Diinii kee Anaakara (Md Ali)
Ir al canal en Telegram
دروس وفتاوي ومحاضرات باللغة العفرية ★Diini barittooy, fatwaa kee Daqwa Qafar afat Tû mabul=> @Anaakar or @acmadxalol
Mostrar más1 615
Suscriptores
-124 horas
+67 días
+2030 días
Archivo de publicaciones
Repost from Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹
የዘካህ ህግጋት አጭር ማብራሪያ
ይህ ርዕሰ ጉዳይ በተለይ ሰሞኑን ብዙዎች ስለምትፈልጉት አንብቡት። 35 ገፅ ነው
በሸይኽ ኢልያስ አሕመድ
[2001 E.C ላይ የተጻፈ]
||
https://t.me/MuradTadesse/18671
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ፆም #የማያበላሹ ነገሮች
~ ~~
ቀጥሎ የተዘረዘሩት ፆም አያጠፉም።
1- የህክምና መርፌ መወጋት፣
2- ምግብ መቅመስ (ከተዋጠ ፆም ያጠፋል)፣
3- የአይን ጠብታ፣ ኩል መኳል፣ የጆሮ ጠብታ፣ የአፍንጫ ጠብታ፣
4- አካልን ለማቀዝቀዝ መታጠብ፣
5- የሽቶ ወይም የኹር ሽታ፣
6- መፋቂያ በማንኛውም ሰዓት መጠቀም፣
7- ዋገምት/ሒጃማ (ሚዛን በሚደፋ አቋም ፆም አያበላሽም)፣
8- ማስታወክ ወይም ማስመለስ (ሚዛን በሚደፋ አቋም ፆም አያበላሽም።)
9- ለምርመራ ደም መስጠት፣ ደም መለገስ፣
10- በፊንጢጣ የሚገባ መድሃኒት፣
11- ዝንብ፣ አቧራ ፣ ... ድንገት መግባት፣
12- ምራቅን መዋጥ፣
13- የአስም ህመምተኞች በአፍንጫ የሚጠቀሙት Sprayer
14- ለምርመራ ወይም ለሌላ በብልት ወይም በፈንጢጣ የሚገቡ ነገሮች፣ ካቲተር፣ ሉፕ፣
15- የማደንዘዣ መድሃኒቶች፣ ኦክስጂን፣
16- በአፍ የሚገቡ እንደ ኢንዶስኮፒ ያሉ መመርመሪያዎች (ፈሳሽ ወይም ሌላ ነገር ይዘው የሚገቡ ካልሆኑ)
17- ጆሮ ማሳጠብ፣ ጥርስ ማስነቀል፣ ጥርስ ማሳጠብ (በፆም ወቅት ባይደረግ የተሻለ ነው)፣
18- ፆም የሚያበላሹ ነገሮችን ተገዶ መፈፀም
እነዚህ ነገሮች በሙሉ ፆም አያበላሹም።
=
የቴሌግራም ቻናል :-
t.me/IbnuMunewor
Repost from Kassis Faage
Rufto le xaagu
Away Addat Akak nan Alsak yamaate Acaadah qafar qaasima samarak Agat kee Agattiinah handagal kaxxa daqwâ borogram yanim sin Aytit hayna
Ta racal daqwa neh Abtu waytam
1.shekh m.d Awwal cayaat
2.d.r m.d cuseen
3.shekh ilyaas Ahmed
4.ustaaz m.d casan
5.d.r saqid qali haaruun
6.ዶ/ር ሠመሃር ተክሌ
Yalli muquk nee sugusay edde Angali nee haay
t.me/NekbaritaayNeebarisa
500 alfik daga takke sayyo irô baaxo, axcih saquudiya fan safrisaanamih bicaabicih gexso tanim aabbe!
Say mari kaxxam xagroo kee hanaawi faxa mara kinni.
Say mari Umaah meqem ken suumuttaamih sabbitih, tohuk kaaduk amô wagitto elle xayi gabat keenik yakkem faxximta!
Tonna hinnay, ken aaxige waah, ken xaleena aaxige waah yan marih gabat radeenik, keenit faxaanamah keenit yantifiqeenim akke waytek, keenih aban caddo malon, ken xaleenah aban caddi malon.
Say num buxak tewqek, edde sooleh uma aracat soltaah, wakliseh uma mara waklissaah, faxxiime sinni marih gabat raddam bictah !!
Tet elle xayi(buxa mari) teetik aba caddiiy, hanaawii kee amô wagitto boolaluk raqta!
Ayduma qafar afâ baaxo fan kaxxam safare wayta way , safra maral obtam abbukuuy, abaluk asna!
Away safar siitingey lih yekkem muslimiin doolata(saquudiya) takke way taqabi raq mali, sarra annah tan saamitte koros dowalih katuk tamaatem bictah, away nuble safar gorrisnam raq matalla !
Kaxxa taqabih tanim kaaduk , away sayyo kah ruubaanam Alsi qasbi edde geyaanam akke waytek #naqoosinna celta buxah addah taamaay, hotel kee tonnah tan taama ikkal, ixxiga kak geyaanaah, sinnih misinkaca currik elle dadlisaanah, tqmsiisaanam xiqan curriyyatle taama hinba.
Kalah Naaxigem faxxintam, qafar sayyo diwah waa maray, ni sayyo gorrisa mangoh, kah gorrisaanam kaaduk, qafar agabut xalak, qafar addat gersi diinitte kah cultannih ikraaro kinni(saquudiyal diini caagidil bohoy mannu)
Toh kee kalah taniimiy cubbuseh meqe mangoomih taagah, taagah, ta caagid nagay cubbudnam faxxinta!
✍Md Ali
https://t.me/httpsDiiniKeeAnaakara
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ሶደቃ
~
በረመዷን ከሚወደዱ ነገሮች ውስጥ አንዱ ሶደቃ ነው። የሶደቃ መስኩ ብዙ ነው። ለምሳሌ፦
* ምስኪኖችን ማብላት፣ መርዳት
* ወላጆችን፣ ዘመዶችን፣ ጎረቤቶችን ማገዝ
* ማስፈጠር (በተለይ ችግረኞችን፣ በየመጠለያው የወደቁ ተፈናቃዮችን፣ ...)፣
* ችግር ላለባቸው ሰዎች ስንሸጥ ከዋጋው ለቀቅ፣ ከእቃው መርረቅ ማድረግ፣
* ችግር ካለባቸው ሰዎች ስንገዛ ደግሞ በምንችለው መልኩ ማገዝ፣
* ሃኪሞችና ሃኪም ቤቶች ደካማ ታካሚዎችን ቢያግዙ፣ በነፃ ወይም በቅናሽ ቢያክሙ ትልቅ ሶደቃ ነው።
* ትራንስፖርት ላይ ለደካሞች መክፈል፣
* መኪና ያላችሁ ስጋት እስከሌለ ድረስ ሰዎችን ማሳፈር (በተለይ ደግሞ ነፍሰ ጡር የሆኑ፣ ልጅ የያዙ እናቶችን፣ አቅመ ደካሞችን፣ ... እያዩ ማለፍ አይገባም።)
* ቁርኣን፣ ኪታብ የሚፈልጉ ደካሞችን መርዳት፣
* መሻይኾችን፣ ኢማሞችን፣ ዱዓቶችን፣ እየለመኑ ዲን የሚማሩ ደረሶችን ማስታወስ፣
* ጂልባብ፣ ኒቃብ፣ የሚፈልጉ አቅመ ደካማ እህቶችን መርዳት፣ ወዘተ.
ሶደቃ ኢማን ይጨምራል። ልብን ያረጥባል። ወንጀልን ያረግፋል። የአላህ ውዴታን ያስገኛል። ደረጃን ከፍ ያደርጋል። በላእን ይመልሳል። ብቻ ሶደቃን አነሰ ብለን ሳንንቅ ያቅማችንን እንፈፅም። የትኛው ስራችን ጀነት ለመግባት፣ ከእሳት ለመራቅ ሰበብ እንደሚሆነን አናውቅም።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
በረመዳን በብዛት የሚፈፀሙ ስህተቶች
~~~~
① ሶላት ሳይሰግዱ መፆም፣
② ሌሊቱን በጫት ካሳለፉ በኋላ ሱሑርን አስቀድሞ በመመገብ ፈጅር ሳይሰግዱ መተኛት፣
③ ቀኑን በእንቅልፍ፣ ሌሊቱን በተከታታይ ፊልም/ ሙሰልሰላት ማሳለፍ፣
④ ረመዳንን ጠብቆ መንዙማና ነሺዳ እየለቀቁ ሰዎችን ከቁርኣን ማዘናጋት፣
⑤ ተራዊሕን በንቃት እየሰገዱ ፈጅር ሶላትን በእንቅልፍ ማሳለፍ፣
⑥ ተራዊሕ ላይ በየ አራቱ ረከዐ መሐል የቢድዐና የሺርክ እንጉርጉሮዎችን ማስገባት፣
⑦ የተራዊሕ ኢማሞች ከሶላቱ ይልቅ ለቁኑት ዱዓእ የበለጠ ትኩረትና ጊዜ መስጠት፣
⑧ መግሪብ ሶላት ሲጠናቀቅ አሳፋሪ በሆነ መልኩ ለፊጥራ መጣደፍ (ሰጋጆችን የሚያቋርጥ፣ የሰው ጫማ የሚያቀያይር፣…ብዙ ነው)
⑨ ሌሊት ላይ "ተሰሐሩ " እያሉ በእስፒከር መጮህ፣
(10) የሱሑር ጊዜ ሳያልቅ ለጥንቃቄ በሚል ቀድሞ አዛን ማድረግ፣
(11) ሱሑር ላይ "ነወይቱ ሰውመ ገዲን" እያሉ በቃል መነየት፣
(12) እያንቀላፉ ተራዊሕ መስገድ፣
(13) ልጆች "እንፁም" ሲሉ ማበረታታት ሲገባ መከልከል፣ "ውሃ አያፈጥርም፣ ተደብቀህ ብላና ትፆማለህ" እያሉ መዋሸትና ውሸት ማለማመድ፣
(14) ሴቶች በተጋነነ የምግብ ዝግጅት ሰፊ ጊዜያቸውን ማቃጠል፣
(15) ሴቶች ሽቶ ተቀባብቶ ለተራዊሕ መውጣት፣
(16) በተራዊሕ ወቅት የሴቶችና የወንዶች አላስፈላጊ መዝረክረክ፣
(17) ሃሜት፣
(18) ፊጥራ ላይ ከመጠን በላይ መመገብ፣
(19) ቀኑን በካርታ፣ በዳማ፣ ወዘተ ማሳለፍ፣
(20) ሙዚቃ ማዳመጥ፣
(21) የሰው ስራ የሚሰሩ ተቀጣሪዎች ጧት በሰዓት አለመግባት (አማና መጠበቅ፣ ቃልን ማክበር ግዴታ ነው። ግዴታ ያልሆኑ ዒባዳዎች ተፅእኖ የሚያሳድሩብን ከሆነ መተው ወይም መቀነስ ይገባል)፣
(22) በተለይ በስራ ቦታዎች ላይ በመንዙማና በነሺዳ ማሳለፍ (መሆን ያለበት ከተመቼ ቁርአን መቅራት፣ ካልሆነ ዚክር ማድረግ ወይም ደዕዋ ማዳመጥ፣ ካልሆነ ዝምታ ይሻላል።)
(23) ለይለተል ቀድርን ለማየት ሰማይ ሰማይ እያንጋጠጡ መጠበቅ (የሚታይ ነገር የለም)፣
(24) አንዳንድ አካባቢዎች ዒሻን በጣም በማዘግየት ሰው ጀማዐ ላይ እንዳይካፈል እንቅፋት መሆን፣
(25) አንዳንድ አካባቢዎች መስጂድ ውስጥ ጫት ይዞ ገብቶ መቃም፣
(26) አንዳንድ አካባቢዎች "ተርቲብ" ብለው ንፍሮ፣ ቆሎና መሰል ምግቦችን ወደ መስጂድ እንዲያቀርቡ ህዝብን ማዘዝ፣
(27) የምግብ ብክነት፣ ወዘተ
(ኢብኑ ሙነወር፣ ግንቦት 05/2011)
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ሲጋራ
~~~
"ለማንም ሰው ሲጋራ መሸጥ አይፈቀድለትም። ምክንያቱም ሲጋራ የተከለከለ ነውና። አላህ አንድን ነገር ክልክል ካደረገ የሽያጭ ዋጋውንም ከልክሏል። እንዲሁም እሱን መሸጥ በወንጀልና ወሰን በመተላለፍ ከመተባበር ነው።" [አሊቃኡ ሸህሪይ፣ ኢብኑ ዑሠይሚን፡ 3/ 597]
-
ጫትም ላይ ተመሳሳይ ብይን ነው ያለው። መሸጥም፣ መግዛትም፣ ማጓጓዝም፣ መሸከምም፣ ማሸከምም፣ ሱቅን ለጫት ንግድ ማከራየትም፣ ... በየትኛውም መልኩ መተባበር አይፈቀድም።
=
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
"ፕራንከ በማድረግ የሚታወቀው ሶሀቢይ"
~
በዚህ መልኩ ርእስ ከሰጠ በኋላ የኑ0ይማን እና የሱወይቢጥን "ገጠመኝ" ማስረጃ አድርጎ የጠቀሰ ሰው አየሁ። የታሪኩን ጭብጥ ከፀሀፊው ልጥፍ ቀንጨብ አድርጌ ላቅርበው፦
{{ኑአይማን ሱወይቢጥን ምግብ ጠየቀው። አቡበክር ሳይመጣ አልሰጥህም አለው። በዚህን ግዜ ኑዐይማን ቆይ እሰራልሃለሁ ብሎት ወደ ሌሎች ነጋዴዎች ዘንድ በመሄድ "ባሪያ ትገዙኛላችሁ?" አላቸው። "አዎ በስንት እንግዛህ?" አሉት። "አይ ዋጋውማ ቀላል ነው ነገር ግን ባሪያው ጉድለት አለበት ጉድለቱን ሳልነግራችሁ አልሸጥላችሁም እስከነጉድለቱ ከገዛችሁኝ ነው የምሸጥላችሁ" አላቸው። "ጉድለቱ ምንድነው ?" ብለው ሲጠይቁት "ባሪያው ምላሱ ረጂም ነው ሁሌ ነጻ ሰው ነኝ ባሪያ አይደለሁም እያለ ይለፈልፋል" አላቸው። "ጉድለቱ ይህ ብቻ ከሆነ አብሽር እንገዛሃለን" አሉት። በ 10 ትናንሽ ግመሎች ተስማሙ። ግመሎችን ሰጥተውት እየነዳቸው ወደ ሱሀይቢጥ ጋር ነጋዴዎችን ይዟቸው መጣ። "ይሄው ባሪያው ውሰዱት" አላቸው። ሱሀይቢጥም "ኧረ ባሪያ አይደለሁም ነጻ ሰው ነኝ" ብሎ ቢጮህ "ዝም በል ይህ ነውር እንዳለብህ ቀድመን አውቀናል ዝም ብለህ ና" ብለው በገመድ አስረውት ወሰዱት።
አቡበክር ሲዲቅ ሲነገረው ስቆ ለነጋዴዎቹ ግመሎቹን መልሶላቸው ሱሀይቢጥን አስለቀቀው። ከጎዞ ሲመለሱ ለነቢያችን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ኑአይማን ሱሀይቢጥ ላይ የሰራው ፕራንክ ሲነገራች እሳቸውም ሶሀቦቻቸውም ሳቁ ኑዐይማንን አልወቀሱትም።
ኑአይማን ሌሎችም በርካታ ፕራንኮች አሉት ነቢያችን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም አይቃወሙትም ነበር ። }}
=
እንግዲህ በማህበራዊ ሚዲያ ፕራንክ እየተባሉ ለሚለቀቁ ስራዎች ማስረጃ መሆኑ ነው። ሌላም ፀሐፊ ከዚህ በፊት ይህንንና ሌሎች ቂሳዎችን በተከታታይ ሲፅፍ አይቻለሁ።
ለማንኛውም በኢስላም እንዲሁ ኪታብ ውስጥ ስለተገኘ ብቻ አንድ ዘገባ ዝም ብሎ አይወስድም። ተቀባይነቱ ይፈተሻል። የዘርፉ ማለትም የሐዲሥ ሊቃውንት ደግሞ ምርቱን ከእንክርዳዱ አበጥረው እየለዩ አስቀምጠዋል። ወደ ተነሳንበት ዘገባ ስንመለስ የሐዲሥ ምሁራን ብይን ይህንን ይመስላል፦
1- አልቡሲሪይ "ይሄ ደካማ ሰነድ ነው" ብለዋል። [ሚስባሑ ዙጃጃህ: 4/115]
2- አልባኒይ ደካማ ነው ብለዋል። [ዶዒፍ ኢብኑ ማጀህ፡ 750]
3- ሹዐይብ አልአርናኡጥ ደካማ ነው ብለዋል። [ተኽሪጁ ሙሽኪሉል ኣሣር፡ 1620] [ ተኽሪጁል ሙስነድ፡ 26687]
ይልቁንም ሰዎችን ለማሳቅ በሚል ውሸት እየፈጠሩ መናገር በኢስላም አይፈቀድም። ነብዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ይላሉ፡-
وَيْلٌ لِلَّذِي يُحَدِّثُ بِالْحَدِيثِ لِيُضْحِكَ بِهِ الْقَوْمَ فَيَكْذِبُ وَيْلٌ لَهُ وَيْلٌ لَهُ
"ሰዎችን ለማሳቅ ብሎ እየዋሸ ወሬን የሚያወራ ሰው ወዮለት! ወዮለት! ወዮለት!"
አቡነ ዳውድ፣ ነሳኢይ፣ ቲርሚዚይ እና አሕመድ የዘገቡት ሲሆን ሸይኹል አልባኒይ “ሐሰን” ብለውታል፡፡
የተጠቀሰውንም ሆነ ሌሎች ከኑ0ይማን ጋር ጋር የተያያዙ ቀልዶች ሰነዳቸው ደካማ እንደሆኑ የሚጠቀም አጠር ያለ ዳሰሳ በዚህ ሊንክ ታገኛላችሁ፦
https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid04D6qPPXykD7WodZJ5eW3Pms9የቴሌግራም ቻናል :-
t.me/IbnuMuneworPkcQBhiVjvwbKAc59Vf1hXwWxSKSQVnZZerTXq47l&id=354099817993687&mibextid=Nif5oz
=
Ibnu Munewor
የቴሌግራም ቻናል :-
t.me/IbnuMunewor
🔊 የወር አበባ እና ፆም
🍂 ለእህቶች አሳሳቢ ጥያቄዎች ምላሽ የተሰጠበት ደርስ
🎙 በሸይኽ ኢልያስ አሕመድ
✔ ሙስሊም ሴት ለመፆም ብላ ሐይድን የሚያስቀር ኪኒን መዋጥ ይፈቀድላታል?
✔ ሙስሊም ሴት በሐይድ ግዜ ምን አይነት ዒባዳ ማድረግ ትችላለች?
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ዛሬም ገንዘባቸውን ለጫት የሚያወጡ ሰዎች አሉ!
~
የኑሮ ውድነቱ እጅግ ከባድ ደረጃ ላይ ደርሷል። የቤተሰቡን ጉሮሮ ለመዝጋት እየተንገዳገደ ያለ ሰው ጫትና ሲጋራ ሲገዛ ማየት የእውነት ሱስ ምን ያህል ህሊናን የሚያውር ክፉ በሽታ እንደሆነ ማረጋገጫ ነው። ልጆች አገር አቋርጠው በሰው ሃገር፣ በሰው ቤት ነጭ ላብ አፈስሰው የሚልኩትን ገንዘብ ለጫት ማዋል የጭካኔ ጥግ ነው። አላህ ማስተዋሉን ያድለን።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
http://t.me//IbnuMunewor
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ከሸዕባን 15 በኋላ መፆም
~
ከሸዕባን አጋማሽ በኋላ መፆምን በተመለከተ በዑለማዎች ሁለት አይነት ሀሳቦች ተሰንዝረዋል፡፡
አንደኛው ወገን፡- መፆሙን የሚከለክሉ ናቸው፡፡ በርካታ ሻፍዒያዎች ይህንን አቋም መርጠዋል፡፡ ማስረጃቸውም፡-
“ሸዕባን ሲጋመስ እንዳትፆሙ” የሚለው ሐዲሥ ነው፡፡ [አቡ ዳውድ፡ 2337] [ቲርሚዚይ፡ 738]
ሌላኛው ወገን፡- ከሸዕባን አጋማሽ በኋላ መፆም ይቻላል የሚሉ ናቸው፡፡ ይሄኛው ምርጫ የብዙሃን ዑለማዎች ምርጫ ነው፡፡ ማስረጃዎቻቸው፡-
1. አቡ ሁረይራ ባስተላለፉት ሐዲሥ የአላህ መልእክተኛ ﷺ “ረመዳንን በአንድ ቀን ፆም ወይም በሁለት ቀን ፆም አትቀደሙት፡፡ የተለመደን ፆም የሚፆም ሰው ቢሆን እንጂ፡፡ እሱ ግን ይፁም” ብለዋል፡፡ [ቡኻሪ፡ 1969] [ሙስሊም፡ 1156]
ይሄ ሐዲሥ ረመዳን ሊገባ አንድና ሁለት ቀን እስከሚቀረው ድረስ መፆም እንደሚቻል ይጠቁማል፡፡ ስለዚህ ከሸዕባን አጋማሽ ጀምሮ ረመዳን ሊገባ አንድና ሁለት ቀን እስከሚቀረው ድረስ መፆም ይቻላል ማለት ነው፡፡ ቀድሞ ካስለመደው ፆም ጋር የገጠመለት ሰው ግን ከረመዳን በፊት ያለውን አንድና ሁለት ቀንም ጭምር መፆም ይችላል፡፡
2. እናታችን ዓኢሻ ረዲየላሁ ዐንሃ እንዲህ ብላለች፡- “ነብዩ ﷺ ከረመዳን በስተቀር ሙሉ የፆሙት ወር የለም፡፡ እንደ ሸዕባን ፆም ያበዙበት አላየሁም፡፡” [ቡኻሪ፡ 1914] [ሙስሊም፡ 1082]
በሌላ ዘገባ ደግሞ እንዲህ ብላለች፡- “ሸዕባንን ጥቂት ሲቀር እንዳለ ይፆሙት ነበር፡፡” [ሙስሊም]
3. እናታችን አሙ ሰለማ ረዲየላሁ ዐንሃ እንዲህ ብላለች፡- “ነብዩን ﷺ ሁለት ወሮችን አከታትለው ሲፆሙ አላየሁም፣ ሸዕባንና ረመዳንን ቢሆን እንጂ፡፡” [ቲርሚዚይ: 736] አልባኒ ሶሒሕ ብለውታል፡፡ [ሶሒሑ ተርጊብ ወተርሂብ፡ 1025] እዚህ ላይ የሸዕባንን አብዛኛውን ለማለት እንጂ ሙሉ ለማለት አይደለም፡፡ በዐረብኛ በዚህ መልኩ መግለፅ የተለመደ ነውና ይላሉ ዑለማዎች፡፡
እነዚህ ከሸዕባን አጋማሽ በኋላ መፆም ይቻላል የሚሉ ዓሊሞች የሚጠቅሷቸው ማስረጃዎች ናቸው፡፡ ሌሎችም ማስረጃዎች አሉ፡፡ ግን ከሸዕባን አጋማሽ በኋላ መፆም አይቻልም የሚሉ አካላት ያቀረቡትን “ሸዕባን ሲጋመስ እንዳትፆሙ” የሚለውን ሐዲሥ በተመለከተ “መፆም ይቻላል” የሚሉት ዓሊሞች ምን አሉ?
1. ከፊሎቹ ሐዲሡ ደካማ ነው ሲሉ ዘግተዋል፡፡ ኢማሙ አሕመድ፣ ኢብኑ መዒን፣ አቡ ዙርዐህ፣ ዐብዱረሕማን ብኑ መህዲ፣ በይሀቂ እና ሌሎችም ሐዲሡ “ሙንከር ነው” በማለት ደካማ እንደሆነ ከገለፁት ውስጥ የሚጠቀሱ ናቸው፡፡
2. ከፊሎቹ መልእክቱ የተገደበ እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡ ሐዲሡን ቲርሚዚይ፣ ኢብኑ ሒባንና ኢብኑ ማጃህ ሶሒሕ እንደሆነ የገለፁ ሲሆን ኢብኑ ሐዝም፣ ኢብኑል ቀይምና ሸይኹል አልባኒይ ሐዲሡን ደካማ ነው ያሉትን ጠንከር አድርገው ሞግተዋል፡፡ ሆኖም ግን የሐዲሡ መልእክት ከነጭራሹ ከሸዕባን አጋማሸ በኋላ መፆምን ለመከልከል ሳይሆን ቀድሞ ልምድ ሳይኖረው ወይም በወሩ የመጀመሪያ አጋማሽ ምንም ሳይፆም ከሁለተኛው አጋማሽ በኋላ የሚፆምን ነው የተከለከለው ይላሉ፡፡ ኢብኑ ባዝ፣ ዐብዱል ሙሕሲን አልዐባድና ሌሎችም ይህንን ሀሳብ ከደገፉት ውስጥ ናቸው፡፡
3. ከፊሎች ደግሞ በሐዲሡ ውስጥ የተገለፀው ክልከላ ሐራምነት የሚደርስ ሳይሆን እንደማይበረታታ ለመጠቆም ነው ይላሉ፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ለረመዳን ፆም መዳከም እንዳይከተል ለማሳሰብ ነው ይላሉ፡፡ ሸይኽ ኢብኑል ዑሠይሚን ረሒመሁላህ ሐዲሡ ሶሒሕ እንኳን ቢሆን ክልከላው ሐራምነት አይደርስም ይላሉ፡፡ አልቃሪም ይህንን ሀሳብ መርጠዋል፡፡
ሲጠቃለል፡-
1. ከሸዕባን አጋማሽ በኋላ መፆም የሚከለክለውን ሐዲሥ አብዛኞቹ ዑለማዎች ደካማ እንደሆነ የገለፁ ሲሆን ከላይ የቀረቡትን ማስረጃዎች መነሻ በማድረግ በሁለተኛው የሸዕባን አጋማሽ ውስጥ መፆም እንደሚቻል ገልፀዋል፡፡
2. ነገር ግን የመጀመሪያው አጋማሽ ውስጥ ያልፆመ፣ ሰኞና ሐሙስ ወይም መሰል ልማድ የሌለው ሰው እንዲሁ ከሸዕባን አጋማሽ በኋላ ለመፆም ባይነሳ የተሻለ ነው፡፡ በተለይ ደግሞ ከልካዩን ሐዲሥ “ሶሒሕ ነው” የሚሉ ዓሊሞች ትንታኔ ጠንከር ያለ ስለሆነ ከሸዕባን 15 በኋላ ያለምንም መነሻ ፆም በመጀመር እራሳችንን ኺላፍ ውስጥ ከማስገባት ልንቆጠብ ይገባል፡፡
3. ሰኞና ሐሙስ ወይም ሌላ ያስለመደው ፆም ያለው ሰው፣ እንዲሁም በመጀመሪያ የሸዕባን አጋማሽ ውስጥ ሲፆም የነበረ እና መሰል ሰበቦች ያሉት ሰው ፍላጎቱ ከሆነ በሁለተኛውም አጋማሽ መፆም ይችላል፡፡ ወልላሁ አዕለም።
(ኢብኑ ሙነወር፣ ሚያዚያ 26/2010)
=
የቴሌግራም ቻናል፦
http://t.me//IbnuMunewor
Repost from ዳር አልሺፋእ የማማከር አገልግሎት
ፆም እና ጤና
👇👇👇👇
ፆማችን በኢኽላስ ስንፆም አላህ ዘንድ ካለው የላቀ ደረጃ በተጨማሪ በተለይ በዚህ ውፍረት ዐለም ዓቀፍ የማህበረሰብ ጤና ችግር በሆነበት ሰዓት በጣም ያረዘመ የምግብ ክልከላ [ፆም] የሚከተሉት የጤና ጠቀሜታዎች አሉት
—የአምሮ የማሰብ አቅም [cognitive performance] ይጨምራል
—አላስፈላጊ የሰውነት መቆጣት [inflammation] ይቀንሳል
—ሰውነት ውስጥ የተከማቸ ስብን በማቅለጥ ጤናማ አቋም ያስገኛል
—ውፍረትን ተከትለው የሚመጡ የብዙ ካንሰሮችን ተጋላጭነት ይቀንሳል
—የmetabolic እና ተላላፊ ያልሆኑ እንደ ስኳር ፣ ደም ግፊት እና ስትሮክ አይነት ገዳይ በሽቶች ተጋላጭነት ይቀንሳል
—አጠቃላይ ንቁነትን ይጨምራል
» በዚህም ምክንያት ሙስሊም ያልሆኑ አካላት እንኳን ሰውነት ገንቢዎችን [body builders] ጨምሮ ሰውነት ውስጥ ያለውን ቅባት ለመቀነስ አልፎ አልፎ የሚፆመውን [intermittent fasting] ለጤናቸው ሲሉ ይተገብራሉ።
ከዚህ በተጨቃራኒው ፆም ጤናቸውን ሊጎዳቸው የሚችል
—ህፃናት
—በድሜ የገፉ
—ነፍሰ ጡሮች
—ተላላፊ ያልሆኑ እንደ ስኳር [በተለይ ጥሩ ክትትል ያልነበራቸው እና የደም ስኳር በቁጥጥር ስር ያልሆነ] በሽተኞች
መፆም ለይኖርባቸው ወይም ከፍተኛ ጥንቃቄ ሊያደርጉ እና ሃኪማቸውን በማማከር ቅርብ ክትትል ማድረግ ሲኖርባቸው
* ርሃሀብ የሚያስነሳው የጨጓር ህመም[gastric ulcer] ያለባቸው ደግሞ ከፍተኛ የምግብ ጥንቃቄ፣አጫሽ ከሆኑ ረመዳንን እንደጥሩ አጋጣሚ በመጠቀም ማቆም ፣ቡናና የሚያስነሳባቸውን ነገር ሁሉ ማስወገድ ይኖርባቸዋል
...ስናፈጥርም ከተቻለ ቴምር እና ቀለል ያሉ ምግቦችን መጠቀሙ ኸይር ነው።
አለህ እኛንም እናንተንም ረመዳንን ደርሰውበት ከሚጠቀሙበት ያድርገን
https://t.me/drdawudconsultancy
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ነፃ ካልወጡ ነፃ አውጪዎች ተጠንቀቂ!
~
የፊታችን ማርች 8 አለም አቀፍ የሴቶች ቀን ነው አሉ፡፡ ወይ ፈረንጅ! አመቱን በሙሉ እኮ “የምንትስ ቀን” እያሉ ሊዘጉት ነው፡፡ ፈረንጅ ሲስል የሚስለው ሌላው ክፍል ነጩ ሰው “የግብረ ሰዶማውያን ቀን” ብሎ ቢጀምር ያለምንም ማመንታት ይከተላል፡፡ አሁንም ስላለመኖሩ እርግጠኛ አይደለሁም፡፡ ብቻ ማርች ስምንትን ለሴቷ ሰጧት አሉ፡፡ “ዶሮን ሲያታልሏት በመጫኛ ጣሏት!!”
እለቱን ሳስታውስ አንድ ነጭ አስተማሪ ስለ ሴቶች “መብት” እንቅስቃሴ እያወራ የተናገረው ነገር ከአመታት በኋላ ትዝ አለኝ፡፡ የሴቶችን መብት ካፋጠኑ ነገሮች አንዱ ብስክሌት ነው ነበር ያለው፡፡ ባስታወስኩ ቁጥር ይደንቀኝ ነበርና ኢንተርኔት ገብቼ ሳስስ ለካንስ ሀሳቡ የሱ ብቻ አይደለም፡፡ ይሄ ነገር ሰዎቹ ምን ያክል ቂ ሎ ች እንደሆኑ እና ነፃነት ሲሉም ግርማ ሞገስ ያለውን አለባበሷን ማስጣል እና በቤት እመቤትነቷ እንድትሸፍት ማድረግ እንደሆነ ቁልጭ አድርጎ ያሳያል፡፡ ብቻ አላማቸው የሴቶችን መብት ማክበር እንዳልሆነ ከሙስሊም ሴቶች አንፃር ያላቸው አተያይና ፖሊሲ በተጨባጭ አይን ላለው ሁሉ እያሳየ ነው፡፡ እርቃንነትን እስከ ጥግ እየፈቀዱ ሙስሊሟን ግን አለባበሷን ምክኒያት በማድረግ፣ ከትምህርት ገበታ፣ ከስራ ቦታ ማፈናቀሉን ተያይዘውታል፡፡ እነዚህ ናቸው እንግዲህ ስለ ሴቶች መብት የሚያቀነቅኑት፡፡ ከባህልም ከሞራልም ያፈነ ገጡ አለባበሶች ላይ ትንፍሽ ሳይሉ ለሙስሊሟ ሲሆን ግን በየመንገዱ ይጎነትላሉ፡፡ አልፈውም ህገ-ደንብ ያወጣሉ፡፡ ፖሊሲ ያረቃሉ፡፡ ከዚያም አያፍሩም ስለ ሴቶች መብት ይደሰኩራሉ፡፡ “የምትለብሺውን እኔ ካልመረጥኩልሽ” ከማለት በላይ ምን አፈና አለ?!!
እህቴ ሆይ! ተጠንቀቂ!! ብዙዎቹ የሴቶች “ነፃ አውጪዎች” የሰይጣን ተልእኮ አራማጅ የሆኑ የሀሰት ጥሩ ንባዎች ናቸው፡፡ እውነት ተቆርቁሮልሽ እንዳይመስልሽ፡፡ ቢሆንማ ለእርቃን እሩብ ጉዳይ መሆንን ፈቅዶ መልበስሽን ለምን ይቃወምሻል?! እውነት ለመብትሽ ተሟጋች ከሆነ ስትራቆቺ ገልፍጦ ስትለብሺ ለምን ደሙ ይፈላል?! ለምንስ በየመንገዱ ይጎነትላል?! ለምንስ ከየተቋሙ ያባርራል?! እመኚኝ “ነፃ ውጪ” የሚለው በየጎዳናው በነፃነት በነፃ ወይም በርካሽ እንዲያገኚሽ ነው፡፡ አስተውይ! ልብስሽን ስለጣልሽ ነፃ አትወጭም፡፡ ነፃ መሆን ልብስ በመጣል ከሆነ ነፃ ሰዎች ማለት እብ - ዶች ናቸው፡፡ የሚጮኸው ስለ ክቡር ማንነትሽ ሳይሆን ስለ እርቃን ገላሽ ነው፡፡ የነቁበት ነቅተውበት እየተመለሱ ነው፡፡ ይሄውና በምዕራቡ አለም ከሚሰልሙት ውስጥ 80% ሴቶች ናቸው፡፡ ብዙዎች ለሀጫቸው የሚዝረበረብለትን የምዕራቡን “ነፃነት” ሸሽተው ወደ ኢስላም “ጭቆና” ይጎርፉ ይዘዋል፡፡ በጊዜ ንቂ፡፡ ብልጥ ማለት በሌሎች ላይ ከደረሰው ቀድሞ የሚማር ነው፡፡ ምሳሌሽን በትክክል ምረጪ፡፡ በአኢሻ ስብእና እያፈርሽ አሊሻን መሆን ካማረሽ ግን ግፊበት፡፡ ጀሀነምን የሚቋቋም ገላ ካለሽ መንገዱን ጨርቅ ያርግልሽ፡፡
ንቂ! ያለበለዚያ ይሄ በስጋዊ ፍላጎት የታወረው “ጠበቃሽ” የኮንዶም ማስታወቂያ ነው የሚያደርግሽ፡፡ ንቂ! ያለበለዚያ ይሄ ካንገት በታች እንጂ ካንገት በላይ የሌለው ርካ ሽ በ ድ ን ከምንም በታች አርክሶሽ የሱ ርካሽ ሸቀጥ ማሻሻጫ ነው የሚያደርግሽ፡፡ ንቂ! ሙስሊም ወንድምሽ ስለበደለሽ በኢስላም ላይ ብታምጪ ኢስላምን ቅንጣት ታክል አትጎጂውም፡፡ ብቻ በዱንያም ላታተርፊ ሁለቱንም አገር የከሰርሽ ከሁለት ያጣሽ ትሆኛለሽ፡፡ እራስሽን ሁኚ፡፡ የገደል ማሚቶ አትሁኚ፡፡ ሌሎች ስለሳሉ አትሳይ ስላነጠሱም አታነጥሺ፡፡ የተፈጠርሺው ለክቡር አላማ ነው፡፡ አላማ ቢስ አትሁኚ፡፡ ያለበለዚያ ኮምፓስ እንደሌለው መርከብ ዋለሽ ዋለሽ አስከፊ ፍፃሜ ላይ ትደርሻለሽ፡፡
ተጠንቀቂ!! ከሸሪዐው አጥር ውጭ ያለ የመብት ጥያቄ አትጠይቂ፡፡ የፈጠረሽ ጌታ አንቺ እራስሽን ከምታውቂው በላይ ያውቅሻል፡፡ ላንቺም ከተኩላው “እንባ ጠባቂ” ቀርቶ ከራስሽም በላይ ያዝንልሻል፡፡ ደግሞም አትዘንጊ፡፡ ህይወት ማለት የአኺራ ህይወት ነው፡፡ አላህ አድሎሽ ሰማንያ ዘጠና አመት ብትኖሪ እንኳ በጊዜ ከኢስላም ባቡር ውስጥ ካልተሳፈርሽ ሲመሽ ይቆጭሻል፡፡ ምን ብትኖሪ ህይወትሽ መጨረሻ አለው፣ ሞት፡፡ ከዚያ በኋላ ደግሞ ዘላለማዊ ህይወት፡፡ የዛሬው ቅቤ አንጓች “እንባ ጠባቂ” ተኩላ ግን የአኺራ ምንነቱም አይገባውም፡፡ ለዚያ ቀርቶ ለዱንያ እንኳ ጤነኛ ህልም የለውም፡፡ ለአኺራማ እንኳን ላንቺ ለራሱም አይሆንም፡፡ የአህያ ባል ከጂብ አያስጥልም፡፡ ለናቱ፣ ለሚስቱ፣ ለልጁ፣ ለእህቱ የማይሆን ሰካ - ራም ነፃ ያወጣኛል ብለሽ ከገመትሽ የመጨረሻ ቂ ል ነሽ፡፡ እሱ እራሱ በስሜቱ የሚገዛ የስሜት ባሪያ ሆኖ በየትኛው ሞራሉ ነው አንቺን ነፃ የሚያወጣሽ?! ቀድሞ ነገር ምን ሲደረግ ለሰካ - ራም ጆሮሽን ሰጥተሽ?! ቦታ ከሰጠሽውማ የአለም እዝነት የሆኑትን ነብይ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ጠላትሽ እንደሆኑ ቀስ እያለ እያዋዛ ያሰርፅብሻል፡፡ በጊዜ ካልነቃሽ መውጣት ከማትችይበት የስሜት አሮንቃ ውስጥ ይነክርሻል፡፡ በደጋሚ ምላሱ ጭንቅላትሽ ላይ ተብትቦብሽ የስሜት ባሪያ ሆነሽ ረክሰሽ፣ ከማንም በላይ ብቁና ንቁ የሆንሽ ይመስልሻል፡፡ ተቆርቋሪ መስሎ ስለቀረበ እንዳያታልልሽ፡፡ ውሃ ሲወስድ እያሳሳቀ ነው፡፡ ከዚያ በኋላ ሐያእሽ ባለመሟጠጡ በግልፅ ባታወጪው እንኳ ውስጥሽ ለኢስላም ይደፈርሳል፡፡ ለነብዩ ሶለላሁ አለይሂ ወሰለም ያለሽ ክብርም ምናልባት ካልጠፋ በእጅጉ ይቀንሳል፡፡ ግን እስቲ እኔ ልጠይቅሽ፡ እውነት ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ላንቺ ስለማይቆረቆሩ ነው ከመቶ ሺ በላይ ሶሐቦቻቸው በተሰበሰቡበት ታላቅ ቀንና ታላቅ ቦታ ላይ “የሴቶችን ነገር አደራ” እያሉ አዋጅ ያሰሙት? እርግጥ ነው ብዙ በደል አለብሽ፡፡ ግን አስተውይ ከበደሎቹ ሁሉ የከፋው ዘላለማዊ ክብር የሚያጎናፅፍሽን ኢስላምሽን እንዳታውቂ መደረግሽ ነው፡፡ እናም እልሻለሁ፡ በኢስላም ከኢስላም መብትሽን ፈልጊ፡፡ ለወዳኛው ህይወትሽም ትጊ፡፡ የተኩላ ሰለባ እንዳትሆኚ ንቂ፡፡ የአላህ ሰላም ላንቺ ይሁን፡፡
(ኢብኑ ሙነወር)
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
السلام عليكم ورحمة الله وبركاته
ረመዳን እየተቃረበ ነው። ከወዲሁ ዝግጅት መጀመር ይኖርብናል። ከምንዘጋጅባቸው ነገሮች ውስጥ ቀዳሚው የእውቀት ዝግጅት ነው። በዚህ ረገድ ከተጳፉ ኪታቦች ውስጥ አጠር ብሎ ግን ብዙ ጥቅሞችን የያዘው የሸይኽ ሙሐመድ ብኑ ዐብዲል ወሃብ አል-ወሷቢ
"مذكرة في أحكام الصيام"
የተሰኝው ኪታብ በሸይኽ ሙሐመድ ዘይን ሸይኽ ኣደም ተቀርቶ ተጠናቆል ሙሉ ደርሱን እኒህን ሊንኮች በመጫን በቀላሉ ማግኝት ይችላሉ።
የኪታቡ ፒዲኤፍ ↓↓↓
https://t.me/SheikhMuhammedZainAdam/1575
ክፍል - አንድ ↓↓↓
https://t.me/SheikhMuhammedZainAdam/1582
ክፍል - ሁለት ↓↓↓
https://t.me/SheikhMuhammedZainAdam/1592
ክፍል - ሶስት ↓↓↓
https://t.me/SheikhMuhammedZainAdam/1670
ክፍል - አራት ↓↓↓
https://t.me/SheikhMuhammedZainAdam/1672
ክፍል - አምስት ↓↓↓
https://t.me/SheikhMuhammedZainAdam/1674
ክፍል - ስድስት ↓↓↓
https://t.me/SheikhMuhammedZainAdam/1689
ክፍል - ሰባት ↓↓↓
https://t.me/SheikhMuhammedZainAdam/1704
ክፍል - ስምንት ↓↓↓
https://t.me/SheikhMuhammedZainAdam/1722
ክፍል - ዘጠኝ ↓↓↓
https://t.me/SheikhMuhammedZainAdam/1738
ተጨማሪ ትምህርቶችን ለማግኝት ቻናሉን ይቀላቀሉ ↓↓↓
https://t.me/SheikhMuhammedZainAdam
Repost from Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹
በሸዕባን አጋማሽ ላይ የሚፈጸም ልዩ ዒባዳህ የለም።
በዚህ ዙሪያ የመጡ ሐዲሦችም ደካማ ናቸው።
ሸይኽ ዶ/ር አልፈውዛንን አዳምጧቸው።
||
t.me/MuradTadesse
Repost from Kassis Faage
حكم تخصيص ليلة النصف من شهر شعبان بالصلاة والصيام؟
▪قال الشيخ ابن باز رحمه الله:
ما ورد في فضل الصلاة فيها فكله موضوع.
#المرجع 📚 [مجموع الفتاوى (١-١٨٦)]
•┈┈┈┈•✿✿•┈┈┈┈•
▪قال الشيخ ابن باز رحمه الله:
الاحتفال بليلة النصف من شعبان بالصلاة أو غيرها, وتخصيص يومها بالصيام بدعة منكرة عند أكثر أهل العلم,
وليس له أصل في الشرع المطهر,
بل هو مما حدث في الإسلام بعد عصر الصحابة رضي الله عنهم .
#المرجع 📚 [مجموع الفتاوى (١-١٩١)]
•┈┈┈┈•✿✿•┈┈┈┈•
▪قال الشيخ ابن عثيمين رحمه الله:
الصحيح أن صيام النصف من شعبان أو تخصيصه بقراءة أو بذكر لا أصل له،
فيوم النصف من شعبان كغيره من أيام النصف في الشهور الأخرى.
#المرجع 📚 [مجموع الفتاوى (٢٠-٢٣)] .
•┈┈┈┈•✿✿•┈┈┈┈•
▪قال الشيخ ابن عثيمين رحمه الله:
صيام يوم النصف من شعبان بخصوصه ليس بسنة وإذا لم يكن صومه سنة كان بدعة، لأن الصوم عبادة فإذا لم تثبت مشروعيته كان بدعة.
#المرجع 📚 [مجموع الفتاوى (٢٠-٢٦)] .
•┈┈┈•✿✿•┈┈┈•
حكم قيام ليلة النصف من شهر شعبان ؟
🎙قال الشيخ ابن عثيمين رحمه الله:
قيام ليلة النصف من شعبان له ثلاث مراتب:
١- أن يكون له عادة في قيام الليل
فيفعل في ليلة النصف ما يفعله في غيرها من غير أن يخصها بزيادة فهذا أمر لا بأس به.
٢- أن يصلي في ليلة النصف من شعبان دون غيرها من الليالي فهذا بدعة.
٣- أن يصلى في تلك الليلة صلوات ذات عدد معلوم، يكرر كل عام، فهذه المرتبة أشد ابتداعاً من المرتبة الثانية وأبعد عن السنة.
#المرجع 📚 [مجموع الفتاوى]
•┈┈┈•✿✿•┈┈┈•
#መልካም_ሚስት ♥
ባለቤቱን ለማጨት ከሽማግሌዎቹ ጋር ወደ ቤቷ አቀና። ልታገባት የምትፈልጋት ሴት ልታይህ ትፈልጋለች በመባሉ ነው አብሯቸው የሄደው። ቤት ገብተው ልጃችሁን ለልጃችን እንዳሉ ከአላህ ቃል ምን ያህል በቃሉ እንደሐፈዘ እንስቲቱ ጠየቀች።
እርሱም "አጫጭር ሱራዎችን እንጂ አልሐፈዝኩም ነገር ግን በአላህ ፈቃድ መልካምና ሷሊህ የአላህ ባርያ ለመሆን እጥራለሁ" አላትና አንቺስ?! በማለት ጠየቃት። ሽማግሌዎቹ በተዳዱበት ቃለ ምልልሱን አጦፉት።
"ጁዝ አማን በከፊሉ ሐፍዣለው" አለች።
እውነተኛ ሰው መሆኑን ከንግግሩ ስታረጋግጥ ልታገባው ተስማማች።
ከጋብቻ በኋላ ቁርአንን በቃላቸው አብረው ሊሐፍዙ ቃል ተጋብተው ተስማሙ። ውጥናቸው ሰምሮ ኒካሑ ታሰረ።
ከሱረቱል መርየም ሒፍዛቸው ተጀመረ የቤታቸው ጣራና ማገር ከሐለቃው እየታደሙ ቁርአኑን በልባቸው አተሙ። ሙሉ በሙሉ የአላህን ቃል ሐፈዙ። ሚስት የቡኻሪ ሐዲሶችን እንቀጥል ስትል ሐሳብ አቀረበች። እሱም ተስማማ ወደ ሐዲስ ሒፍዙ ተሸጋገሩ።
ከዕለታት በአንዱ ቀን ባል ወደ አባቷ ቤት ለዚያራ አቀና። በጨዋታ መሐል "አልሐምዱሊላህ ልጅህ ከሰሞኑ ቁርአንን በቃሏ ሐፈዛ ቡኻሪን ጀምራለች" አለ አባቷን እየተመለከተ። ስለሷ ሲያወራ አይጠግብም እንዲሁ ከንፈሮቹን ያንቀጠቅጣል ፅናቷ መልካምነቷ በህመም ላይ ሆና እንኳ የቁርአን ሒፍዝ ፕሮግራሟን ዝንፍ አለማድረጓን ተመልክቷል።
አባት በንግግሩ ግራ እየተጋባ ወደ ልጁ ክፍል አመራ። ብዙ ወረቀቶችን አምጥቶ ከፊቱ አስቀመጠ። ሚስቱ ከማግባቷ በፊት ቁርኣንንና ስድስቱን የሐዲስ መጽሃፎች መሐፈዟን የሚያሳዩ ወረቀቶችን ተመልክቶ እጁን በአፉ ላይ ጫነ።
የእውቀቱ ማነስ ሳያሳፍራት መልካምነቱን ተቀብላ የበታችነት ሳይሰማው ባሏን የሰራችው ይህቺ ሴት ክብርና ምስጋና ይገባት።
★★★★ ★★★ እናንተ ወጣቶች ሆይ!! ★★★★★★★
ሷሊህ ወጣን ባልሆንም ሷሊህ ልታደርገኝ የምትጥርን መልካም ሚስት ለግሰኝ ብላችሁ ዱዓ አድርጉ።
Via Mahi Mahisho
Hijra Tube ኢስላማዊ ድህረ ገፅ
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
