cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

AFZAN MEDIA / አፍዛን ሚዲያ

አላህን በደስታህ ጊዜ ተዋወቅ በችግር ጊዜ ያውቅሀልና!!!

Mostrar más
Publicaciones publicitarias
383
Suscriptores
Sin datos24 horas
-17 días
-730 días

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

በቢላል እና ጓደኞቹ እስር ዙርያ ያለው መነቃቃት እና ተቃውሞ ጥሩ ነው ።በዚሁ ሊቀጥል ይገባል ። የቢላልን በጎ ስራ እየጠቀሱ ተቃውሞውን ጎን ለጎን ማስኬድ ቢቻል የበለጠ ይሆናል ። ለምሳሌ -ቢላል የዞኑ መንግስ እንኳን ያቃተውን ንፁህ የውሃ አቅርቦት ለነዋሪው ለመስጠት ተግቶ ሰርቷል። ጉድጓድ አስቆፍሯል። -ተጨማሪ ለማስቆፈርም በጥናት ላይ ይገኛል። -ከተለያዩ አካላት ጋር በመተባበር ትምህርት ቤት አስገንብቷል ። -ምግብ አልባሳት እና ቁሳቁስ ለህዝቡ አቅርቧል -የታመሙ አሳክሟል ። ይህን እና መሰል መልካም ስራዎቹን እየጠቀስን ከፎቶው ጋር እያያዝን አሳሪዎቹ የልማት እንቅፋት መሆናቸውን እናጋልጥ። በቢላል ዙርያ ከሰለሙ ታዳጊ ወላጆች በቂ መረጃ የሚሆን ቪዲዮ ደርሶኛል በአላህ ፈቃድ በቅርብ እመለስበታለሁ። ጎን ለጎን ደሞ በጉጂ ዞን አክራሪ ጴንጤዎች ሴራ የታሰሩትን ሸኽ አህመድ እና ጓደኞቻቸው ድምፅ ብንሆን መልካም ነው ሸኽ አህመድ ከ30 አመታት በላይ በገጠር ዳእዋ ስራ ላይ የኖሩ ጠንካራ ዳኢ ናቸው ። በተለይ ሚሽነሪዎች በሚበዙባቸው እንደጉጂ ዞን ያሉ አካባቢዎች በርካቶችን ወደተፈጥሪዊ ዲናቸው ኢስላም በመመለስ እና በማስተማር ይታወቃሉ። ሸኽ አህመድ በዚህ ስራ የተነሳ በርካታ ችግር ገጥሟቸው ግን በፅናት አልፈውታል። አሁን ያነሱት ጥያቄ ሸኽ አሊ ከሚባሉ በጎ ሰው ከ90 ዓመት በፊት ለህዝበ ሙስሊሙ የተበረከተ 15 ሄክታር የዛውያ እና መስጅድ ይዞታ ለመኖሪያ ቤት አይሸንሸን የመስጅድ ይዞታ ለግል አይሰጥም በማለቱ ነው። አሁን የወረዳው መጅሊስ አመራር እንደነገረኝ ይህ የሙስሊሞች ይዞታ ተሸንሽኗል ለግለሰብ ቤትነት አልፎ ከቸርችም ተቆርጦለታል ። ይህን ግፍ መቃወም ወንጀል አይደለም ። ሸኽ አህመድ እና ጓደኞቻቸው በአስቸኳይ ይፈቱ ብለን ከታሳሪዎች ጎን እንቀየም። አቡሱመያ ዲኑ
Mostrar todo...
በቢላል ጉዳይ መጅሊሱ በህግ ክፍሉ በኩል በቀጥታ ጣልቃ ሊገባ ይገባል። የማህበሩ ሰዎች ሃይማኖታቸውን በቅጡ መስበክ ሲከብዳቸው ዳእዋ ለአይ ያሉ ወንዶሞቻችንን በውሸንት እየወነጀሉ በማሸማቀቅ ስራውን እንዲያቆሙየሚሄዱበት እርቀት አሳፋሪ ነው። የሆነው እንደዚህ ነው እነቢላል ዳእዋ አደረጉ ።በርካቶች ሰለሙ ።ከዚያ ውስጥ አምስት ታዳጊዎች ዲን ለመማር ወደቀይ አፈር መሄድ ፈለጉ ።ከቤተሰብ ከልጆቹ እና ከቀበሌው ፈቃድ ተገኘ ። ወደቀይ አፈር ተጓዙ ።እውነታው ይሄ ሆኖ ሳለ የማህበሩ ሰዎች ከአምስቱ አንዱን በተንኮል ከተጓዦቹ ውስጥ እንዲካተት እና ተገድጄ ነው እንዲል አሴሩ። ነገር ግን የቀበሌው ደብዳቤ የአራቱ ምስክርነት እና የቤተሰብ ፈቃድ መኖሩን እረስተዋል። ወዳጆቼ ፍትህ ለቢላል የሚል ቻሌጅ ካልጀመርክ ካልጀመርሽ ከቢላል ጎን መቆም ካቃተህ ካቃተሽ ይህን ጉዳይ ዝም ካልክ ዝም ካልሽ ነገ ዳኢ አልባ ሃይማኖት ተከልካይ የለሽ ዲን ሁሉም የሚደፍረው እምነት ባለቤት ለመሆን ፈቅደካል ፈቅደሻል። ፍትህ ለቢላል እና ጓደኞቹ ቢላል እና ጓደኞቹን ያለምንም ቅደመ ሁኔታ ፍቱልን
Mostrar todo...
Photo unavailableShow in Telegram
ይህ በ1900ዎቹ የተነሳ ምስል ነው ከሂጃዝ ተነስቶ ኢስታንቡል ይደርስ የነበረ ባቡር ነው። በውስጡ የደማስቆ፣ የኢራቅ፣ የሊባኖስ፣ የቱርክ ሙስሊሞች ሁሉም በአንድ ባቡር ያለ ቪዛ፣ ያለ ፓስፖርት፣ ያለ መታወቂያ ተጉዘው የፈለጉበት ሀገር የፈለጉበት ቦታ ያርፋሉ። በጥንታዊቷ የደማስቆ ከተሞች አንዷ በሆነችው ኢየሩሳሌም ቁድስ ዙህራቸውን ሰግደው ዮርዳኖስ ኦሲስ የሚወስደውን መንገድ አልፈው የሂጃዝን በረሃ አቆራርጠው መካና መዲና ይደርሳሉ። ሲመለሱ የሂጃዝን ቴምር፣ የፍልስጤምን ወይራ፣ የደማስቆን ወይንና የኢራቅን እርጥብ ተምር ሸክፈው ይመለሳሉ። ይሄ ታዲያ አንድ በነበሩበት ጊዜና ኢስላም አለምን በመራበት ወቅት ነው። © Mahi mahisho
Mostrar todo...
ማህበረሰቡ "እዝነት የአካል ጉዳተኛ ህፃናት እና ወላጆች መርጃ ድርጅትን" እንድጎበኝ ጥሪ ቀረበ! ... እዝነት የአካል ጉዳተኛ ህፃናት እና ወላጆች መርጃ ድርጅት ከተመሰረተ ሶስት አመት የሞላው ሲሆን በማእከሉ የሚረዱ ህጻናት ማየት የተሳናቸው፣ መስማት የተሳናቸው ፣ መናገር የማይችሉ፣ ራሳቸውን ችለው መቆም ሆነ መቀመጥ የማይችሉ፣ የሚጥል በሽታ ያለባቸው፣ ራሳቸው መመገብ የማይችሉ  ተደራራቢ የአካል ጉዳት ያለባቸው ህፃናትን እየረዳ ይገኛል በተጨማሪም ማዕከሉ ህፃናቱን ለመከባከቡ ወላጆች የስራ ዕድል መፍጠር ችሏል። . "ሰኔን ለእዝነት"በሚል መሪ ሀሳብ ማህበረሰቡ  ማዕከሉ የሚሰራቸውን ተግባራት ለጉብኝት ክፍት ያደረገ ሲሆን በዛሬው ዕለት በርካታ ሰዎች ማዕከሉን ጎብኝተዋል።እዝነት የአካል ጉዳተኛ ህፃናት እና ወላጆች መርጃ ድርጅት መስራች እና ስራአስኪያጅ ወ/ሮ ዘቢብ አህመድ ስለድርጅቱ ለጎብኝዎች ያስረዳች ሲሆን ጎብኝዎች በበኩላቸው ማዕከሉ እያከናወነ ያለው ስራ እጅግ አድካሚና ጥንካሬ የሚጠይቅ በመሆኑ ሁሉም የበኩሉን ድጋፍ ማድረግ አለበት ብለዋል። . እዝነት የአካል ጉዳተኛ ህፃናት መርጃ ማዕከል አሁን ላይ በማዕከሉ  ከ50 በላይ ተደራራቢ የአካል ጉዳት ያለባቸውን ህፃናት እየተንከባከበ የሚገኝ ሲሆን የቤት ኪራይን ጨምሮ በወር ቢያንስ ከ800 ሺህ ብር በላይ ወጪ እንደሚያደርግ ወ/ሮ ዘቢባ ተናግራለች።በመሆኑም ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል "ሰኔን ለዕዝነት"ንቅናቄን ተቀብሎ ድርጅቱን እንድጎበኝ ጥሪ ቀርቧል።
Mostrar todo...
ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ  ራጅዑን የካእባ ቁልፍ ዋና ያዥ  እና የሶሃባው የኡስማን ኢብኑ ጠልሃ (ረዐ) 109ኛ ተከታይ ቤተሰብ የነበሩት ሼክ ሳሊህ አል-ሻይባ ከዚህ አለም በሞት ተለዩ ... በረሱል ሶለሏሁ አለይሂ የካእባን ቁልፍ መያዝ  የነርሱ  ቤተሰብ ድርሻ እንደሆነ  የተነገረላቸው የሶሃባው ኡስማን ኢብን ጦልሃ (ረ.ዐ) ቤተሰቦች ከትውልድ ወደ ትልልድ  እየተሸጋገረ 109ኛው  ተከታይ  የሆኑት  ሼይኽ ሳሊህ አል-ሸይባ  እጅ ላለፉት ዓመታት ቆይቷል:: ሀረመይን የሼይኽ ሳሊህን ማለፍ የገለፀ ሲሆን ሶላተል ጀናዛ  ከፈጅር በኋላ ዛሬ በመስጂድ አል ሀራም የሚከናወን ሲሆን የቀብር ስነ ስርዓቱም በመካ በሚገኘው አል ሙአላ እንደሚከናወን ታውቋል :: አላህ ጀነተል ፊርደውስን ይወፍቃቸው ::
Mostrar todo...
Photo unavailableShow in Telegram
ዛሬ ጁምዓ ታላቅ የሆነ እጅግ ጠቃሚ የሆነ የዚያራ ፕሮግራም ተዘጋጅቷል ። የምትችሉ ይህ እድል ተጠቀሙበት ዛሬ ጁምዓ ቢላል መስጅድ ሰግደን Eznet Akal Gudategna Hitsanatina wolajoch Merja Dirjit beethiopia. (እዝነት የኣካል ጉዳተኛ ህፃናት የእንክብካቤ ማእከል) እንገናኝ። በማእከሉ የሚረዱ ህጻናት ማየት የተሳናቸው፣ መስማት የተሳናቸው ፣ መናገር የማይችሉ፣ ራሳቸውን ችለው መቆም ሆነ መቀመጥ የማይችሉ፣ የሚጥል በሽታ ያለባቸው፣ ራሳቸው መመገብ የማይችሉ ወዘተ ተደራራቢ የአካል ጉዳት ያለባቸው ህፃናት ይገኛሉ። እዝነት የምትንከባከባቸው ኣካል ጉዳተኛ ህፃናት ተመልክተን፣ ዱዓ አድርገን፣ የእዝነት አምባሳደር ሆነን እንመለስ። ማእከሉን ለመጎብኘት ስንመጣ በስጦታ መልክ የንጽህና ቁሳቁሶች (ዳይፐር፣ ዋይፕስ፣ ሶፍት፣ ሳሙና ወዘተ) ይዘን በመምጣት በማእከሉ አብረን እናሳልፋለን። ኢንሻአላህ !
Mostrar todo...
Photo unavailableShow in Telegram
ሸይኽ አህመድ አሽ-ሻሚ ይሰኛሉ። ፈቂህ ሙሐዲስና ሙአሪኽ ናቸው። ቀን ቀን በርካታ ተማሪዎችን እያስቀሩ ቀናቸውን ይገፋሉ። ማታ ማታ ለጌታቸው ሱጁድ ወርደው ያ አላህ ሲሉ ያነጋሉ። ከዕለታት በአንዱ ቀን ሽፍታ የቤታቸውን በር አልፎ ወደካዝናቸው አቀና። "ልጄ!" አሉት በትህትና "ልጄ ይህን ገንዘብ አትውሰድብኝ። ሰዎች እኔ ዘንድ ያስቀመጡት አደራ ነው። ከዚህ ውጪ ያሉት የኔ ንብረቶች ናቸውና የፈለከውን መርጠህ ውሰድ" አሉት። ሌባውን ያውቁታል። የሚፈልገውን ኃብት መርጦ ሸክፎ የቤቱን በር አልፎ ወጣ። Mahi mahisho በሁለተኛው ቀን ሸኹ ወደ ሌባው ቤት አቀኑ። በሩን አንኳኩተው ወደ ውስጥ ዘለቁ። "ልጄ ሆይ!" ብለው ተጣሩ። ከፊታቸው ቀረበ። በእጃቸው የያዙትን ተጨማሪ ገንዘብ እያቀበሉት "ለአላህ ብለህ ይቅር በለን እንደቸገርክ እያወቅን የደረሰብክን እያየን በዝምታ አለፍንህ ችግርን መቋቋም ሲያቅትህ የቤተሰብህን ጉሮሮ ለመድፈን ወደ ስርቆቱ ገባህ አፉ በለን ሐቃችንን አልተወጣንምና" ሲሉት በድርጊቱ አፍሮ አቀረቀረ። ዳግም ላይሰርቅ ምሎ ከፊታቸው ተገዘተ። ግንባር ቀደም ፈሪሀ አላህ የሸኹ ደረሳ ለመሆን በቃ። ስታስተምር ጥበብን ከዕዝነት ጋር አዋህደህ ውብ ቃልና ተግባርህን አጣምረህ ይሁን።
Mostrar todo...
👍 2
🛑 የአረፋ ቀን ፆም! ነቢዩ (ﷺ) ስለ አረፋ ቀን ፆም ተጠይቀው እንዲህ ብለዋል፦ “ያለፈውንና የመጪውን አመት ወንጀል ያስምራል።” 📚 ሙስሊም ዘግበውታል: 1162 🛑 የአረፋ ቀን ፆም የሚፆመው ነገ ቅዳሜ ሰኔ 8 ነው። ⚫️ ቀዳ ያለበትም ሰው ቢሆን የዐረፋን ቀን ጾም መጾም ይችላል። ⚫️ ማንኛውም ከነጋ በኋላ ምግብና መጠጥ ያልቀመሰ ሰው ከነጋ በኋላም ቢሆን ነይቶ ጾም መጀመር ይችላል። ነገር ግን ምንዳው የሚጀምረው ከነየተበት ሰዓት ጀምሮ ነው። ⚫️ከ9ኛው ቀን በፊት ምንም ላልጾመ ሰውም ቢሆን 9ኛው ቀን ብቻ መፆም ይቻላል/ችግር የለውም። ⚫️በዐረፋ (9ኛው ቀን) ላይ ይበልጥ የሚወደዱ 3 ዒባዳዎች፣ 1/ ቀኑን መጾም 2/ ዚክር ማብዛት በተለይም ተክቢር 3/ ዱዓእ ማብዛት ⚫️ለዐረፋ ቀን ራሱን የቻለ ዱዓእ የለውም ሁሉም የቻለውንና የሚፈልገውን ዱዓእ ማድረግ ይችላል። 🛑 የአረፋ ቀን ፆም የሚፆመው ነገ ቅዳሜ ሰኔ 8 2016 ነው።
Mostrar todo...
ሁጃጆቻችን ያረፉባት ሚና፤ የምሽት ዕይታ
Mostrar todo...
Photo unavailableShow in Telegram
የአረፋ ቀን ፆም መፆም እንዳትረሳ! ከአቢ ቀታዳ (رضي ﷲ عنه) ተይዞ፡ ነቢዩ (ﷺ) ስለ አረፋ ቀን ፆም ተጠይቀው እንዲህ ብለዋል፦ ﴿يُكَفِّرُ السَّنَةَ الماضِيَةَ والْباقِيَةَ﴾ “ያለፈውንና የመጪውን አመት ወንጀል ያስምራል።” 📚 ሙስሊም ዘግበውታል: 1162 ማስታወሻ፦ የአረፋ ቀን ፆም የሚፆመው ቅዳሜ ሰኔ 8 ነው።
Mostrar todo...
Elige un Plan Diferente

Tu plan actual sólo permite el análisis de 5 canales. Para obtener más, elige otro plan.