ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem
Ir al canal en Telegram
የዘመናችንን ቀለም ያሳያሉ ያልናቸውን የዚህ ትውልድ የስነ ግጥም ውጤቶችን እንጋራ - እናጋራ። ለማካፈል የፈለጋችሁትን በGitem_Sitem ፣ gitemsitem@gmail.com የጸሃፊ ስም እና ርዕስ አክላችሁ ላኩልን። We are all about sharing this generation's poetry. Please email us your pieces gitemsitem@gmail.com
Mostrar más1 722
Suscriptores
Sin datos24 horas
-27 días
-530 días
Archivo de publicaciones
እንደ ብርቱ ምዕመን ፥ እንደ በቃ ወልይ
ቀኝ ብቻ ሲሆን የአህዛብ መስተሐልይ
በግራ አውለኝ ብለህ ወደ አምላክህ ፀልይ ።
ጊዜህን አትግድል ፥ ከአቅምህም አትጉደል
ስትፈልግ አቻህን ፤
አንዳንዴ
ህብረት ካላዋጣህ ሞክረው ብቻህን ።
አትችልበትም ወይ ?
እንዲሁ በሰውነት
ያለ መንግስት አዋጅ ራስን መዳኘት
ሃይማኖት ሳይኖርህ ፈጣሪህን ማግኘት
ከወተት ነጥሎ ገነትን መመኘት ?
የሸረሪት መንጋ ድሮች አሰባስቦ አንበሳን ሲያጠምደው
እስኪ አንተም ሰው ሆነህ በዜማህ አላምደው
ውደደው
ውደደው
በፖለቲካ አቋም
ድርጅት ማቋቋም
ኮሚቴና ተቋም
እንደ እህል ተዘርቶ በየ ስፍራው ሲናኝ
ልክ እንደ መናፍቅ ፥ የከተማ መናኝ
ከዓለም ተነጥለህ ፥ ከዓለም ጋ ተገናኝ ።
© Hab HD
We will be having an open mic poetry and music session at the Easter Bazaar at Sabegn Concept Store on the eve.
Come join us checkout the venders and jam with us!
Repost from Arada T-Shirts
Some of the products made for ግጥም ሲጥም
Contact us to ORDER or to take INFO. 0944213490
@A_Sentient_Being Or @Yoyo_101
Don't forget You can also order t-shirts, hoodies & mugs of your own design (pictures, text any thing)
Repost from N/a
ማስ 1
ማስፈለጉን ባያይ
ከጊዜ የተጣላ የዘመን ባተሌ
ማስ ፈለኩን ባያይ
መኖር አጎድጉዶት የዛሬ ገደሌ
ማስ አልኩት ለልቤ
ለተንጎዳጎደው የትላንት ገድሌ
መቀበር ላልቀረ
ወግ ሁሉ ቀርቶብኝ
በራሴ አቆፋፈር በድኔ እንዲያርፍልኝ
ማስ ሰብን እስከውስጥ
ከላይላይ በዝቶ ነው
የምንጎደፍረው
ከላይ ልጡን ላንልጥ
ማስጠርጠሩ ላይቀር
ገና ከምጣዱ
ማስታወቁ ሳለ
ምንድነው ማስፋቱ
ጠብ የማይል እህል ?
ምንድነው ማስፋቱ
ጠብ የሚያህል እልህ?
ይኸውልህ - እኔ
ከልብ ያላደረ
እውነት መሳይ ሃሰት
ሃሰት መሳይ እውነት
እያደናበረው
ማስመሰል ምስ ሆኖት
በማሱለት ጉድ ጓድ
ያልተዛቀን ቁልል
ተራራህ ነው ብለው
ዘመን ተጋሪዬን
ይሸነግሉታል
ከፍታህ፤ ጉድጓድ ውስጥ
ከወለሉም በታች
ካሉት ከተሻለ
ምን ይሰራልሃል
ከተማሰው መውጣት
ይሉታል ያስሩታል
ሰው ከተማ ሳለ
ከተማሰው ገብቷል
... ይኸውልህ እኔ ...
ማስ መቀበሪያህን
ማንም ከሚያበጀው ምንምነትህን!
ማስተካከል ቀርቷል
እራሱ ልክነት ይሳሳት ከጀመር
ዘመናት ተቆጥረው
የርዝማኔው ስፋት
የጊዜው ክብደቱ
ስህተት ልክሆኖ
እራሱ ልክነት
ልክ የሳተበቱ
የቀናቱ ውፍረት የቀጠነበቱ
ስንት ቆጥሯል ዘመን
ማስተካከል ትተን
ማስከተል ከጀመርን
ይኸው በኔ ዘመን
ማስከተል እንደአዲስ
አሁንም ብርቅ ነው
አዲስ የእምነት በር
እንደፈለሰፈ
የፋርስ ወይ የመካ
የናዝሬት የኔፓል
የግሪክ የካም ሰው
ተከታይ ከሌለህ
ማስመስከር አትችልም
ሰው መሆንክን ለሰው
ማስፈለጉን ባያይ
ከጊዜ የተጣላ የዘመን ባተሌ
ማስ ፈለኩን ባያይ
መኖር አጎድጉዶት የዛሬ ገደሌ
ማስ አልኩት ለልቤ
... ይኸውልህ እኔ ...
ማስ መቀበሪያህን
ማንም ከሚያበጀው ምንምነትህን!
Repost from YOM CARTOON PICTURES
#መባቻ_የጥበብ_ማህደር
እነሆ ወርሃዊው የጥበብ ድግሳችን የሚያዚያ ወር ዝግጅቱን መደገሱን ተያይዞታል።
በዚህ የጥበብ ምሽት ላይ በተለያዩ የጥበብ ስራዎች በመረጣችሁት ርዕሰ ጉዳይ ዙሪያ መሳተፍ ለምትፈልጉ
በግጥም
ወግ
የአንድ ሰው ተውኔት
ሙዚቃ እና መሠል የጥበብ ስራዎች መሳተፍ የምትችሉ ሲሆን ስራዎቻችሁን መጋቢት 26/2014 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 ሰዓት ይዛችሁ መቅረብ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
ለበለጠ መረጃ 0948034115/0928567096 ደውሎ መጠየቅ ይችላሉ።
የኅብረቃል ድምቀት የነበሩት መባቻዎች ደብረማርቆስ ላይ ቀጣይ ድግስ አላቸው
ለምን ከከተማ ግርግር አፍታ ወስደን ወጣ ብለን የነሱን ልዩ ቀለም ታድመን በስጦታቸውም ተደምመን አንመለስም?
የኅብረቃል ድምቀት የነበራችሁ ሁሉ ምስጋናችን ይድረሳችሁ!!!
ፌስቲቫሉን ስፖንሰር በማድረግ እውን እንዲሆን ያገዘን ሐረር ቢራም ውሎ ይግባ!
ፈለክ በአጋርነት አብሮን ስለነበረም ከልብ እናመሰግናለን!
Shout out to the beautiful HibreQal crowed!!! The turn out was great, it didn't look like a first edition!
Thank you Harar Beer for sponsoring our unique festival!
Felek Notebooks, we are proud to call you a partner in pulling off this one of a kind event!
#HibreQal_Festival #World_Poetry_Day #HibreQal2022 #Poetry
#Harar #Felek #Poetic_Saturdays #LinkUp_Addis
#Krinfud #GitemSitem
ወሎ ሰፈር ግርጌ
ከጎተራ ራስጌ
ስሽከረከር ብውል ጠፍቶብኝ መንገዴ
በቀዝቃዛ ውሃ እንደ እሳት መንደዴ
ለሰው ልጅ ቢደንቀው አውሬ ማላመዴ
ይኸው እገኛለው
የአህያዬን በረት ለጅብ አጋርቼ
ነባቢቱን ስንቅ ዱዳውን አውርቼ
የሚሽቴን መቀነት ለውሽማ አውርሼ
ጫካ እባርካለሁ ህንጻ ላይ ቀድሼ
©️እስሩ ገብሩ
አታውቂም?
ጓደኛ መስታወት የኔነት ነጸብራቅ:
በሩቅም እያለ ከልብ ውስጥ የማይርቅ:
ጓደኛ ፈውስ ነው የሚስጥሬ አለም:
እንደ ብቸኝነት ከቶ የወጋኝ የለም:
እኔ አንቺን ካጣው ሞቴ ነው አታውቂም?
:
ኦ ኦ ኦ ትችላለህ አትበይኝ አልችልም ግድየለም:
አጉል ተስፋ አትስጪኝ ድጋሜ አልታመም:
ብቸኝነት ጎድቶኝ መቼም አላገግም:
አስበሽዋል...ሊያውም በድጋሜ ስጎዳ ስሰበር:
ምን የሚሉት ቁስል ወይ ላይድን ወይ ላይ ሽር:
አረ ወይኔ....ልቤ ለይ ሲወጣ እንዴትስ ሊረሳ:
ሰው የማጣት ቁስል ዘላቂ ጠባሳ::
ይድናል አትበይኝ ጊዜውን ጠብቆ:
ትዝታ እያለበት ቁስል መቼ ደርቆ:
ይታያል ብለሽ ነው ሰውን ያጣ አለም:
አንድም ባዶ ሸክም:
ሌላም
በቁሙ የሞተ መሆኑን አታውቂም???
©ከ ሚኪ ሳ.
Repost from N/a
"ትክክል"
~~
ትክክሉን ሁላ
ማነው ልክ ያረገው?
ልክ አይደለም ብሎስ
ማነው የደነገገው?
ሁሉም ትክክል ነው
ሁሉም እንደራሱ፣
በተረዳው መጠን
መልሱን መመለሱ፡፡
የማነው ትክክል
እነማን?የትኞች?
በወጣኸው ዳገት
ባለፍኩት መንገዶች፡፡
የየቅሉ መንገድ
ስህተት የተባለው፣
ያረከው ያረኩት
ሁሉም ትክክል ነው፡፡
በአንተነትህ መዝን
በእኔነቴ አውጣኝ፣
በዳገትህ ስፈር
በመንገዴ ለካኝ፡፡
ሊያ አበበ✍
The Mosaic Hotel is hosting a professional networking and inspirational event on Saturday 14 April 2022. The event, which will be titled Self-Reconciliation for Generation Building will be hosted by Fitsum Atnafwerk, and will feature prominent opinion leaders and social influencers. Doors will open at 4:30pm, and entrance fee is ETB 200.
@linkupaddis
Repost from LinkUp Addis
Gitem Sitem and Krinfud Digitals are partnering up to organize a festival titles Hibrekal Festival on Saturday 09 April 2022 at Fana Park. The event will feature poetic performances, music, live art, short plays and other performances. Entrance fee is ETB 150. Stay tuned for more info. @linkupaddis
በየወሩ ሽፍታ የሚካሄደው ክፍት መድረካችን መጋቢት 28 የእናንተን ስራዎች ለእናንተው ለታዳሚዎች ያቀርባል።
ዝግጅታችን ለማንኛውም ሰው ፊት መቅረብ ለሚችሉ የጥበብ ዘርፎች ክፍት ነው። ምዝገባ 12 ሰዓት ይጀመራል ዝግጅቱ ደግሞ 12:30 ይጀምራል። መግቢያ 50ብር ብቻ!
ኑ እና በነጻነት እራሳችንን እንግለጥበት!
ለመጀመሪያዎቹ 50 ታዳሚያን ነጻ አራዳ አለን።
