እሱን ተደግፋ እሷን እንዳቀፈ በወርቃማ ፍሬም በፎቶ ሰማይ ላይ ምስላቸው አረፈ .. . . ይሔም ቀን አለፈ። ከብዙ አመት ሗላ ጊዜ እሷን ነጥቆት ትራስ እያቀፈ ከግድግዳው ደረት ከሰቀለው ፎቶ አይኑን አሳረፈ። [መሽቶ ነበር] ካፊያ ነበር ቀኑ በታላቅ ፍርሃት ጧቷን ይዞ ነበር ወደ ቤት ሲያቀኑ የተውሶ ጃኬት አምሮ ለመታየት! አዲስ ሚኒ እስከርቷ ሳታየው በጣቱ ታጉን ያነሳላት ያነሳላት! እሱ በተውሶ እሷ አዲስ ገዝታ ፍቅራቸው ሲጀመር ሲፃፍ በትዝታ። ቀጠሮ ለማክበር የተለበሰው ጨርቅ እርቃን ሊተያዩ ለደስታቸው ሳይወልቅ (በመጀመሪያው ቀን።) አንድ ሰው ጠራቸው ቆሞ ፎቶ ቤት ጎን "አምሮብሃል " አለው ፎቶ ይነሱ ዘንድ ተጭኖ አስገደደው በደንገት ያየችው ኢሔ እንግዳ ሰው -ቀናችው ያምር ዘንድ ጃኬቱን ያዋ-ሰው እንደሆነ ነግሮአት ካለፈ በሗላ የሳቀችለት ሳቅ አሁን የሆነ ያህል በልቡ ሲደልቅ አቤት አጋጣሚ አቤት ሬ ከልብሶቹ መሃል ሲመረጥ ለዛሬ እድለኛ ሲሆን እሱን ተደግፋ እሷን እንዳቀፈ በፎቶ ሰማይ ላይ በተውሶ ልብሱ ምስላቸው አረፈ እሱን ተደግፋ እሱ እሷን አቅፎ ከቀኖቹ መሃል ሳይሞት ይታየዋል ይሔ ቀኑ ተርፎ።( ገዝፎ) እለቷን አሰበ በዕዝነ ህሊናው የሃሊት ተሳበ ተስፋ የገመደው ያ ታላቁ ፍቅር በቀናት ሲከዳ ትዝታ ትርፍ ሆኖ ፎቶ ይሆናል እዳ። እንደ ጊዜ አምሮ እንደ እለት ያለፈ ይሔ ውበታም ቀን ከአራቱ ግድግዳ በአንደኛው ያረፈ ፎቶ የለንም ወይ ተሰቅሎ የሚያን ዛሬን ያኮረፈ። ደሞ ስንተውን በሂወት መድረክ ላይ ድራማ ስንሰራ ታዛቢ ካልሆነ ፎቶና ካሜራ ሰው ድፍረት የለውም ትናንቱን ዘጋቢ ዛሬ ስለሌላው ነገን የሚያብራራ (ወይም) ከትናት ቀኖች ውስጥ በስሜት በእውነት ሊታረም የሚሻ ገጠመኙን ጥሎ ዛሬ ታሟል ይላል በትናንቱ ቆስሎ። በትዝታ ገመድ ለመሳብ ሲሞክር ዐይን ጨፈን አርገው ሊያዩት የሚቸግር ስንት ቀን ተሸኘ ከፎቶ ላይ ሳይቀር በአይምሮ ነየሚኖር ትዝታን መታመን አጉል ትምክህት ነው ስንት ትውስታ አለ..? በስሜት ተረድተን በምስል ያጣንው እዛጋር ነበርን.. እዚጋ ነበር..ን ለምን ወዲያ ሔድን ለምንስ ወዲ መጣን.? ምክንያቱ ምን ነበር ያወለካከፈን? . በቦታ በጊዜ ብልጭ የሚል ምስል አቅ በፎቶ ላይ ሳይቀር ከድሜ ጀንበር ደጃፍ ከምኔው ደረስን..? ዓለም ነን እያለን ከዓለም እያነስን። ሁሉም ጋር ለመኖር ቀን እንደባከንን ያልኖርን ናፈቀን የኖርን አስተከዝን... ሠው ሙሉ ትዝታ-ተነሳ በርጅና ሊፅፍ ወደሃላ -ሊያለቅስ እንደገና #ያይቆብ_ነኝ_አታላዩ #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ

የምስል ጥበብ ስነ-ግጥምን ስታውቃት. . . ! When photography meets poetry...! @ribkiphoto #ርብቃሲሳይ #ribkasisay #ግጥምሲጥም #gitemsitem
+4
የምስል ጥበብ ስነ-ግጥምን ስታውቃት. . . ! When photography meets poetry...! @ribkiphoto #ርብቃሲሳይ #ribkasisay #ግጥምሲጥም #gitemsitem

ሥራችንን በአዲስ መልክ ጀምረናል ሳይሆን አዲሱ ሥራችንን ጀምረናል። አእምሮ: የበላውን የማይረሳ፣ ባላመጠ መጠን የማይደክም፣ ባመነዠከ ቁጥር የሚሰላ የሚጠነክር ነው፡፡ ሆድማ ላሽ ነው፤ ቅድም የበላውን ምጥን ረስቶ እንቶፈንቶ ሲያቀርቡለት ስልቅጥ ነው፡፡ ለዚህ ውለታ አይረሴ አእምሮ መጽሐፍትን ለራሳችሁ እንዲሁም እንደ ሀብል፣ እንደ ቀለበት አሸብርቆ ለወዳጅ እና ለዘመድ ለመስጠት ስትፈልጉ፣ እኛ አለን። Book Bouquet/ የመጽሐፍት ጥምር ለየትኛውም ዝግጅት መጻሕፍትን በስጦታ መስጠት ለምትሹ የመጻሕፍት ጥምር አዘጋጅተን፥ ሊደርስ የምትፈልጉበት ቦታ ላይ ለማድረስ ተዘጋጅተን እየጠበቅናችሁ ነው፡፡ ለእንዲህ አይነት ሰው ምን መጽሐፍ ልስጥ ብትሉም፣ ግዴለም እኛ የሚገባቸውን እና የሚመጥናቸውን ዝርዝር አውጥተን እና ከእናንተ ጋር ተማክረን ለመስጠት ዝግጁ ነን፡፡ **ደራሲያን ወዳጆች ደግሞ ልዩ በደራሲያን የተፈረሙ፣ የተመረጡ መጽሐፍትን አዘጋጅተናል። -ከአዲስ አበባ፣ በተጨማሪ --ባህር ዳር እና አማራ ክልል አገልግሎት እንሰጣለን። --ባህር ማዶም። እዘዙን እንታዘዛለን ታዘን ያሉበት ድረስ እናደርሳለን! በኢንቦክስ ጻፉልን። በ0993514883 ደውሉልን። _ _

---------ምክንያት አልባ ሰበብ-------- ከሩቅ ይሰማኛል............. ስሰማው ያመኛል........... ትከሻሽ በክንዱ ይታየኛል ታጥሮ ከፍቅር ላመለጥሽ ምሽግ አስቆፍሮ ........................................ ፍቅር' ብሎ ጠራኝ ወደ ደስታ መራኝ እሱ ሩህሩህ ሁኖ እኔንም አራራኝ ...........,,,,,,,,,,,,,,,,,, ትይኛለሽ አሉ ክስ ስታቀርቢ ላዲሱ ፍቅረኛሽ እኔን ስተርቢ ለኔ ይኑር እንጂ ለሱ ኑሮ አያቅም ሁሌ ለሷ እያለ ለሱ አይጨነቅም ምን ልበልህ በቃ ራሱን አይጠብቅም! ~~~~~~~~~~~~~ እያልሽ ስታሚኝ እሱ ይደነቃል በውስጡ ይስቃል በውጩ ይበሽቃል ለፍቅር አልባ ፍቅር ራሱን ያሟሙቃል ..............._________________ @no_one2me

ሰው በሞላው ሃገር ሰው ባረፈ ቁጥር ትንሽ እሞታለሁ አገር 'ሚያሰድብ ያገር ሰው እያየሁ በከሰሩ ቁጥር ትንሽ እረክሳለሁ በሰከሩ ቁጥር ትንሽ አከስራለሁ በረከሱ ቁጥር ትንሽ እሰክራለሁ በከሰሱ ቁጥር ዶሴ አቀብላለሁ ሰው በሞላው ሃገር የሰው ያለህ እላለው ሲመርቁኝ አሜን አልል ሲነጅሱኝ የምነቅል ስንቀለቀል የማልነድድ ሳልለኮስ የምከስል ሰው በሞላው ሃገር ያውም የረገፈ አፈር ነካው ዘሬን ጸድቆም ተገዘፈ ሃሳቤም ተምቧችሮ እልፍ ረፈረፈ ሆዴም ልብ የባሰው ልቤም ሆድ የባሰው ሆኖት እያረፈ ሰይፈ ተማም #ሰይፈተማም #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ

እወቂብኝ ከማላቃቸው መልኮች ላይ ሳቆችሽን ዘግኛለሁ ለራሴ በልቤ መንገዶች ላይ በእግሬ ብዙ ተጉዣለሁ ለነፍሴ 'ምናለውና አይኗ!' 'ትቅራ!' ብዬም ፍቅር ስቀራ. . . ብርሃን ተምታቶብኛል . . . ብራ ቀኔን ብገብር ምን ይረባታል ማለቴስ ሰማይ ልቧ ላይ ብበራ ምኗ ነዶ ምኔ ሊጤስ...? . . . እኔ ተወርዋሪ ነኝ ምኔ ጋር እንደጨላለምኩ ምኑ ታወቀኝ ገና ዥው ብዬ እስከማልፍሽ ይጎበኘኛል ወና አንቺ ቅጽበት የምትይዢ ቦግ ብዬ ሳልፍብሽ በብርሃኔ የምትፈዢ ምኞት 'ምትናዘዢ ፍቅር የምታፍዢ እኔ ምኑ ጋር በርቼ ምኔን ጽልመት እንደወጋኝ ምኑም ምኑም የማይገባኝ ተወርዋሪ በሪ ሰይፍ ነኝ እወቂብኝ! እወቂብኝ! ሰይፈ ተማም #ሰይፈተማም #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ

የስዊድን መንግስት በኢትዮጵያ ውስጥ የኪነ-ጥበብ እና የባህል ባለሙያዎችን ለመደገፍ እና ለማጠናከር የሚረዳ አዲስ ከ3-5 ዓመት የሚቆይ መርሃ ግብር በማዘጋጀት ላይ ሲሆን ለዚህም ዘለቄታዊነት ያለው እና ለእርስዎ ጠቃሚ የሆነ ፕሮግራም ለማዘጋጀት የእርስዎን ጉልህ አስተያየትና እና ምልከታ እንፈልጋለን ፡፡ ስለሆነም ይህንን የዳሰሳ ጥናት በጥበብ እና ባህል ሙያ ዘርፍ ያለውን ተግዳሮትና ክፍተት ለማሻሻል ለዘርፉ የሚያስፈልገውን ለማሟላት እርሶ መፍትሔ ይሆናል ብለው የሚሰጡንን ሀሳብና አመለካከት እያደነቅን ለትብብርዎ ከልብ እናመሰግናለን! ጥናት (አማርኛ): shorturl.at/jtyK2 The Swedish government is developing a new 3-5 year-long programme to help support and strengthen art and culture practitioners in Ethiopia and we need your significant feedback and perspective to design a programme that has long-term impact and is relevant for You. We would therefore very much appreciate if you could fill out this survey and provide your perspective on needs, gaps and possible solutions to improve your condition as an art and culture practitioner. SURVEY (ENGLISH): shorturl.at/jmpyA #survey #swidish #creatives #art #culture #ግጥምሲጥም

https://www.youtube.com/watch?v=CZ_sjCXYiQ8 ይህን Amazing Addis የተሰኘ ቤት ብትከታተሉ ግጥሞችን እንዲህ ገጣሚዎቹ እራሳቸው አሳምረው ሲያነቡት ታገኛላችሁ እና እንጠቁማችሁ - ግቡ። መታሰቢያ እታለማው በአሜዚንግ አዲስ #መታሰቢያ_እታለማው #አሜዚንግ_አዲስ #ግጥምሲጥም

ታዳሚዎቹም አቅራቢዎቹም ወደነዋል፣ ጥሞናል፣ ድገሙንም ብለዋል! የታደማችሁም ያቀረባችሁም ተመስገኑልን! መምጣት ሳትችሉ ብትቀሩም ድጋፋችሁንና ሀሳባችሁን የቸራችሁንም ክበሩ! ቦታውን ሳታገኙት ቀርታችሁ
+4
ታዳሚዎቹም አቅራቢዎቹም ወደነዋል፣ ጥሞናል፣ ድገሙንም ብለዋል! የታደማችሁም ያቀረባችሁም ተመስገኑልን! መምጣት ሳትችሉ ብትቀሩም ድጋፋችሁንና ሀሳባችሁን የቸራችሁንም ክበሩ! ቦታውን ሳታገኙት ቀርታችሁ መምጣት ያልቻላችሁ ደሞ ይቅር በሉን! ቀጣዩ እንዳያመልጣችሁ ለታህሳስ 10 ቀጠሮ ያዙ ገጾቻችንንም ተከታተሉ https://t.me/seifetemam #ኤልያስ_ሽታሁን #ምግባር_ሲራጅ #አንዱ_ጌታቸው #ሌላ_ምስክር #ረቂቅ_አሰገደው #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም ህዳር 12 ከተካሄደው የመጀመሪያው የግጥም ሲጥም ዝግጅት ላይ የተወሰዱ ምስሎች 📷 @AnimaHela

ታዳሚዎቹም አቅራቢዎቹም ወደነዋል፣ ጥሞናል፣ ድገሙንም ብለዋል! የታደማችሁም ያቀረባችሁም ተመስገኑልን! መምጣት ሳትችሉ ብትቀሩም ድጋፋችሁንና ሀሳባችሁን የቸራችሁንም ክበሩ! ቦታውን ሳታገኙት ቀርታችሁ
+1
ታዳሚዎቹም አቅራቢዎቹም ወደነዋል፣ ጥሞናል፣ ድገሙንም ብለዋል! የታደማችሁም ያቀረባችሁም ተመስገኑልን! መምጣት ሳትችሉ ብትቀሩም ድጋፋችሁንና ሀሳባችሁን የቸራችሁንም ክበሩ! ቦታውን ሳታገኙት ቀርታችሁ መምጣት ያልቻላችሁ ደሞ ይቅር በሉን!

አስተምረኝ ( ሠይፈ ወርቅ) አስተምረኝ - ከማዕበል ጋር መደነስ አሠልጥነኝ - በእሳት ላይ መመላለስ ስሬን አጥብቅ - እንድታጠፍ ለነፋሳት ልቤን ግራው - ሲቀጠቀጥ እንዲከፈት ከዶፍ ከጎርፍ ከጣይ፣ ከቁር ከበረድ ጋር ከውሽንፍር ከመብረቅ ጋር እንድጨፍር ውብ ህይወትን እንድዘምር አስተምረኝ! ያለነፋስ - ዋሽንት በድን ሳይገረፍ - ክራር አይድን ሳይመታ - ሙት ከበሮ ለሰከነ - ለነፍስ ጆሮ በህመም ውስጥ ተቀምሮ ውብ ዜማ አለ በተፈጥሮ አስተምረኝ የማየትን ጥልቀት፣ ርቀት አሠልጥነኝ የማድመጥን ስር መሠረት በሸለቆ በከፍታ፣ በቁልቀለት ህመም ሳልሸሽ ያለህመም ልኑርበት #አስተምረኝ። #ምራኝ! #ማረኝ! ( ሠይፈ ወርቅ ) #አስተምረኝ #ሰይፉወርቁ #ሰይፈወርቅ #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ

የምስል ጥበብ ስነ-ግጥምን ስታውቃት. . . ! When photography meets poetry...! @ribkiphoto #ርብቃሲሳይ #ribkasisay #ግጥምሲጥም #gitemsitem
+4
የምስል ጥበብ ስነ-ግጥምን ስታውቃት. . . ! When photography meets poetry...! @ribkiphoto #ርብቃሲሳይ #ribkasisay #ግጥምሲጥም #gitemsitem

Elias Shitahun: (ከሚወጣው መድብል ቅምሻ : : ካቲካላ የለም ፤ ከዛሬ ጀምሮ! ለምን? መለኪያው ተሰብሮ። (ብለሽ ደሞ መሸጥ ቀጠልሽ) ጥያቄ! መለኪያው ነው እንጂ የተሰባበረው፣ ካቲካላሽማ… በርሜሉን ሙሉ ነው። ይሄንን ስትሰሚ እንዳትገረሚ። መኮመሪያ ቤትሽ ፣ መስፈሪያ የጣለ ባገኘው ይ፟ለካል ፤ ያገኘውን ኹሉ ፣ ልኬት ነው እያለ፡፡ እረ ያንቺስ እውነት ፣ ልኩን ያሳጣሽው፣ በምን ለክተሽ ነው? አንድ አረቄ እያሉ ፣ በርሜል የጨረሽው። መለኪያሽን ዐየሽ ፣ ንቀሽው ተሰብሮ፤ በዋጋ ያጣላል ፤ ልክ የሌለው ኑሮ። ለዋጋሽ መለኪያ፤ ለስካር መለኪያ፤ ለማወቅ መለኪያ፤ ለመኖር መለኪያ ፣ ጠፍቶሽ እንዳሰምጪ፤ አረቄሽን ዘግተሽ ፣ መለኪያሽን አውጪ፤ ተይ በልክ ቅጂ! ቀጥ ብሎ እየገቡ ፣ ሲወጡ በዳዴ፣ በምን ሰጠሻቸው ፣ ሰከሩልሽ ባንዴ። የአረቄሽ ሞገስ… ሰው እየመሰለው ፣ ዐይኑ ደም ሲቀላ፣ ገ፟ዳም ናት ይልሻል ፤ ሰው ቤትሽ ሲሞላ። ገድሽ መለኪያሽ ነው! የተሰበረልሽ፤ አትሰሰትም ብሎ ፣ ሰው የሚያመጣልሽ። ሀገሬው ሀገርሽ ፣ ስስት ከመለካት ተደበላልቆበት፣ የሚለካን ኹሉ ፣ ስስታም የሚል ስም ፣ ወስዶ ለጠፈበት። ተይ በልክ ቅጂ! ማይለካ አረቄ ፣ እያደልሽው በገፍ፣ ሀገር ሰከረልሽ ፤ በምኑ ይደገፍ። ተይ በልክ ቅጂ! ጤነኛውስ ይኹን ፤ እብድ አታስብጂ፤ ተይ በልክ ቅጂ! -------//////------- ኤልያስ ሽታሁን

ጥዑም ግጥም ቅመሱማ! ዮሐንስ ላቀው በግጥም ሲጥም ዝግጅት ላይ #ዮሐንስ_ላቀው #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ምግባርሲራጅ

በመጀመሪያው የግጥም ሲጥም ዝግጅት ላይ የተገኛችሁ ሁሉ ተመስገኑልን! ዝግጅቱን እንዴት አገኛችሁት? አጣሚዎቻችንስ እንዴት ነበሩ? #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም #መግባርሲራጅ
+3
በመጀመሪያው የግጥም ሲጥም ዝግጅት ላይ የተገኛችሁ ሁሉ ተመስገኑልን! ዝግጅቱን እንዴት አገኛችሁት? አጣሚዎቻችንስ እንዴት ነበሩ? #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም #መግባርሲራጅ

ኤሊያስ ሽታሁን በግጥም ሲጥም!

እንግዲህ በየወሩ የዘመናችንን የግጥም ጀግኖች እንዲህ አንዳቸውን ከፊት እያዘመትን ስራዎቻቸው የሚገባቸውን ቦታ እንዲያገኙ እንጮሃለን! የመጀመሪያው የግጥም ሲጥም ዝግጅት 'ራስ' ይህ ድንቅ ገጣሚ ነው
እንግዲህ በየወሩ የዘመናችንን የግጥም ጀግኖች እንዲህ አንዳቸውን ከፊት እያዘመትን ስራዎቻቸው የሚገባቸውን ቦታ እንዲያገኙ እንጮሃለን! የመጀመሪያው የግጥም ሲጥም ዝግጅት 'ራስ' ይህ ድንቅ ገጣሚ ነው! ምግባር ሲራጅን እስካሁን ለማታውቁ ጥሩ አጋጣሚ መጥቶላችኋል። #ምግባርሲራጅ #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም

Here is your event calendar from @linkupaddis for the next two weeks. Thank you @linkupaddis for the usual support and for in
+1
Here is your event calendar from @linkupaddis for the next two weeks. Thank you @linkupaddis for the usual support and for including our event in your calendar! Checkout their TV channel here 👇🏽 http://www.linkupaddis.com/linkup-tv