Diinii kee Anaakara (Md Ali)
Ir al canal en Telegram
دروس وفتاوي ومحاضرات باللغة العفرية ★Diini barittooy, fatwaa kee Daqwa Qafar afat Tû mabul=> @Anaakar or @acmadxalol
Mostrar más1 617
Suscriptores
-124 horas
+67 días
+2030 días
Archivo de publicaciones
Repost from Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹
እነዚህን ሁለት ባህሪዎች ያየህባት ሴት፤ እንዳታመልጥህ ያዛት።
ሐያእ + ዐቅል
(የሹዓይብ ልጅ → የሙሳ ባለቤት)
||
t.me/MuradTadesse
Repost from 𝐀𝐟𝐚𝐫 𝐊𝐚𝐬𝐬𝐢𝐬 𝐌𝐞𝐝𝐢𝐚
#Maysaxxaga
Birik ciggilte daqwa Sheykh Macammad Awwal cayaat acarra magribik qisha fanah #camzâ masjidil daqwâ barnaamij yan.
Maraaqina hay
Aki baaxol geerí ikkek makkoh akah yamaaten nanu cinna meqaane. Bas dagoom coylasitaay maraaqina.
Repost from 𝐀𝐟𝐚𝐫 𝐊𝐚𝐬𝐬𝐢𝐬 𝐌𝐞𝐝𝐢𝐚
Shekh Macammad Awwal Cayaat (حفظه الله) loogiyak camzâ masjiidil mucaadara (daqwa) acayuk geytima.
Zul cijjak 26/1443
Repost from channel 0
👆👆👆👆👆ይህ ወንድማችን ዓፊፍ መሃመድ ታጅ ይባላል በ2009 ከአአዪ 4ኪሎ ካምፓስ
በከፍተኛ ማእረግ ተማራቂ ነበር።
አሁን ላይ በሱዳን የመስጂድ ኢማምና የሜድስን ተማሪ ነው።
አላህ ይቀበለው ! አላህ ይጨምርለት !
Repost from Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹
የዚህ ልጅ ረዘም ያለ ቂርኣት ስትሉኝ ለነበራችሁ!
||
t.me/MuradTadesse
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
የበዳይ እርግማን
~
አንዳንዱ ሰው እራሱ በድሎ ለበደሉ እጅ የማይሰጡለትን ይራገማል። እንዲህ አይነቱ የበደለኛ ማስፈራሪያ ሊያስጨንቀን አይገባም። ሸይኽ ኢብኑ ዑሠይሚን ረሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ፦
فلا تخف من دُعاء مَن يدعو عليك بِغير حقّ، لأنّ المُسْتجِيب للدّعاء هو اللّه عزّ وجلّ، وأنّهُ سبحانه وتعالى لا ينصر الظّالم أبداً.
"ያለ ሐቅ ዱዓእ ለሚያደርግብህ ሰው ዱዓእ አትፍራ። ምክንያቱም ዱዓእን የሚቀበለው አላህ - ዐዘ ወጀል - ነው። እሱ ደግሞ - ጥራትና ልቅና ይገባውና - ፈፅሞ በዳይን (በበደሉ ላይ) አይረዳም።"
(ሸርሑ ቡለጊል መራም፡ 1/476)
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
ከአገር መፍረስ ባሻገር
~
አገር እንድትፈርስ የሚመኙ፣ አገር ለማፍረስ የሚጥሩ፣ ለአገር አፍራሾች ድጋፍ የሚሰጡ ብዙ ሰዎች አሉ። ወንድሜ ሆይ! እውነት በሃገር መፍረስ የምታተርፍ መስሎህ ነው? ለመሆኑ አገር ሲፈርስ ምን ምን ሊከሰት እንደሚችል አሻግረህ ተመልክተሃል? ወይስ በሆኑ አካላት ላይ ያለህ ጥላቻና ቁጭት በሩቅ እንዳትመለከት ሸፍኖብሃል? ወንድሜ አገር ዳቦ አይደለም ፤ እንደዋዛ ቆራርሰህ በመካፈል አትገላገልም።
* ሃገር ሲፈርስ እልፍ አእላፍ ይፈናቀላሉ። እንኳን አገር ፈርሶ በብሄር ግጭትና ጥቃት ብቻ የሚሊዮኖች ህይወት ተመሰቃቅሏል። ምናልባት አንተ ከሚፈናቀሉት ባትሆን እንኳ ራስህን በነሱ ጫማ ላይ አድርገህ ተመልከት።
* ሃገር ሲፈርስ እልፍ አእላፍ ትዳር ይፈርሳል። ከሌላ ብሄር ጋር የተጋቡ ወገኖቻችን እጅግ ብዙ ናቸው። ይሄ ዘር እየለየ የሚገድል ትውልድ የሚተዋቸው እንዳይመስልህ። ስንት ቤተሰብ እንደሚበተን ተመልከት።
* ሃገር ሲፈርስ እልፍ አእላፍ ንብረት ይወረሳል። እንኳን አገር ፈርሶ ሰላም በመጥፋቱ ብቻ የስንቱ ምስኪን ንብረት በተለያዩ ክልሎች በጉልበተኛ ተነጥቋል!
* ሃገር ሲፈርስ እዚያም እዚህም መቋጫ የሌለው የድንበር ግጭት ይነሳል። በአንድ መንግስት ስር ሆነን ነው በሶማሊና በኦሮሞ የድንበር ግጭት ከሚሊየን በላይ ህዝብ የተፈናቀለው። በአንድ መንግስት ስር ሆነን ነው አፋርና ዒሳ በየጊዜው የሚጋደለው። በአንድ መንግስት ስር ሆነን ነው ዘጠኝ መቶ ሺ አካባቢ የጌዲዎ ህዝብ የተፈናቀለው። በአንድ መንግስት ስር ሆነን ነው የወሎ ኦሮሞና የሸዋ አማራ የሚጋጨው። በአንድ መንግስት ስር ሆነን ነው በደቡብ ክልል የተለያዩ ህዝቦች መካከል ግጭት የሚቀሰቀሰው። በአንድ መንግስት ስር ሆነን ነው "ወሎ ኦሮሞ ነው"፣ "ወልቃይት፣ ደራ፣ በረራ፣ መተከል አማራ ነው" የሚል ጩኸት የምንሰማው፡፡ ሃገር ከፈረሰ እነዚህ ጩኸቶች ዛሬ ከምናየው በላይ ሚሊዮኖችን የሚበላ እሳት ይቀሰቅሳሉ።
* ሃገር ሲፈርስ እልፍ አእላፍ ነፍስ ይጠፋል። ከላይ የተጠቀሱት በሙሉ መጨረሻቸው እልቂት ነው።
* ምናልባት መልኩ ይቀየር ካልሆነ በስተቀር በሃገር መፍረስ ጭቆና የሚቀር፣ ለድሃ ቀን የሚወጣ እንዳይመስልህ። ወላሂ! ዘር እየለየ፣ ሃይማኖት እየመረጠ በሚገድል ቡድን፣ ከርሱን በሚያስቀድም ፖለቲከኛ መቼም ፍትህና ነፃነት አታገኝም።
የሚሻለው በጋራ ለሰላምና ለፍትህ መጣር ነው። መፍትሄው እንደ ህዝብ ከገጠመን የስነ ምግባር ዝቅጠት ለመውጣት ተባብሮ መሥራት ነው። ችግራችን ስር የሰደደ ነው። ችግራችን በማህበረሰብ ደረጃ የተንሰራፋ ነው። ስለ መንግስት ችግር ጧት ማታ ማውራቱን እንደ ንቃት ቆጥረን እራሳችንን እየሸወድን እንጂ እንደ ህዝብ መተዛዘናችን ሳስቶ መጨካከን ነግሶብናልኮ።
~ በየገበያው የሚያጭበረብረው፣ በየተቋሙ ህዝብ የሚያጉላላው፣ ... ሁሉ ምንም ስቅ ሳይለው ስለ ፍትህ እየወሸከተ ነው።
~ ለብዙዎች ከትምህርት ገበታ መራቅ ሰበብ የሚሆነው፣ ዘርና ሃይማኖት እየለየ ተማሪዎቹን የሚያከላፍተው አስተማሪ ምንም ሳያፍር ስለ ፍትህና ርትእ እየጮኸ ነው።
~ ታካሚዎቹን ፊቱን አጨፍግጎ የሚያስተናግደው፣ በግዴለሽነት የሰው ነፍስ ላይ የሚቀልደው፣ ለርካሽ ጥቅም ሲል የማይገናኝ ምርመራ እያዘዘ ደካማ ወገኑ ላይ ጭካኔ የሚፈፅመው ሃኪም እኮ ነው ስለ ፍትህ የሚጮኸው!
~ የተበላሸ ምግብ፣ ጊዜው ያለፈበት መድሃኒት፣ ፎርጂድ እቃ፣ የተጭበረበረ ምርት፣ ... የሚሸጠው ነጋዴ እኮ ነው "መስራት አቃተን" እያለ የሚያለቅሰው።
~ ፍትህ በገንዘብ የሚሸጠው፣ ከሌባ ጋር ተቀናጅቶ የሚሰራው፣ እምነትና ብሄር እየመረጠ ፍትህ የሚቀብረው ዳኛና ፖሊስ እኮ ነው ስለ ፍትህ የሚዘፍነው።
~ ሚሊዮኖች የወጡበትን መሬት ሶስት አራት ካርታ ሰርቶ የሚቸበችበው ሰራተኛ፣ የሚሊዮኖችን ውሃና መብራት እየቆረጠ ሺ ጊዜ ብር እየተቀበለ የሚቀጥለው ሌባ እኮ ነው ስለ ፍትህና ስለ ነፃነት የሚለፍፈው።
~ መንገዶችንና ህዝባዊ ተቋማትን ከደረጃ በታች እየሰራ በሀገር በወገኑ ላይ የሚቆምረው እኮ ነው ለሀገር ለወገኑ ተቆርቋሪ መስሎ የሚፈተፈተው።
~ መኪናና ሞተር ሳይክል አዘጋጃቶ፣ አንድ ላምስት ተደራጅቶ የሚዘርፈው፣ ህፃናት እያፈነ የሚወስደውኮ ነው እኩል ስለ ፍትህ የሚያወራው!
~ የሁለት ቀን ጨቅላ፣ የ70 አመት አዛውንት፣ አቅመ ደካማ ሴቶችን ሳይቀር የሚገድለው እኮ ነው የነፃነት ታጋይ የሚባለው።
እስኪ በየትኛው ዘርፍ ነው የሚነሳ ጥሩ ነገር ያለን? ፖለቲከኞቹ የኛው ነፀብራቆች ናቸው። እኛኑ ነው የሚመስሉት። ከኛው የወጡ እንጂ ከሌላ ፕላኔት የመጡ አይደሉም። ክፋታቸው ክፍታችን፣ ንቅዘታቸው ንቅዘታችን ነው።
እንደ ህዝብ በዚህ ደረጃ መልካሞች የመነመኑ ከሆኑ እንዴት ነው ፍትህና እፎይታ የምናገኘው? በቅድሚያ በራሳችን ላይ ሰፊ ስራ መስራት ይጠበቅብናል። ወደተነሳሁበት ስመለስ፣ ስግብግብ ስሜታችን እየጋረደን፣ ቁንፅል አመልካከታችን እየሸወደን እንጂ በርግጠኝነት በሃገር መፍረስ እንደ ህዝብ ከሳሪዎች እንጂ አትራፊዎች አይደለንም። ስለዚህ ደግመን ደጋግመን ልንመለከት፣ ከጥፋት ልንርቅ፣ ለአጥፊዎች ጉልበት ከመሆንም ልንጠነቀቅ ይገባል። ጥፋትን ማስቆም ባንችል እንኳ ቢያንስ ተጋሪ ባለመሆን የራሳችንን ድርሻ ልንወጣ ይገባል።
=
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ልብህ ላይ ምን እየዘራህ ነው?
~
ኢማሙ ሻፊዒይ ረሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ፦
"ልቦች የምላስ እርሻዎች ናቸው። መልካም ንግግር ዝራባቸው። ሙሉውን ባያበቅሉ እንኳ ከፊሉን ያበቅላሉ።"
(መናቂቡ ሻፊዒይ፣ በይሀቂይ፡ 2/76)
=
https://t.me/IbnuMunewor
(Mp3) እውን «ኢስተዋ» በ«ኢስተውላ» ይተረጎማልን?
በሸይኽ ኢልያስ አህመድ || NesihaTv
አላህ ስለራሱ የገለፀውን ኢስቲዋእ (ከዐርሹ በላይ ከፍ ያለ መሆን) በ«ኢስቲይላእ» (መቆጣጠር፣ መሾም) መተርጎም በሰለፎች ሙሉ ድምፅ የተኮነኑት የጀህሚያዎችና የሙዕተዚላዎች ፈጠራ እንደሆነ ከመሰከሩ ቀደምት ሊቃውንት መካከል ኢብኑ ኹዘይማ፣ ኢብኑ ቁተይባ እና አቡ'ል‐ሐሰን አል‐አሽዐሪይ ይጠቀሳሉ
ይህ ትርጓሜ ውድቅ መሆኑ በአጭሩ የተብራራበት ትምህርት👇
https://youtu.be/2BtH6CDoCwk
ነሲሓ ቲቪ...
ኢስላማዊ እውቀት ለሁሉም!!
@ustazilyas
Repost from 𝐀𝐟𝐚𝐫 𝐊𝐚𝐬𝐬𝐢𝐬 𝐌𝐞𝐝𝐢𝐚
#Atu_maca_abe_raxxe...?
Yallih farmoytih (q.s.w) cadiis gaaboysak sugeeh, saciicik yan xaaguy maqar leh yani qaalam gudduysuh kaxxam macaleeh, yalli (s.w) gabal akak biciseh yan Macammad ibnu ismaaqiil (imaamul bukhaari) yalli kaah racmatay) Ama qilmi goraanah elle gaxaah, yallih farmoytih cadaysiy saciicik tanih goraana elle gexah yan baaxol mangoh tan tekkookah amo awquk yenem kee baxaa baxsa le taqabi kaa gifak yeneemih kassittot yaabak yen.
Too kassitto kaxxam mangooh qajaa-ibik tan waka, Ayrok teena dumak akah abah yan innah saciicik yan cadiisih goraanah baaxok teena gexam faxak baddi markabat feere. Tokkel kaxxam suge kalah inki num kaat xayyowwa iyyeh kaa walalise. Bukhaari ulim kaak maaqurinnaay, baguuk kaa yaabise. Too yaabak addat inki caagid kaah warse. Maaluk alfi (1000) diinar sakayih lem kaah waese.
Too yaalo gexaak aseenik sarra xiineenih elle maacisen ikkel kaxxa deero edde hee. Maca tekke? Inte sinam "alfi diinaar yok baye" iyye. Tokkel sugeh yan mari itta maqayeeh, "tawak ta num iyyam macaay?" Ittak iyyen.
A num aham akah iyyaamat radeh yan imaamul bukhaari luk sugeh yan alfi dirham badat sakuyya hee. Taaxige num weeqah hayya hee. Baddi markabat taamittah tan taama abeenit weeqat ayti kalla ken hee wak markabat yanih yan marat fettesha akah takkay iyyen.
Inkih taftiish keenit aben wak ulim waytinte. Toysa wokket taamitta taama abeenit "gabah badaa badsah abtem ikkah kok baye maali mayanay nee duquurussuh abteemi" kaak iyyen.
Dagoom sugga iyyen wak woo num wacarriy maliiy, imaamul bukhaarit xayyowwa iyyeh "a yoh warisse maaluk maca abte?" Kaak iyye. "Badat qidem" kaah warse. "Tagid yakke maalu badat qidda hayteh foyyah mannal akak raqtu dudde?" Kaak iyye.
Imaam Al bukhaari iyyemi: "Anu Yallih farmoytih (s.q.w) cadiis gaaboysa num kinniyo. Toysa kú innah yan maray umaaliteh yanih sabbatah migaq yok yaameemik lakqok foyyah raaqam doorite" kaak iyye.
Ahak maca baritte...? Annah tanim kot boodinnay maca abak ten?
Cikmat le marih taama qajiibi. Bukhaari abeh cabe taama asaaku qaalamal aaxige waa num mayan. Kaaduk kay gide maadise num mayan. Toh akah tekkem ikh-laas kee aamantissol abak yenem kinniimi tascassem.
Kaxxa gaddaliinok baacoyta tikka akah iyyeeh, bar kee loqo inkih akah taamiteeh, gidbaabinay yaamineenim xiqe waana kaat booadak abe taama neh daabiseh cabem (yalli kaah racmatay)
Repost from Abdul Aziz Nur
መስጂድ አንዱ ስልኩ ሲጠራ ዘፈን ነበርና ደንግጦ ሰላቱን አቋርጦ ስልኩን ካጠፋ በኋላ ወደ ሰላት ተመለሰ። የዘመኑ በክላሲካል የታጀቡ የአላህ እና የመለእክተኛውን ስም ከማንሳት ውጭ በምንም መልኩ ከዘፈን የማይለዩ ነሺዳዋች ሰላት ላይ ሆነን ቢጠራብን ግን ምንም የማይመስለን ኢማናችን የጨመረ የሚመስለን ብዙ ነን። ሀራም ብለን የተውነው ዘፈን ግጥማቸው የኢስላምን መልእክት አላስተላለፈም ብለን አደለም። አንድ ዘፋኝ ስለ ረሱል ሲዘፍን ነሺዳ የተፈቀደ ሊባልለት ስለ ፍቅር ሲዘፍን የተከለከለ ሀራም የሚሆንበት የተወዘጋገበ ሸሪኣ የለም። መርሆው የተቀመጠው መለኮታዊው ህግ ነው። አንድ ዘፈን ዘፈን ካስባሉት ነገሮች አንዱ የሙዚቃ መሳሪያ ስለገባበት ነው። ሙዚቃ መሳሪያ የገባበት ማንኛውም ነገር ግጥሙ ከርክሰት አይጠብቀውም።
🍂 t.me/zizuQ
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
በታላቁ ፍንዳታ ውስጥ እንዲህ አይነት ሂደትና ቅደም ተከተል የለም። ፍንዳታ ውስጥ ምን አይነት ስርአትና ቅደም ተከተል ይኖራል? ደግሞም ቀደም ብዬ እንደጠቀስኩት በሳይንሱ ባዶ ህዋ እንጂ ሰማይ የሚባል በቁጥር 7 የሆነ አካል የለም። በኢስላም ግን ያለ ምሰሶ አላህ በቁድራው ያንጣለላቸው 7 ግዙፍ ሰማያት አሉ። የላቀው አላህ እንዲህ ይላል:-
{ خَلَقَ ٱلسَّمَـٰوَ ٰتِ بِغَیۡرِ عَمَدࣲ تَرَوۡنَهَاۖ}
{ሰማያትን ያለምታዩዋቸው አዕማድ (ምሰሶዎች) ፈጠረ።} [ሉቅማን: 10]
{ ٱللَّهُ ٱلَّذِی رَفَعَ ٱلسَّمَـٰوَ ٰتِ بِغَیۡرِ عَمَدࣲ تَرَوۡنَهَاۖ}
{አላህ ያ ሰማያትን የምታዩዋት አዕማድ ሳትኖር ያነሳት ነው።} [ረዕድ: 2]
እነዚህን እውነቶች ይዘን ስንመለከት በአንዳንዶች የሚደረገው የቁርኣን አንቀፆችን ታይቶና ተሰምቶ በማይታወቅ መልኩ እየተረጎሙ "ታላቁን ፍንዳታ" ለማስለም መንደፋደፍ ተሸናፊ ስነ ልቦና የፈጠረው የከሸፈ ልፋት ነው።
ደግሞስ በቁርኣን ውስጥ የተጠቀሰው ሰማይና ምድር ቀድሞ የተጣበቁ ነበሩ ማለት እነሱ እንደሚሉት 'The whole universe is an infinite mass and nearly a zero volume matter ነበር' ማለት አይደለም። ሰዎቹ ያለ ጥርጥር ቁርኣንን ያላግባብ እየመነዘሩ ነው። የቁርኣኑ አንቀፅ የሚያወራው ስለ ሰማያትና ምድር ብቻ ነው። እንዲሁ ከbig bang ጋር ለማዛመድ ነው ሌሎች ፍጥረታትን አብረው የሚጨፈልቁት።
ከሰማያትና ምድር መፈጠር በፊት ጊዜና ቦታ (time & space) አልነበረም ማለት ግልፅ ቅጥፈት ነው። ይህንን ነው ወደ ቁርኣን የምታስጠጉት?
በነገራችን ላይ "ታላቁ ፍንዳታ" /The big bang/ ከበርካታ ሳይንቲስቶች ጠንካራ ትችት አስተናግዷል። የምሁራን ኢጅማዕ አለበት የሚለው ጩኸት ነጭ ውሸት ነው። ይህንን እውነታ ሌላው ሁሉ ቢቀር ጉግልን በስሱ የፈተሸም የሚያረጋግጠው ነው። ሲጀመር እነሱም ዘንድ ንድፈ ሃሳብ (theory) እንጂ ያለቀለት እውነታ አይደለም። እንዳልኩት ይሄ "ዐቂዳ" መሰረተ-ቢስ ንድፈ ሃሳብ እንደሆነ የተናገሩ ብዙ ሳይንቲስቶች አሉ። ለምሳሌ ያክል Halton Arpን እንደ ምሳሌ መውሰድ ይቻላል። በሳይንሱ ዓለም ስሙ የገነነ፣ ብዙ ዓለማቀፍ ሽልማቶችን ያገኘ ነው። ከመሆኑም ጋር የ"ታላቁ ፍንዳታ" አከርካሪ ላይ ደግሞ ደጋግሞ ብርቱ ምት አሳርፏል። ሌሎችም ብዙ አሉ። ይህን የማነሳው ሳይንሳዊ "ግኝቶችን" እንደ ወረዱ ከመቀበል፣ የተረጋገጡ እውነታዎች አድርጎ ከማመን፣ አልፎም ከቁርኣን ጋር ለማዛመድ ከመሞከር በፊት ቢያንስ እዚያው እነሱው ሰፈር ስላሉ ሙግቶች ዳሰሳ ብናደርግ መልካም እንደሆነ ለመጠቆም ነው።
አንዳንዶች በሳይንስ ስም የሚቀርቡ ሙግቶችን ሳያኝኩ ለመዋጥ የፈጠኑ ናቸው። እነዚህ "ግኝቶች" በሚነቀፉ ጊዜ ይረበሻሉ። ጭንቀታቸው ይገባኛል። እነዚህን "ግኝቶች" ስለነቀፍን ሃይማኖታችን አደጋ ላይ የሚወድቅ እየመሰላቸው ነው። ይሄ የዋህነት ነው። በመጨረሻም የምለው:-
1ኛ፦ ሃይማኖታችን ከተረጋገጡ እውነታዎች ጋር ፈፅሞ አይጋጭም። ስለዚህ ስጋት አይግባን። የሚጋጭበት ቦታ ከገጠመን ወይ "ግኝቱ" fact አይደለም። ወይ ሸሪዐዊ መረጃዎችን በትክክል አልተረዳንም።
2ኛ፦ አንድ ግኝት ከተገኘ በቃ ተገኘ። ግኝት በተገኘ ቁጥር "ቁርኣንም ውስጥ ተጠቅሷልኮ" እያሉ አጉል መዘባረቅ አይገባም። የግድ እያንዳንዱ ግኝት ቁርኣን ውስጥ እንዲኖር አይጠበቅም። ቁርኣንኮ የሳይንሳዊ እውነታዎች መዘርዘሪያ መፅሀፍ አይደለም። ይሄ ቀርቶ ሶላት፣ ፆም፣ ሐጅ፣ ... ዒባዳዎች እንኳ ሙሉና ዝርዝር አፈፃፀማቸው ቁርኣን ውስጥ የለም።
3ኛ:- በሳይንስ ስም የሚነገሩ "ግኝቶች" ሁሉ ያለቁና የተረጋገጡ እውነቶች አይደሉም። ስንት "ግኝቶች" በዘመናት ውስጥ ተቀይረዋል? እነሱ በቀየሩ ቁጥር ተፍሲራችንን ልንቀያይር ነው ወይ?
4ኛ:- በሳይንስ ስም የሚነገሩ "ግኝቶች" ሲነቀፉ አርካኑል ኢስላም የተነኩ ያህል አንደግጥ። የሰዎች የምርምር ውጤቶች እንጂ መለኮታዊ ወሕይ አይደሉምኮ! እዚያው ከጎናቸው ብዙ የሚነቅፉ ሳይንቲስቶች ባሉበት ከመምህሩ ደቀመዝሙሩ ሲብስ ደስ አይልም።
5ኛ፦ ከአንዳንድ ሳይንሳዊ "ግኝቶች" ጀርባ ሰዎችን ከሃይማኖት ለማራቅ የታሰቡ ያደፈጡ ሴራዎች ይኖራሉ። ችኩል ድምዳሜ ከመስራት በፊት ረጋ ብሎ ዓሊሞች ምን እንደሚሉ ማየት ይገባል። የ"ታላቁ ፍንዳታ" "ግኝት" አላማም በፈጣሪ መኖር ከነ ጭራሹ የማያምኑ ሰዎች "እና ፈጣሪ ከሌለ ፍጥረተ ዓለሙ እንዴት ተገኘ?" ለሚለው ፈታኝ ጥያቄ መሸወጃ ሆኖ የቀረበ ሰይጣናዊ እሳቤ ነው። ስለዚህ ጥንቃቄ ይኑረን።
=
(ኢብኑ ሙነወር፣ ሐምሌ 7/2014)
የቴሌግራም ቻናል:-
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
"ታላቁን ፍንዳታ" - የማስለም ግብግብ
===============
ሰሞኑን የአሜሪካው የህዋ ሳይንስ ምርምር ተቋም (NASA) በጀምስ ዌብ ቴሌስኮፕ የተወሰዱ የህዋ ፎቶዎች ናቸው በማለት ምስሎችን መልቀቁን ተከትሎ በሳይንቲስቶች የሚቀርበውን "ታላቁ ፍንዳታ" (The big bang) ላይ የተመሰረተውን የፍጥረተ አለም አጀማመር ንድፈ ሃሳብ ቁርኣን ውስጥ እንደተጠቀሰ አድርገው በቁርኣን አንቀፆች ላይ ደፋር ትንታኔ የሚሰጡ ሰዎችን እያየን ነው። ለዚህም መነሻ የሚያደርጉት ተከታዩዋን አንቀፅ ነው:-
(أَوَلَمْ يَرَ الَّذِينَ كَفَرُوا أَنَّ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ كَانَتَا رَتْقًا فَفَتَقْنَاهُمَا)
{እነዚያም የካዱት ሰማያትና ምድር የተጣበቁ የነበሩና የለያየናቸው መሆናችንን አያውቁምን?} [አንቢያእ: 30]
የቁርኣኑን መልእክት ያዙና ቀጥሎ ያለውን ሃሳብ ታዘቡ እስኪ።
<<በጥቅሉ ሰማይ የሚለው ቃል Space/ህዋን እና Astronomical object's/ ስነ-ፈለካዊ ቁስ አካላት የሚለውን ይወክልልናል።
ምድር የሚለው ቃልም Galaxy/የከዋክብቶች ክምችት እና Nebula/ድብዝ ስብስብ ከዋክብት መሬትን ጨምሮ ለተዋቀሩበት Matter መገለጫ ነው።>>
ይሄንን እርስ በርሱ የሚዋጋ የተቀዣበረ ትርጓሜ ተመልከቱ። ይሄ እጅግ አሳፋሪ ትንታኔ ነው፡፡ አንድ ነገር ልጠይቅ። በአንቀጿ ውስጥ የተጠቀሰው ምድር (الْأَرْضَ) ትርጓሜው ይሄ ነው? በታሪክ የትኛው የኢስላም ሙፈሲር ነው Galaxy/የከዋክብቶች ክምችት እና Nebula/ድብዝ ስብስብ ከዋክብት ሁሉ ምድር ተብሎ ይጠራል ያለው? ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን!
ይሄ ብቻም አይደለም የታላቁ ፍንዳታ አማኞች ዘንድ ሰማይ ማለት ህዋ / Space እንጂ እራሱን የቻለ ግዙፍ አካል አይደለም። ኢስላማዊው ግንዛቤ ይሄ እንዳልሆነ ሁሉም የሚያውቀው ነው። ለምሳሌ ያህል እነዚህ ተሸናፊዎች ያላግባብ ከሚመነዝሯት አንቀፅ አለፍ ብሎ እንዲህ የሚል እናገኛለን፦
{ وَجَعَلۡنَا ٱلسَّمَاۤءَ سَقۡفࣰا مَّحۡفُوظࣰاۖ }
{ሰማይንም (ከመውደቅ) የተጠበቀ ጣራ አደረግን፡፡} [አንቢያእ: 32]
አያችሁ? ሰማይ እራሱን የቻለ ግዙፍ አካል እንጂ እነሱ እንደሚረዱት ባዶ ህዋ አይደለም። በዚያ ላይ በቁጥር 7 እንደሆኑ ነግሮናል።
{ ٱللَّهُ ٱلَّذِی خَلَقَ سَبۡعَ سَمَـٰوَ ٰتࣲ وَمِنَ ٱلۡأَرۡضِ مِثۡلَهُنَّۖ}
{አላህ ያ ሰባትን ሰማያት የፈጠረ ነው፡፡ ከምድርም እንዲሁ መሰላቸውን (ፈጥሮአል)።} [ጦላቅ: 12]
ሰማይንም ምድርንም ቁርኣን ውስጥ ከተረጋገጠው አውጥተን ከተረጎምን በምን አግባብ ነው ለዚህ አይነት ቅብዥርዥር ያለ 'ዐቂዳ' የቁርኣን አንቀጾችን የምንጠቀመው?
የ"ታላቁ ፍንዳታ" አማኞች ዘንድ የፍጥረተ ዓለሙ መነሻ የአንዲት በአይን እንኳ የማትታይ ከatom ያነሰች እጅግ ደቂቅ ነገር ነች። ይቺ ደቂቅ ነገር እጅግ በከፍተኛ ሁኔታ ታምቃ ኖራ ስትፈነዳ ጊዜ ይሄ ግዙፍ ፍጥረተ ዓለም ተገኘ ይላሉ። ከዚች ደቃቅ ነገር ምን ምን ተገኘ ይላሉ መሰላችሁ?
- ብዛታቸው በቁጥር የማይገለፅ እልቆ መሳፍርት (infinite) ፍጥረተ ዓለሞች ተገኙ።
- ከነዚህ ውስጥ አንዱ ፍጥረተ ዓለም (univers) ብቻ በቢሊየን የሚቆጠሩ ጋላክሲዎች አሉት።
- አንዱ ጋላክሲ ብቻ (Milky Way የሚባለው) ፀሐይን፣ በርካታ ፕላኔቶችንና በመቶ ቢሊዮን የሚቆጠሩ ከዋክብት ይዟል ይላሉ።
ይህን ሁሉ ጉድ ነው ከአንዲት ነጥብ እንኳ ከማታክል ነገር ፍንዳታ ተነስቶ ተፈጠረ የሚሉት። ከዚህ ፍንዳታ በኋላ ነው ጊዜና ቦታ (time & space) ተገኘ የሚሉት። ለዚህ ተረት (ኹራፋ) ነው እንግዲህ "ሰማያትና ምድር የተጣበቁ ነበሩ፤ ለያየናቸው" የሚለውን የቁርኣን አንቀፅ የሚጠቅሱት። ሱብሓነላህ! ይሄ ምን የሚሉት ድፍረት ነው?
አንዳንዶች ይሄ አካሄዳቸው ሲነቀፍ "እኛ ከቁርኣን ጋር ያዛመድነው የተረጋገጠን ሳይንሳዊ እውነታ እንጂ፣ ያልተረጋገጠን ንድፈ ሃሳብ አይደለም" ይላሉ። የቱ ነው የተረጋገጠው ሐቅ?
* "ፍጥረተ-ዓለሙ ሁሉ በአንድነት እምቅ ብሎ የተጠቀለለ፣ የታጨቀ፣ የታፈገ አንዲት ትንሽ እኑስ ቅንጣት ነበር" የሚለው ነው የተረጋገጠው ሐቅ?
* "ይህ እኑስ በውስጡ ምንም አይነት አተም መዋቅርም ሆነ ቅጥ አልነበረውም" ማለት ነው የተረጋገጠው ሐቅ?
* ይሄ ግዙፍ ዓለም፣ ይሄ ፍፁም የሆነ የፈለክ እንቅስቃሴ ከዚህ ደቂቅ ነገር ድንገቴ ፍንዳታ የተገኘ ነው ማለት ነው የተረጋገጠው ሐቅ?
* "ከዛሬ 13.78 ቢሊዮን ዓመት በፊት፣ ይህ ጥንጥ ጠጣር ነገር ድንገት ፈንድቶ በመበታተኑ ህዋ እና አተሞች ተፈጠሩ። አተሞቹ እየጓጎሉ ኮከቦችን ፈጠሩ" ማለት ነው የተረጋገጠው ሐቅ?
* "ከፍንዳታው በኋላ የተፈጠረው ዓለም እየሰፋና እየቀዘቀዘ በመሄዱ እንደ መሬት ያሉ ፈለኮች (ፕላኔቶች) በሂደት ቀስ እያሉ ተፈጠሩ" ማለት ነው የተረጋገጠው ሐቅ?
* "The black hole has an infinite density; since its volume is zero, ... የሚለው መላምት ነው የተረጋገጠው ሐቅ?
ቁርኣን ውስጥ አግኝተኸው ነው የተረጋገጠ ሐቅ ነው የምትለው? ነው ወይስ በሳይንስ ስም ስለቀረበ ብቻ የነሱን ንግግር ባይገባንም እንደ ወሕይ እንመን? ከመላምት ባለፈ የትኛው መረጃ ቀርቦ ነው የተረጋገጠ ሐቅ ነው የሚባለው? ወንድሜ ሆይ! በአላህ ላይ ያለ እውቀት መናገር ከባድ ጥፋት ነው።
ለነዚህ ሰዎች የምንላቸው የምትጠቅሱት አንቀፅ ውስጥ ሰማያትና ምድር የተጣበቁ ነበሩ አለ እንጂ የፍጥረት መጀመሪያ ይሄ ነው አይልም። እንዲያውም ከነሱ በፊት ሌሎች ፍጥረቶች እንደቀደሙ ነው ቁርኣን የሚጠቁመው። ሰማያትና ምድር ከመፈጠራቸው በፊት የአረሕማን ዐርሽ ነበር። ዐርሹ በውሃ ላይ ነበር። የላቀው አላህ እንዲህ ይላል:-
{وَهُوَ ٱلَّذِی خَلَقَ ٱلسَّمَـٰوَ ٰتِ وَٱلۡأَرۡضَ فِی سِتَّةِ أَیَّامࣲ وَكَانَ عَرۡشُهُۥ عَلَى ٱلۡمَاۤءِ}
{እርሱም ያ ሰማያትንና ምድርን በስድስት ቀኖች ውስጥ የፈጠረ ነው፡፡ ዐርሹም በውሃ ላይ ነበር፡፡} [ሁድ: 7]
ከዚህ በኋላ ነው ሰማያትና ምድር የተፈጠሩት። በመጀመሪያ ምድር ተፈጠረች። ቀጥሎ ደግሞ ሰማያት። የላቀው አላህ እንዲህ ይላል:-
{هُوَ ٱلَّذِی خَلَقَ لَكُم مَّا فِی ٱلۡأَرۡضِ جَمِیعࣰا ثُمَّ ٱسۡتَوَىٰۤ إِلَى ٱلسَّمَاۤءِ فَسَوَّىٰهُنَّ سَبۡعَ سَمَـٰوَ ٰتࣲۚ}
{እርሱ ያ በምድር ያለውን ሁሉ ለእናንተ የፈጠረ ነው፡፡ ከዚያም ወደ ሰማይ አሰበ፤ ሰባት ሰማያትም አደረጋቸው፡፡} [በቀራህ: 29]
ፀሐይ፣ ጨረቃና ከዋክብት የተፈጠሩት ከዚህ በኋላ ነው። የላቀው አላህ እንዲህ ይላል:-
{ فَقَضَىٰهُنَّ سَبۡعَ سَمَـٰوَاتࣲ فِی یَوۡمَیۡنِ وَأَوۡحَىٰ فِی كُلِّ سَمَاۤءٍ أَمۡرَهَاۚ وَزَیَّنَّا ٱلسَّمَاۤءَ ٱلدُّنۡیَا بِمَصَـٰبِیحَ}
{በሁለት ቀኖችም ውስጥ ሰባት ሰማያት አደረጋቸው፡፡ በሰማይቱም ሁሉ ነገሯን አዘጋጀ፡፡ ቅርቢቱንም ሰማይ በመብራቶች አጌጥን፡፡} [ፉሲለት: 12]
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
