Diinii kee Anaakara (Md Ali)
Ir al canal en Telegram
دروس وفتاوي ومحاضرات باللغة العفرية ★Diini barittooy, fatwaa kee Daqwa Qafar afat Tû mabul=> @Anaakar or @acmadxalol
Mostrar más1 617
Suscriptores
+124 horas
+97 días
+2430 días
Archivo de publicaciones
መሳፍንት ተስፋ ይባላል። ጠ/ሚ አብይ አሕመድን ሙስሊም አድርጎት ኖሮ እንዴት ሙስሊም ስልጣን ይይዛል? እያለ ነው። ሙስሊም ኢትዮጵያን ለመምራት ብቁ አይደለም። ትላንትም ልጅ እያሱ ከስልጣኑ የተፈናቀለው በሙስሊምነት ተጠርጥሮ ነው። የትላንቱ ሲገርመን ዛሬም በ21ኛው ክ/ዘመን ትላንት ላይ የተቸነከሩ ሻጋታሞች መኖራቸው ነው የሚገርመው።
በነገራችን ላይ ጠቅላዩን ሙስሊም አድርጎ ማሰብ የብዙ ደናቁራን የጋራ እምነት ነው። ለማንኛውም የኢትዮጵያ መቻቻል ከፍ ሲል ይሄ ነው። በአንዳንድ ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ መጋራት። አለቀ። እንዲያውም እነሱ የሚፈልጉት ታቦት የሚሸኝ፣ መስቀል የሚያከብር፣ ወዘተ ነው። ከዚያ ባለፈ የዚች ሃገር መሪ ለመሆን ከሚያስፈልጉ መስፈርቶች አንድ ሙስሊም አለመሆን ነው። እሳቤያቸው አይደለም የሚደንቀኝ። የሚደንቀኝ ይህንን ዘገምተኛ አሳባቸውን ባደባባይ ማቀርሸታቸው ነው።
(ቪዲዮው የነ ዲያቆን ሃብታሙ አያሌው፣ የነ ዲያቆን ዘመድኩን በቀለ መዋያ በሆነው መረጃ ቲቪ የቀረበ ሲሆን ወዲያው አጥፍተውታል። ልብ ቢኖራቸው ሙስሊሙን ማህበረሰብ ግልፅ ይቅርታ መጠየቅ ይገባቸው ነበር።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
🌿ሴትን መንካት ውዱእ ያፈርሳልን?🌿
~ ~ ~ ~ ~ ~~ ~ ~
♻️ ማሳሰቢያ፦
ለወንድ ሴትን መንካቱ ውዱእ ያፈርሳልን? የሚለውን ነጥብ ስናነሳ በተመሳሳይ ለሴት ወንድን መንካት ውዱእ ያፈርሳል ወይ የሚለው ታሳቢ ይደረጋል። ስለዚህ ጉዳዩ በአንዱ ፆታ ላይ የሚገደብ አይደለም።
ተቃራኒን ፆታ መንካት ውዱእ ያፈርሳል ወይስ አያፈርስም በሚለው ላይ ከኢስላም ምሁራን 3 ጎላ ያሉ የተለያዩ አቋሞች ተንፀባርቀዋል።
✅ አቋም አንድ ✅
በየትኛውም ሁኔታ ሴት መንካት ውዱእ ያፈርሳል የሚል ነው። ይሄ የኢማሙ ሻፊዒይ አቋም ሲሆን ማስረጃቸውም ተከታዩዋ የቁርኣን አንቀፅ ነች፦
(أَوْ لاَمَسْتُمُ النِّسَاء)
"ወይም ሴቶችን ብትነኩ (ሶላትን ራቁ)።" [ኒሳእ፡ 43]
ነገር ግን እዚህ ላይ የተጠቀሰው አካላዊ ንክኪ ሳይሆን የግብረ ስጋ ግንኙነት እንደሆነ ኢብኑ ዐባስ ረዲየላሁ ዐንሁ በግልፅ ፈስረውታል። ተፍሲራቸው ከሌሎች የተሻለ ክብደት ይሰጠዋል። ምክንያቱም ነብዩ (ﷺ) "አላህ ሆይ! በዲን ላይ አስገንዝበው። ተፍሲርንም አሳውቀው" ብለው ዱዓእ አድርገውላቸዋልና። [አልባኒ ሶሒሕ ብለውታል።]
ኢብኑ ጀሪርም ይህኛውን ተፍሲር ነው የመረጡት። ስለዚህ የተጠቀሰውን ቁርኣናዊ መልእክት በአካላዊ ንክኪ መተርጎም ልክ አይሆንም።
✅ አቋም ሁለት ✅
ሴትን መንካት ከነጭራሹ ውዱእ አያፈርስም የሚል ነው። ይሄ የኢማሙ አቡ ሐኒፋህ አቋም ነው። በዚህ ላይ ያለው ማስረጃም፦
1ኛ፦ ጦሃራን በተመለከተ ግልፅ አፍራሽ እስከሚገኝ ድረስ መነሻ መሰረቱ የተደረገው ባለበት መኖሩ ነው። መጥፋቱን የሚጠቁም ግልፅ ማስረጃ እስከሚቀርብ ድረስ ባለበት ይዘልቃል። ሴትን መንካት ጦሀራን የሚያፈርስ ለመሆኑ ደግሞ ማስረጃ የለም። ስለዚህ ውዱኡ ባለበት ይቆያል ማለት ነው።
2ኛ፦ እናታችን ዓኢሻህ ረዲየላሁ ዐንሃ እንዲህ ትላለች፦
كُنْتُ أَنَامُ بَيْنَ يَدَيْ رَسُولِ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ وَرِجْلَايَ فِي قِبْلَتِهِ فَإِذَا سَجَدَ غَمَزَنِي فَقَبَضْتُ رِجْلَيَّ فَإِذَا قَامَ بَسَطْتُهُمَا
"ከአላህ መልእክተኛ (ﷺ) ፊት ለፊት እተኛ ነበር። እግሮቼ በቂብላቸው በኩል ይሆናሉ። ሱጁድ ሲወርዱ ይቆነጥጡኛል እግሮቼን እሰበስባለሁ። ሲነሱ አዘራጋቸዋለሁ።" [ቡኻሪ፡ 382]
በነሳኢ ዘገባ ደግሞ "ዊትር ሊያደርጉ ሲያስቡ ጊዜ በእግራቸው ይነኩኛል።" [አልባኒ ሶሒሕ ብለውታል።]
3ኛ፦ አሁንም እናታችን ዓኢሻ ረዲየላሁ ዐንሃ እንዲህ ትላለች፦
فَقَدْتُ رَسُولَ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ لَيْلَةً مِنْ الْفِرَاشِ فَالْتَمَسْتُهُ فَوَقَعَتْ يَدِي عَلَى بَطْنِ قَدَمَيْهِ وَهُوَ فِي الْمَسْجِدِ وَهُمَا مَنْصُوبَتَانِ ...
''የአላህ መልእክተኛን (ﷺ) በአንድ ሌሊት ከመኝታቸው አጣኋቸው። ስፈልጋቸው መስጂድ ውስጥ ሆነው እጄ በውስጥ እግሮቻቸው ላይ አረፈች። እነሱ (እግሮቻቸው) ተተክለው (መሬት ይዘው ቀጥ ብለው) ነው ያሉት። ..." [ሙስሊም የዘገቡት]
በነሳኢና በይሀቂ ዘገባ ላይ ደግሞ "እሳቸው ሱጁድ ውስጥ ሆነው" የሚል ጭማሪ አለው።
በነዚህ ሐዲሦች ውስጥ ነብዩ (ﷺ) ሶላት ውስጥ ሆነው ዓኢሻን መንካታቸው ንክኪው ውዱእ አፍራሽ እንዳልሆነ ያሳያል።
♻️ ብዥታ፦
ሻፊዒያዎች ግን እጅ አይሰጡም። "ምናልባት ከቀጥተኛ አካላዊ ንክኪ የሚጠበቅ ነገር (ጨርቅ) ላይስ ቢሆን የነኳት?" ይላሉ። ሸውካኒ በዚህ ላይ ምላሽ ሲሰጡ እንዲህ ይላሉ፦ "ይሄ አጉል መድረቅረቅና ግልፅ ተቃርኖ ያለበት አረዳድ ነው።"
4ኛ፦ አሁንም እናታችን ዓኢሻ ረዲየላሁ ዐንሃ እንዲህ ትላለች፦
4- أن النبي صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَبَّلَ امْرَأَةً مِنْ نِسَائِهِ ثُمَّ خَرَجَ إِلَى الصَّلَاةِ وَلَمْ يَتَوَضَّأْ
"ነብዩ (ﷺ) ከሴቶቻቸው አንዷን ከሳሙ በኋላ ከዚያ ለሶላት ወጡ። ውዱእ አላደረጉም።"
ይህንን መረጃ በርካቶች ከሰነድ አንፃር ደካማ ነው ሲሉ ኢብኑ ጀሪር፣ ኢብኑ ዐብዲልበር፣ ዘይለዒ እና አልባኒ ሶሒሕ ብለውታል። ዶዒፍ ነው የሚለውን ብናስቀድም እንኳ ያሳለፍናቸው መረጃዎች በቂ ናቸው።
✅ አቋም ሶስት ✅
በስሜት ከነካ ውዱእ ይፈርሳል። በስሜት ካልሆነ ግን አይፈርስም የሚል ነው። ይሄ የማሊኪያና የሐናቢላ አቋም ነው። ያደረጉት የቀደሙትን ሁለት አቋሞች መረጃዎች ለማጣጣም መሞከር ነው። ሴትን መንካት ውዱእ ያፈርሳል የሚሉት ወገኖች የሚያቀርቡት መረጃ ተፍሲራቸው ልክ እንዳልሆነ አሳልፈናል። ስለዚህ ይሄኛው ሃሳብ ልክ የሚሆነው የነዚያኞቹ ተፍሲር ልክ ቢሆን ነበር። ተፍሲሩ ልክ ካልሆነ ይሄኛው አካሄድ ውሃ አያነሳም።
ስለዚህ ሁለተኛው ውዱእ አያፈርስም የሚለው አቋም ያለ ተቃርኖ ይቀራል ማለት ነው። ስለሆነም በስሜትም ሆነ ያለ ስሜት፣ አስቦበትም ሆነ በስህተት፣ ቤተሰብም ትሁን ሩቅ (አጅነቢያህ) በየትኛውም ሁኔታ ሴት መንካት ውዱእ አያፈርስም የሚለው አቋም ትክክለኛ ነው ማለት ነው።
♻️ ማሳሰቢያ፦
1- በስሜት የነካ ሰው ፈሳሽ (መዝይ) ከወጣ በዚህን ጊዜ ውዱኡ ይበላሻል።
2- ንክኪው ብቻውን ውዱእ አያፈርስም ማለት ለወንድ አጅነቢያህ ሴትን ወይም ለሴት አጅነቢይ ወንድን መጨበጥ ይቻላል ማለት አይደለም። ክልክል ነው። ያወራነው ስለ ውዱእ ብቻ ነው።
(ኢብኑ ሙነወር፣ ጥር 6/2014)
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
#Rufto_le_xaaguy_Inkih_tan_Samara_kee_Loogiyaay_Dariifal_Geytinta_Ummattah_rubna
بسم الله الرحمن الرحيم الحمد لله رب العالمين والصلاة والسلام على المبعوث رحمة للعالمين سيدنا محمد وعلى آله وأصحابه أجمعين
Yamaate Acaadah axcih ayrok 8/5/2014 Qafár Qoloma #Daqwâ barnaamij #Samarâ Magaalal Aallelem sin aytit hayna.
1. Dr Macammad Saani
2. Sheykh Macammad Awwal Cayaat
3. Sheykh Qali Qabdalla Ismaaqil
Fooca akak beyta qoloma elle geytimak barnaamij Aallelon.
Toysa Raaqaanam madudda.
Acaad Saaku 2:15 xabba haanam
#Arac
Samarak Qolô Majlisi. Axcih Sayyô xintimah tû barittok taturra intan wak geeliton.
Share Abaanam mahawweenina
☔️Racbiyya deqsita nagrâ kitaabih darsi.
🎬Shek caydar Saalic(cafizahullaah)
🔰2⃣3⃣
Join us📩
t.me/httpsDiiniKeeAnaakara
☔️Racbiyya deqsita nagrâ kitaabih darsi.
🎬Shek caydar Saalic(cafizahullaah)
🔰1⃣8⃣
Join us📩
t.me/httpsDiiniKeeAnaakara
☔️Racbiyya deqsita nagrâ kitaabih darsi.
🎬Shek caydar Saalic(cafizahullaah)
🔰1⃣6⃣
Join us📩
t.me/httpsDiiniKeeAnaakara
☔️Racbiyya deqsita nagrâ kitaabih darsi.
🎬Shek caydar Saalic(cafizahullaah)
🔰 1⃣1⃣ & 1⃣2⃣
Join us📩
t.me/httpsDiiniKeeAnaakara
☔️Racbiyya deqsita nagrâ kitaabih darsi.
🎬Shek caydar Saalic(cafizahullaah)
🔰1⃣0⃣
Join us📩
t.me/httpsDiiniKeeAnaakara
☔️Racbiyya deqsita nagrâ kitaabih darsi.
🎬Shek caydar Saalic(cafizahullaah)
🔰0⃣9⃣
Join us📩
t.me/httpsDiiniKeeAnaakara
☔️Racbiyya deqsita nagrâ kitaabih darsi.
🎬Shek caydar Saalic(cafizahullaah)
🔰0⃣8⃣
Join us📩
t.me/httpsDiiniKeeAnaakara
☔️Racbiyya deqsita nagrâ kitaabih darsi.
🎬Shek caydar Saalic(cafizahullaah)
🔰0⃣7⃣
Join us📩
t.me/httpsDiiniKeeAnaakara
☔️Racbiyya deqsita nagrâ kitaabih darsi.
🎬Shek caydar Saalic(cafizahullaah)
🔰0⃣6⃣
Join us📩 https://t.me/httpsDiiniKeeAnaakara
የፈጅር (የሱብሕ) ሶላት ትሩፋቶች እና ፈጅርን አለመስገድ ያለው አደጋ
~ ~ ~~~~ ~~~ ~
1. ፈጅርን ስገድና በአላህ ጥበቃ ስር ሁን፡፡ ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም “ሱብሕን የሰገደ በአላህ ጥበቃ ስር ነው” ብለዋል፡፡ [ሙስሊም]
2. ፈጅርን ስገድ ሌሊቱን በሶላት እንደቆምክ ይቆጠርልሃልና፡፡ ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም “ዒሻእን በጀማዐህ የሰገደ ግማሽ ሌሊትን በሶላት እንደቆመ ነው፡፡ ሱብሕን በጀማዐህ የሰገደ ደግሞ ሌሊቱን በሙሉ እንደቆመ ነው” ይላሉ፡፡ [ሙስሊም]
3. ሱብሕን ስገድ እራስህን ከሙናፊቆች መገለጫ አፅዳ፡፡ ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም “በሙናፊቆች ላይ እንደፈጀር እና ዒሻእ ሶላት የሚከብድ የለም” ይላሉ፡፡ [ቡኻሪና ሙስሊም]
4. ፈጅርን ስገድ ለጭንቅ ቀን ብርሃን ይሆንሃልና፡፡ ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም “በጨለማዎች ወደ መስጂዶች የሚጓዙትን በቂያማህ ቀን ሙሉ በሆነ ብርሃን አብስራቸው” ይላሉ፡፡ [ሶሒሕ አቢ ዳውድ፡ 570]
5. ሱብሕን ስገድ መላእክት ይመሰክሩልሃል፡፡ ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል፡- “በናንተ ውስጥ የሌሊት መላእክትና የቀን መላእክት ይተካካሉ፡፡ በፈጅር ሶላት እና በዐስር ሶላት ላይ ይሰባሰባሉ፡፡ ከዚያም እነዚያ በናንተ ዘንድ ያደሩት (ወደ ሰማይ) ይወጣሉ፡፡ ይህኔም ጌታቸው በነሱ ሁኔታ አዋቂ ሆኖ ሳለ “ባሪያዎቼን በምን ሁኔታ ላይ ተዋቸኋቸው?” ሲል ይጠይቃቸዋል፡፡ “እነሱ እየሰገዱ ነው የተውናቸው፡፡ እየሰገዱም ነው የመጣናቸው” ይላሉ፡፡ [ቡኻሪና ሙስሊም]
6. ሱብሕን ስገድ ሙሉ የሐጅና የዑምራን አጅር እፈስ፡፡ ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም “የማለዳን ሶላት በጀማዐ የሰገደ ከዚያም ፀሀይ እስከሚወጣ ድረስ አላህን እያወሳ የተቀመጠ እና ከዚያም ሁለት ረከዐ ሶላት የሰገደ ልክ እንደ ሐጅና ዑምራ አጅር አለው፡፡ ሙሉ! ሙሉ ! ሙሉ!” ይላሉ፡፡ [አስሶሒሐህ፡ 3403]
7. ፈጅርን ስገድ በአለም ላይ ካሉ ፀጋዎች ሁሉ በላጭ የሆነ ፀጋ የምትጎናፀፍበት እድል ታገኛለህና፡፡ ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም “የፈጅር ሱንናህ (ከፈርዱ በፊት የምትሰገደዋ ትርፍ 2 ረከዐ ሶላት) ከዱንያ እና በውስጧ ካለ ሁሉ በላጭ ነች” ይላሉ፡፡ [ሙስሊም]
8. ፈጅርን ስገድ ከጀሀነም መትረፊያ ጀነትን መጎናፀፊያ ብስራትን ታገኛለህና፡፡ ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም “ፀሀይ ከመውጣቷ እና ከመግባቷ በፊት የሰገደ አንድም ሰው እሳት አይገባም” ይላሉ፡፡[ሙስሊም] እነዚህ ሶላቶች ፈጅርና ዐስር ናቸው፡፡ በሌላም ሐዲሥ “ሁለት ብርዳማ ሶላቶችን የሰገደ ጀነትን ይገባል” ብለዋል፡፡ [ቡኻሪና ሙስሊም]
9. ፈጅርን ስገድ ከፀጋዎች ሁሉ በላጭ ፀጋ የሆነውን የላቀውን ጌታ መመልከትን ትታደላለህና፡፡ ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም “እናንተ ይህን ጨረቃ እንደምታዩት ጌታችሁን ታያላችሁ፡፡ እሱን በማየትም አትቸጋገሩም፡፡ ፀሀይ ከመውጣቷና ከመግባቷ በፊት ባለ ሶላት አለመረታት ከቻላችሁ አድርጉት (ስገዱ)” ይላሉ፡፡ [ቡኻሪና ሙስሊም]
10. ፈጅርን ስገድ ጥሩ ነፍስ ይዘህ አንግተህ ንቁ ሆነህ ትውላለህ፡፡ [ቡኻሪና ሙስሊም]
ተጠንቀቅ!
1. የፈጅርን ሶላት ከማሳለፍ ተጠንቀቅ፡፡ ከፈጅር ሶላት መሳነፍ አደገኛ የሆነ የሙናፊቆች ምልክት ነውና!! [ቡኻሪና ሙስሊም]
2. የፈጅርን ሶላት ከማሳለፍ ተጠንቀቅ፡፡ የሸይጣን መፀዳጃ አትሁን፡፡ በአንድ ወቅት ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ዘንድ እስከሚነጋ ድረስ ሌሊቱን ስለሚተኛ ሰው ተወራ፡፡ ይህኔ እሳቸው እንዲህ አሉ፡- “ያ በጆሮዎቹ ውስጥ ሸይጣን ሽንቱን የሸናበት ሰው ነው!” አሉ፡፡ አልባኒ ሶሒሕ ብለውታል፡፡ [ሶሒሑትተርጊብ ወትተርሂብ፡ 644]
3. የፈጅርን ሶላት ከማሳለፍ ተጠንቀቅ፡፡ ያለበለዚያ የሸይጣን ወጥመድ ሲሳይ ትሆናለህ፡፡ ቀንህን ሙሉ ድብርት ይጫጫንሃል፣ ንቃት ይቀልሃል፡፡ ፈጅር ላይ ተነስቶ ውዱእ አድርጎ ያልሰገደ ሰው ቆሻሻ ነፍስ ይዞ እንደሚያነጋና ስንፍና እንደሚጫጫነው ተናግረዋል፡፡ [ቡኻሪና ሙስሊም]
4. ፈጅርን ስገድ ያለበለዚያ በቀብርህ ውስጥ እስከ እለተ ቂያማ የሚዘልቅ ዘግናኝ ስቃይ ትሰቃያላህ፡፡ ከነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንደተላለፈው አንድ ሰው ተንጋሎ ሌላው ካጠገቡ ቋጥኝ ይዞ በመቆም እራሱን ይደቁሰዋል፡፡ ድንጋዩ ተንከባሎ ሲሄድም እሱን አምጥቶ እስከሚመለስ ድረስ እራሱ እንደነበር ይመለሳል፡፡ ከዚያም እንደ መጀመሪያው ይሰራበታል፡፡ ቂያማ እስከሚቆም ድረስም በዚሁ መልኩ ይቀጥላል፡፡ ይህን በዚህ መልኩ የሚሰቃየውን ሰውየ ምንነት ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ጂብሪል ሲጠይቁት “ይሄ ቁርኣንን ይዞ ፊት የሚነሳው ከግዴታ ሶላትም የሚተኛ ነው” አላቸው፡፡
ወንድሜ ሆይ! ከፈጅር ሶላት አትዘናጋ፡፡ ወቅቱን ጠብቀህ እንድትሰግድ የሚያግዝህን ብልሃትም ተጠቀም፡፡
1. በጊዜ ተኛ፡፡ የምሽት ወሬ ይቅር፡፡ ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ከዒሻ በፊት እንቅልፍ፣ (ከዒሻ) በኋላ ደግሞ ወሬ ይጠሉ ነበር፡፡ [ቡኻሪና ሙስሊም]
2. ቀኑን በወንጀል ከማሳለፍ ተጠንቀቅ፡፡ ወንጀል ከኸይር ስራ ያቅባል፡፡ በሌላ በኩል ለኸይር ስራ ትጋ፡፡ ኢስላማዊ የመኝታ ስርኣቱን ጠብቅ፡፡ የኸይር ስራ አንድ ሽልማቱ ለሌላ ኸይር ስራ መታደል ነውና፡፡
3. ማታ ከመተኛትህ በፊት ለፈጅር ለመነሳት ቁርጠኛ ውሳኔ አድርግ፡፡ ረጅም ጉዞ ወይም አሳሳቢ ጉዳይ ቢኖርብህ ያለ ማንም አጋዥ ምናልባትም ያለአላርም እየነቃህ ለሶላት ሲሆን መዘናጋትህ ስለእውነት ከባድ የሞራል ልሽቀት ነው፡፡
4. ማንቂያ ደወል (አላርም) ተጠቀም፡፡ ምናልባት ሳይታወቅህ አጥፍቶ የመተኛት አጉል ባህሪ ካለብህ ትንሽ ራቅ አድርገህ አስቀምጠው፡፡
5. በሰአቱ ነቅተህ ከተጫጫነህ “ትንሽ ተኛ” ለሚሉ ሸይጣን እና ነፍስያ ሸንጋይ ጉትጎታ እድል አትስጥ፡፡ መነሳትህ ያለውን ዋጋ፣ መተኛትህ ያለውን አደጋ ላፍታ አስብ፡፡ ብትነሳ 50 ዶላር ይሰጣል ቢባል የሚኖርህን ንቃት ቃኝና እራስህን ታዘብ፡፡ ፈርዱ ቀርቶ ትርፍ የሆነችዋ የፈጅር 2 ረከዐ እንኳን ከዱንያ ፀጋ ሁሉ በላጭ እንደሆነች እራስህን አስታውስ፡፡
6. በመልካም የሚያግዝ ጓደኛ ወይም የህይወት አጋር ካለህም እሰየው፣ ተጠቀምበት፡፡
(ኢብኑ ሙነወር፣ ሃምሌ 21/2007)
https://t.me/IbnuMunewor
Darsi duddaluk geyam faxa marak...
👇👇
https://t.me/qafarAfihkitooba
☔️Racbiyya deqsita nagrâ kitaabih darsi.
🎬Shek caydar Saalic(cafizahullaah)
🔰0⃣5⃣
Join us📩
t.me/httpsDiiniKeeAnaakara
☔️Racbiyya deqsita nagrâ kitaabih darsi.
🎬Shek caydar Saalic(cafizahullaah)
🔰0⃣4⃣
Join us📩
t.me/httpsDiiniKeeAnaakara
☔️Racbiyya deqsita nagrâ kitaabih darsi.
🎬Shek caydar Saalic(cafizahullaah)
🔰0⃣3⃣
Join us✍
t.me/httpsDiiniKeeAnaakara
Assalaamu Qaleykum waracmatullaahi wabarakaatuh
☔️Racbiyya deqsita nagrâ kitaabih darsiy logyi magaalal Shek caydar Saalic(cafizahullaah) barisak suge internet(wifi) geynek ahak ciggiilak siinih ruubennok, katattaanam massakaxxaluk sin kassisna!
✍Md Ali
t.me/httpsDiiniKeeAnaakara
🔰0⃣1⃣
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
