es
Feedback
الفوائد/Al fawaid/ አልፈዋኢድ

الفوائد/Al fawaid/ አልፈዋኢድ

Ir al canal en Telegram

السلام عليكم ورحمة الله وبركاته እንኳን ወደ አል-ፈዋኢድ ቻናል በሰላም መጡ! እዚህ የተለያዩ ደርሶችን፣ ማስታወሻዎችን፣ ቲላዋዎችን እና መልእክቶችን ያገኛሉ። ቻናሉን በመከታተል እና ለሌሎች በማስተላለፍ ተጠቃሚ ይሁኑ። "በመልካም ነገር ላይ ያመላከተ እንደ ሰሪው ነው" https://t.me/fawaid_00

Mostrar más
El país no está especificadoLa categoría no está especificada
227
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
Sin datos30 días

Carga de datos en curso...

Canales Similares
Sin datos
¿Algún problema? Por favor, actualice la página o contacte a nuestro gerente de soporte.
Nube de Etiquetas
Sin datos
¿Algún problema? Por favor, actualice la página o contacte a nuestro gerente de soporte.
Menciones Entrantes y Salientes
---
---
---
---
---
---
Atraer Suscriptores
julio '26
julio '26
+107
en 0 canales
junio '260
en 3 canales
Get PRO
mayo '26
+120
en 3 canales
Fecha
Crecimiento de Suscriptores
Menciones
Canales
02 julio+1
Publicaciones del Canal
2
የማለዳ መልእክት #27 አላህ አንድን ባሪያ በሆነ ነገር ሲያዘው ባሪያው ላይ ሰባት(7) ነገሮች ግዴታ ይሆኑበታል 2. ትእዛዙን ወዶ መቀበል/محبته አንድ ሰው አላህ ያዘዘውን ትእዛዝ ወዶ ሊቀበል የከለከለውን ክልከላ ወዶ ሊርቅ ይገባዋል፤ ምክንያቱም አላህ እንዲህ ብሏል፦ «فَلَا وَرَبِّكَ لَا يُؤْمِنُونَ حَتَّىٰ يُحَكِّمُوكَ فِيمَا شَجَرَ بَيْنَهُمْ ثُمَّ لَا يَجِدُوا فِي أَنفُسِهِمْ حَرَجًا مِّمَّا قَضَيْتَ وَيُسَلِّمُوا تَسْلِيمًا» سورة النساء {{በጌታክ እምላለሁ! ሰዎች አላመኑም(አማኝ አይባሉም) በገጠማቸው ጉዳይ አንተን ፈራጅ አድርገው፥ በፈረድከው ነገር ቅር ሳይሰኙ፥ መታዘዝን እስካልታዘዙ ድረስ}} ሡረቱ ኒሳእ #በፈረድክላቸው ነገር ቅር ሳይሰኙ ማለቱ የመልእክተኛውን ውሳኔ ወደን መቀበል እንደሚገባ ያሳያል "ذَٰلِكَ بِأَنَّهُمْ كَرِهُوا مَا أَنزَلَ اللَّهُ فَأَحْبَطَ أَعْمَالَهُمْ»سورة محمد {{አላህ ያወረደውን ነገር(ቁርአንና ድንጋጌውን) በመጥላታቸው ምክንያት አላህ ስራቸውን አበላሸባቸው}} ሡረቱ ሙሓመድ #ለዚህም ሲባል የአላህ መልእክተኛ እንዲህ እያአሉ ዱዓእ ያድርጉ ነበር፦ «اللَّهُمَّ إِنِّي أَسْأَلُكَ حُبَّكَ، وَحُبَّ مَنْ يُحِبُّكَ، وَالْعَمَلَ الَّذِي يُبَلِّغُنِي حُبَّكَ» رواه الترمذى “አላህ ሆይ ውዴታህን፤ አንተን የሚወድን ሰው ውዴታ፤ ወዳንተ የሚያቀርበኝ ስራን ውዴታ እጠይቅሀለሁ" ቲርሚዚይ ዘግበውታል
71
3
የዕለተ ረቡእ የአደብ ተከታታይ ትምህርት ክፍል - 4 الْأَدَبُ الثَّالِثُ: سَمِّ اللهَ فِي ابْتِدَاءِ أَكْلِكَ وَشُرْبِكَ قَائِلًا (بِسْمِ اللهِ)، وَكُلْ بِيَمِنِكَ، وَكُلْ مِمَّا يَلِيكَ، فَإِذَا فَرَغْتَ فَالْعَقْ أَصَابِعَكَ، وَقُلِ (الحَمْدُ للهِ). ሶስተኛው፦ መመገብ ወይም መጠጣት ስትጀምር “ቢስሚላህ” በማለት የአላህን ስም አውሳ፤ በቀኝ እጅክ ተመገብ/ጠጣ፤ ፊት ለፊትክ ካለው ብላ፤ ስትጨርስ ጣቶችህን ላስ፤ “አልሐምዱ ሊላህ” በል። ማብራሪያ፦ ይህ አደብ የአመጋገብ አደብ በመባል የሚጠራ ሲሆን በውስጡ ስድስት(6) ነጥቦችን ይዟል; 1• መመገብ/መጠጣት ከመጀመራችን በፊት የአላህን ስም ማውሳት እንዳለብን; 2• የአላህን ስም ስናወሳ “بِسْمِ الله” በማለት እንደሆነ; -. ይህን ማለት ረስቶ መሀል ላይ ያስታወሰ “بِسْمِ اللهِ فِي أَوَّلِهِ وأَخِرِهِ” ማለት እንደሚችል የመጣ ዘገባ አለ። 3• በቀኝ እጅ መመገብ/መጠጣት እንዳለብን 4• ከፊትለፊታችን ካለው መመገብ እንዳለብን; -. ይሄ አንድ አይነት ምግብ የምንመገብ ከሆነ ነው፤ የተለያየ ምግብ ከሆነ ችግር የለውም። 5• ስጨርስ ጣታችንን መላስ እንዳለብን; -. እንደ ወላጅ እና ልጅ፤ ባልና ሚስት አንዳቸው የአንዳቸውን ጣት ማስላስ ሱና መሆኑን የሚጠቁም ሐዲስ አለ። “الْحَمْدُ للهِ” •6 ማለት እንዳለብን -. ሌሎች ምግብ ሲጠናቀቅ የሚባሉ ዚክሮችንም ማለት ይቻላል። https://t.me/fawaid_00
761
4
የማለዳ መልእክት #26 አላህ አንድን ባሪያ በሆነ ነገር ሲያዘው ባሪያው ላይ ሰባት(7) ነገሮች ግዴታ ይሆኑበታል 1. የታዘዘውን ነገር ማወቅ/العلم አላህ አንድን ባሪያ በሆነ ነገር ሲያዘው; ምንድነው የታዘዝኩት? ለማን ነው የምፈፅመው? መቼና የት?እንዴት? እስከ መች? እና መሰል የሆኑ ነገሮችን ማወቅ ግዴታ ነው። قَالَ اللهُ تَعَلَى: «فَاعْلَمْ أَنَّهُ لَا إِلَٰهَ إِلَّا اللَّهُ وَاسْتَغْفِرْ لِذَنبِكَ وَلِلْمُؤْمِنِينَ وَالْمُؤْمِنَاتِ» سورة محمد: ١٩ “ከአላህ በስተቀር በሐቅ የሚመለክ አለመኖሩን እወቅ! ከዛም ለወንጀልክ፤ ለሙእሚን ወንዶች እና ሴቶች ምህረትን ጠይቅ"ሡረቱ ሙሐመድ: 19 #ቡኻሪ; ይህን አንቀፅ በመደገፍ “እውቀት ከንግግርም ከተግባርም ይቀድማል” ብለዋል። ▶️ አላህ በየቀኑ ሰላታችን ላይ ፋቲሓን እንድንቀራ ያዘዘን ሲሆን ፋቲሓ ውስጥ ደግሞ «وَلَا الضَّالِّينَ» የሚል ቃል አለ፤ #ትርጉሙም፦ “አንተን ያለ እውቀት በመገዛታቸው መንገድን የሳቱትን መንገድ ውጪ ያለን መንገድ ምራኝ” ማለት ነው። ነቢዩ ﷺ በየቀኑ ከፈጅር ቡሀላ ከሚያደርጓቸው ዱዓዎች መካከል; اللَّهُمَّ إِنِّي أَسْأَلُكَ عِلْمًا نَافِعًا، وَرِزْقًا طَيِّبًا، وَعَمَلًا مُتَقَبَّلًا የሚል ሲሆን; “አላህ ሆይ ጠቃሚ እውቀትን፤ መልካም ሲሳይን፤ ተቀባይነት ያለው ስራን እጠይቅካለሁ” ማለታቸው የእውቀትን አስፈላጊነት እና ከስራ በፊት መጠየቃቸው ደግሞ ከስራ በፊት ማወቅ እንደሚቀድም ይጠቁማል። https://t.me/fawaid_00
58
5
የማለዳ መልእክት #25 የሐጅ ምንዳን የሚያስገኙ ተግባራት 7(የመጨረሻ) በረመዷን ዑምራህ ማድረግ عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُمَا، قَالَ: لَمَّا رَجَعَ النَّبِيُّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ مِنْ حَجَّتِهِ قَالَ لِأُمِّ سِنَانٍ الأَنْصَارِيَّةِ: «مَا مَنَعَكِ مِنَ الحَجِّ؟» قَالَتْ: أَبُو فُلاَنٍ - تَعْنِي زَوْجَهَا - كَانَ لَهُ نَاضِحَانِ حَجَّ عَلَى أَحَدِهِمَا، وَالآخَرُ يَسْقِي أَرْضًا لَنَا، قَالَ: «فَإِذَا كَانَ رَمَضَانُ اعْتَمِرِي فِيهِ، فَإِنَّ عُمْرَةً فِي رَمَضَانَ تَقْضِي حَجَّةً مَعِي» رواه البخاريّ ومسلم. ከኢብኑ ዐባስ እንደተወራው እንዲህ አለ፦ «ነቢዩ ﷺ ከሐጅ ጉዟቸው በተመለሱ ጊዜ ለኡሙ ሲናን አል-አንሷሪያህ እንዲህ አሏት፦ “ሐጅ እንዳታደርጊ የከለከለሽ ምንድን ነው?” እሷም፦ “የእገሌ አባት (ባሏን ማለቷ ነው) ሁለት የውሃ ማጠጫ ግመሎች ነበሩት፤ በአንዱ ላይ እሱ (ከነልጁ) ሐጅ አደረገበት፣ ሁለተኛው ደግሞ መሬታችንን ያጠጣበታል (ስለዚህ መጓጓዣ አጣን)” አለች። ነቢዩም ﷺ እንዲህ አሏት፦ “ረመዷን ሲመጣ ኡምራ አድርጊ፤ በረመዷን የሚደረግ ኡምራ ከእኔ ጋር እንደተደረገ ሐጅ ይቆጠራልና (በምንዳው)”።» ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል #ማስታወሻ፦ በተከታታይ ያየናቸው የሐጅ ምንዳን የሚያስገኙ ተግባራት;አንድ ሰው ሐጅ ቢያደርግ የሚያገኘውን አጅር ያስገኛሉ ማለት እንጂ ግድ የነበረበትን ሐጅ ይቀርለታል ማለት አይደለም
757
6
የማለዳ መልእክት #24 የሐጅ ምንዳን የሚያስገኙ ተግባራት - 6 ከግዴታ ሰላት ቡሀላ እነዚህን ዚክሮች ማለት عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُ، أَنَّ فُقَرَاءَ الْمُهَاجِرِينَ أَتَوْا رَسُولَ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ، فَقَالُوا: ذَهَبَ أَهْلُ الدُّثُورِ بِالدَّرَجَاتِ الْعُلَى، وَالنَّعِيمِ الْمُقِيمِ. فَقَالَ: «وَمَا ذَاكَ؟» قَالُوا: يُصَلُّونَ كَمَا نُصَلِّي، وَيَصُومُونَ كَمَا نَصُومُ، وَيَتَصَدَّقُونَ وَلَا نَتَصَدَّقُ، وَيُعْتِقُونَ وَلَا نُعْتِقُ. فَقَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ: «أَفَلَا أُعَلِّمُكُمْ شَيْئًا تُدْرِكُونَ بِهِ مَنْ سَبَقَكُمْ وَتَسْبِقُونَ بِهِ مَنْ بَعْدَكُمْ؟ وَلَا يَكُونُ أَحَدٌ أَفْضَلَ مِنْكُمْ إِلَّا مَنْ صَنَعَ مِثْلَ مَا صَنَعْتُمْ؟» قَالُوا: بَلَى يَا رَسُولَ اللَّهِ. قَالَ: «تُسَبِّحُونَ، وَتَحْمَدُونَ، وَتُكَبِّرُونَ، خَلْفَ كُلِّ صَلَاةٍ ثَلَاثًا وَثَلَاثِينَ مَرَّةً» (رواه البخاري ومسلم) ከአቡ ሁረይራ (ረዲየላሁ አንሁ) እንደተወራው፡ የሙሃጅር ድሆች ወደ አላህ መልክተኛﷺ መጥተው እንዲህ አሉ፦ “ባለሀብቶች እኮ ከፍተኛውን ደረጃና ዘላቂውን ፀጋ ይዘውት ሄዱ።” የአላህ መልክተኛምﷺ ፦ “ምንድነው እሱ?” አሏቸው። እነሱም፦ “እኛ እንደምንሰግደው ይሰግዳሉ፣ እኛ እንደምንጾመው ይጾማሉ፣ (ነገር ግን) እነሱ ይመጸውታሉ እኛ አንመጸውትም፣ እነሱ ባሪያ ነጻ ያወጣሉ እኛ ግን ማውጣት አንችልም (በገንዘባቸው በላጩን ስራ ሰሩ)” አሉ። የአላህ መልክተኛምﷺ እንዲህ አሉ፦ “ከእናንተ በፊት የቀደሟችሁን የምታገኙበት፣ ከእናንተ በኋላ የሚመጡትን የምትቀድሙበት፣ እንዲሁም እናንተ የሰራችሁትን የሰራ ካልሆነ በስተቀር ማንም ከእናንተ በላይ በላጭ የማይሆንበትን ነገር ላስተምራችሁን?” እነሱም፦ “አዎን ያስተምሩን የአላህ መልክተኛ ሆይ!” አሉ። እሳቸውምﷺ ፦ “ከእያንዳንዱ ሶላት በኋላ ሰላሳ ሶስት (33) ጊዜ ‘ሱብሀነላህ’፣ ‘አልሀምዱሊላህ’፣ ‘አላሁ አክበር’ በሉ።” (ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)
670
7
የማለዳ መልእክት #23 የሐጅ ምንዳን የሚያስገኙ ተግባራት - 5 ዒልምን ለመማር/ለማስተማር ወደ መስጂድ መሔድ عَنْ أَبِي أُمَامَةَ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُ، عَنِ النَّبِيِّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ: "مَنْ غَدَا إِلَى الْمَسْجِدِ لَا يُرِيدُ إِلَّا أَنْ يَتَعَلَّمَ خَيْرًا أَوْ يُعَلِّمَهُ، كَانَ لَهُ كَأَجْرِ حَاجٍّ تَامٍّ حِجَّتُهُ"رواه الطبراني والحاكم. ከአቢ ኡማማህ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንደተላለፈው፤ ከነቢዩﷺ አስተላልፈው እንዲህ አሉ። «መልካምን ነገር ለመማር ወይም ለማስተማር ብቻ አስቦ ወደ መስጂድ የሔደ ሰው፤ ሐጁ ሙሉ የሆነለትን የሐጅ ተጓዥ ምንዳ ያገኛል»ጦበራኒይ እና ሓኪም ዘግበውታል
540
8
የዕለተ ማክሰኞ የፊቅህ ተከታታይ ትምህርት - 5 የሰላት ምእራፍ ሰላት ማለት፦ በውስጡ ንግግር እና ተግባርን የያዘ በተክቢረተል ኢሕራም ተጀምሮ በተስሊም የሚጠናቀቅ ዒባዳ ነው። በነቢዩ ኡመት(ህዝብ) ላይ 5 ሰላቶች በግዴታነት የተደነገጉ ሲሆን; እነሱም፦ ፈጅር፦ ሁለት ረከዓ ይሰገዳል ዙህር፦ አራት ረከዓ ይሰገዳል ዐስር፦ አራት ረከዓ ይሰገዳል መግሪብ፦ ሶስት ረከዓ ይሰገዳል ዒሻእ፦ አራት ረከዓ ይሰገዳል #ሰላትን የተወ ሰው; አንድ ሰው ሰላትን ትቷል የሚባለው፦ ከአምስቱ ሰላቶች አንዱን ሰላት ሆን ብሎ ካልሰገደ፤ ሶስቱን ሰላቶች ሆን ብሎ ካልሰገደ፤ አምስት ወቅት ሰላት(የአንድ ቀን) ሆን ብሎ ካልሰገደ፤ የአንድ ሳምንት ሰላት ሆን ብሎ ካልሰገደ፤ የሶስት ተከታታይ ሳምንት ሰላት ሆን ብሎ ካልሰገደ፤ “እሱ አይሰግድም” በሚያስብለው ደረጃ/ በቁጥር ወይም በቀን ሳይገደብ ሆን ብሎ ካልሰገደ ነው በማለት ዑለሞች የተለያዩ አስተያየቶችን ያስቀመጡ ሲሆን; በዚህ መሰረት ሰላትን የተወ ሰው፦ ትክክለኛው አቋም ይከፍራል/ከእስልምና ይወጣል። #ለዚህም የተለያዩ ማስረጃዎችን መጥቀስ የሚቻል ከመሆኑ ጋር ለአብነት ያክል፦ «ሰላትን ቀጥ አርጋችሁ ስገዱ፤ ከአጋሪዎች እንዳትሆኑ» ሡረቱል አንከቡት «በአንድ ሰው እና በሺርክና ኩፍር መሀል ያለው ሰላትን መተዉ ነው»ሙስሊም ዘግበውታል https://t.me/fawaid_00
534
9
የማለዳ መልእክት #22 የሐጅ ምንዳን የሚያስገኙ ተግባራት - 4 ፈጅርን በጀመዓ ሰግዶ ፀሀይ እስከምትወጣ ዚክር እያረጉ መቆየትና ሁለት ረከዓ መስገድ عَنْ أَنَسِ بْنِ مَالِكٍ قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ: «مَنْ صَلَّى الْغَدَاةَ فِي جَمَاعَةٍ ثُمَّ قَعَدَ يَذْكُرُ اللَّهَ حَتَّى تَطْلُعَ الشَّمْسُ، ثُمَّ صَلَّى رَكْعَتَيْنِ كَانَتْ لَهُ كَأَجْرِ حَجَّةٍ وَعُمْرَةٍ، تَامَّةٍ تَامَّةٍ تَامَّةٍ» (رواه الترمذي) ከአነስ ኢብኑ ማሊክ በተላለፈ ሐዲስ እንዲህ ብሏል: የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ብለዋል: «የጠዋቱን(የፈጅርን) ሰላት በጀመዓ የሰገደ፤ ከዛም ፀሀይ እስከምትወጣ ድረስ ዚክር እያደረገ የተቀመጠ፤ ከዛም ሁለት ረከዓ የሰገደ፤ የተሟላ፤ የተሟላ፤ የተሟላ ሓጅ እና ዑምራ እምደፈፀም ይቆጠርለታል.» ቲርሚዚይ ዘግበውታል. ማስታወሻ፦ -. ሴቶች ቤታቸው ለብቻቸው ሰግደው፤ በሰገዱበት ቦታ ዚክር እያደረጉ ቆይተው፤ ፀሀይ ስትወጣ ሁለት ረከዓ ቢሰግዱ ይህን አጅር ያገኛሉ። -. ዚክር የሚባለው፦ ቁርአን መቅራት፤ ዒልምን መማር/ማስተማር፤ ዱዓእ ማድረግ፤ ሌሎች ዚክሮችን ማድረግን ያካትታል።
504
10
የዕለተ ሰኞ የዓቂዳ ተከታታይ ትምህርት ክፍል - 5 نواقض الإسلام - እስልምናን የሚያበላሹ ተግባራት النَّاقِضُ الثَّالِثُ: مَن لَّمْ يُكَفِّرِ الْمُشْرِكِينَ أَوْ شَكَّ فِي كُفْرِهِمْ أَوْ صَحَّحَ مَذْهَبَهُمْ كَفَرَ إِجْمَاعًا. 3ኛው እስልምናን የሚያበላሽ ተግባር: “ሙሽሪኮችን የማያከፍር፤ ወይም ካፊር መሆናቸውን የተጠራጠረ፤ ወይም መንገዳቸውን ትክክል ነው ያለ; በዑለሞች ስምምነት መሰረት ይከፍራል።” ይቀጥላል…. #ይህ እስልምናን የሚያበላሽ ተግባር በውስጡ ሶስት ነገሮች ይዟል; #1ኛ. «مَن لَّمْ يُكَفِّرِ الْمُشْرِكِينَ» ሙሽሪኮችን የማያከፍር እራሱ ይከፍራል የሚለው አ.ነገር ሲሆን; ሙሽሪክ የሚባሉት በቁርአን እና በሐዲስ ሙሽሪክ ተብለው የተገለፁ እንደ አህለል ኪታቦች፣ ሀይማኖት የሌላቸው ሰዎችና ሌሎችም ሰዎችን ነው። #አንድ ሰው ላ ኢላሀ ኢለላህ ሲል; ሁለት ነገሮች ግድ ይሉታል; 1ኛ. ላ ኢላሀ፦ አምላክ የሚባሉ ማንኛቸውንም መካድ እና 2ኛ. ኢለላህ፦ አምልኮን ለአላህ ብቻ መስጠት ሙሽሪኮች/ካፊሮችን የማያከፍር ሰው በ1ኛው( አምላክ የሚባሉ ማንኛቸውንም መካድ) የሚለውን አጉድሏል። #2ኛ. «شَكَّ فِي كُفْرِهِمْ» ሙሽሪኮች ካፊር ናቸው ወይስ በሚለው የተጠራጠረ የሚለው አ.ነገር ሲሆን; ይህን የፈፀመ ሰው ከ8ቱ የላ ኢላሀ ኢለላህ መስፈርቶች አንዱ የሆነውን “እርግጠኝነት” አጉድሏል። እርግጠኝነት፦ ማለት አንድ ሰው ላ ኢላሀ ኢለላህ ሲል; ከአላህ ውጪ በሐቅ የሚመለክ አለመኖሩን እርግጠኛ መሆን አለበት ማለት ነው፤ ስለዚህ ሙሽሪኮች በአላህ መካዳቸውን የተጠራጠረ ሰው ከአላህ ውጪ በሐቅ የሚመለክ መኖሩን ተጠራጥሯል ማለት ነው። #3ኛ. «صَحَّحَ مَذْهَبَهُمْ» መንገዳቸውን(የሙሽሪኮቹን) ትክክል ነው ያለ ሰው ይከፍራል ማለት ሲሆን; ይህም “አላህ ዘንድ ትክክለኛው ሀይማኖት እስልምና ነው” የሚለውን የቁርአን አንቀፅ ማስተባበል ይሆናል። https://t.me/fawaid_00
594
11
📌 التَّكْبِيرُ الْجَمَاعِيُّ دُبُرَ الصَّلَوَاتِ عِنْدَ عُلَمَاءِ الْمَالِكِيَّةِ: قَالَ الْحَطَّابُ: (وَأَمَّا مَا يَفْعَلُهُ بَعْضُ النَّاسِ الْيَوْمَ أَنَّهُ إِذَا سَلَّمَ الْإِمَامُ مِنْ صَلَاتِهِ كَبَّرَ الْمُؤَذِّنُونَ عَلَى صَوْتٍ وَاحِدٍ عَلَى مَا يُعْلَمُ مِنْ زَعَقَاتِهِمْ، وَيُطَوِّلُونَ فِيهِ، وَالنَّاسُ يَسْتَمِعُونَ إِلَيْهِمْ وَلَا يُكَبِّرُونَ فِي الْغَالِبِ، وَإِنْ كَبَّرَ أَحَدٌ مِنْهُمْ فَهُوَ يَمْشِي عَلَى أَصْوَاتِهِمْ، وَذَلِكَ كُلُّهُ مِنَ الْبِدَعِ، وَفِيهِ إِخْرَامُ حُرْمَةِ الْمَسْجِدِ، وَالتَّشْوِيشُ عَلَى الْمُصَلِّينَ وَالتَّالِينَ وَالذَّاكِرِينَ) 📚 ((مَوَاهِبُ الْجَلِيلِ)) (2/582). وَقَالَ الْعَدَوِيُّ: (وَيُكَبِّرُ كُلُّ وَاحِدٍ وَحْدَهُ فِي الطَّرِيقِ، وَفِي الْمُصَلَّى، وَلَا يُكَبِّرُونَ جَمَاعَةً؛ لِأَنَّهُ بِدْعَةٌ) 📚((حَاشِيَةُ الْعَدَوِيِّ)) (1/497). وَقَالَ النَّفْرَاوِيُّ: (وَلَا يُكَبِّرُونَ جَمَاعَةً؛ لِأَنَّهُ بِدْعَةٌ) 📚 ((الْفَوَاكِهُ الدَّوَانِي)) (2/649). 📌 በማሊኪያ ዑለሞች (ሊቃውንት) ዘንድ ከሶላት በኋላ በጋራ (በአንድ ድምፅ) ተክቢራ ማድረግ፡ አል-ሐጧብ እንዲህ ይላሉ፦ (“ዛሬ በአሁኑ ጊዜ አንዳንዶች የሚያደርጉት ነገር፤ ኢማሙ ከሶላቱ አሰላምቱ እያለ ሲያበቃ፣ ሙአዚኖቹ ከጩኸታቸው እንደሚታወቀው በአንድ ድምፅ ተክቢራ ያደርጋሉ፣ ያረዝሙታልም። ሰዎቹም እነሱን ያዳምጣሉ እንጂ በአብዛኛው አብረው ተክቢራ አያደርጉም። ከነሱ መካከል ተክቢራ የሚያደርግ ቢኖርም እንኳ በነሱ ድምፅ እየተመራ (እየተከተለ) ነው። ይህ ሁሉ ከቢድዓ (በዲን ውስጥ ከተፈጠሩ አዳዲስ ነገሮች) ይመደባል፤ በውስጡም የመስጂድን ክብር መድፈር፣ እንዲሁም ሶላት ሰጋጆችን፣ ቁርኣን ቀሪዎችንና ዚክር አድራጊዎችን መረበሽ አለበት።”) 📚 ((መዋሂቡል ጀሊል)) (2/582) አል-ዐደዊ እንዲህ ይላሉ፦ (“እያንዳንዱ ሰው በመንገድ ላይም ሆነ በሶላት መስገጃ ቦታ (ሙሶላ) ላይ ለየብቻው ተክቢራ ያደርጋል፤ በቡድን (በጋራ) ግን ተክቢራ አያደርጉም፣ ምክንያቱም እሱ ቢድዓ ነው።”) 📚 ((ሐሺየቱል ዐደዊ)) (1/497) አን-ነፍራዊ እንዲህ ይላሉ፦ (“በጋራ ተክቢራ አያደርጉም፤ ምክንያቱም እሱ ቢድዓ ነው።”) 📚 ((አል-ፈዋኪሁ አድ-ደዋኒ)) (2/649)
741
12
Sin texto...
624
13
🔅 የተወሰኑ የኡድሑያ ሕግጋት ▪️ አስተራረድ ✔️ ቢላዋውን አንገቱ ላይ ከመጫኑ በፊት የግድ "ቢስሚላህ" ማለት አለበት። ሱናውን ሙሉ ለማድረግ ግን የሚከተለውን ይላል፡- "ቢስሚላሂ ወላሁ አክበር" (በአላህ ስም፣ አላህ ታላቅ ነው) "አላሁማ ሀዛ ሚንከ ወለከ"፣ (ትርጉም፦ አላህ ሆይ! ይህ ካንተ የተገኘ (ጸጋ) ነው፣ ላንተም የተደረገ ነው። ✔️በውክልና ከሆነ ደግሞ "ቢስሚላሂ ወላሁ አክበር" (በአላህ ስም፣ አላህ ታላቅ ነው) "አላሁማ ሀዛ ሚንከ ወለከ፣ አላሁማ ተቀበል ሚን [የወካይ ስም]" (ትርጉም፦ አላህ ሆይ! ይህ ካንተ የተገኘ (ጸጋ) ነው፣ ላንተም የተደረገ ነው፤ አላህ ሆይ! ከእገሌ [የወካይ ስም] ተቀበለው):: ▪️ የኡድሒያ ስጋ አከፋፈል ✔️ ኡድሒያ ካረዱ በኋላ ስጋውን ሙሉ በሙሉ መብላትም፣ ሁሉንም ሰደቃ ወይም ስጦታ መስጠትም ይቻላል። ነገር ግን ሶስት ቦታ አካፍሎ መብላት፣ ለአቅመ-ደካማ ሰደቃ መስጠትና ለወዳጅ ዘመድ ስጦታ ማበርከቱ ይወደዳል። ምንም እንኳ በቂና ግልጽ መረጃ ባይኖረውም በርካታ ሊቃውንት ትንሽም ቢሆን ለአቅመ ደካማ መስጠት ግዴታ ነው ስለሚሉ ሰደቃ መስጠቱ ባይቀር ይመረጣል። ✔️ በዛ ያለ ቤተሰብ ያለበትና ስጋ የሚያንሰው አባወራ ማካፈሉን ትቶ ሙሉውን ለቤተሰቡ ማድረጉ እንደሚሻል ኢብራሂም አል-ሐለቢይ የሚባሉት የፊቅህ ሊቅ ገልጸዋል። ▪️ የኡድሒያን ቆዳ መሸጥ ይቻላልን? ኡድሒያ የሚታረደው ወደ አላህ ለመቃረብ ነው! ስጋውን ለሶስት ከፍሎ፥ አንድ ሶስተኛውን ለቤት፣ አንድ ሶስተኛውን በስጦታ መልኩ ለዘመድ፣ ለጎረቤትና ለጓደኛ፤ አንድ ሶስተኛውን ሳይበስል ለአቅመ-ደካሞች መስጠቱ የጠበቀ ሱና ነው። ✔️ የኡድሒያውን ቆዳም ይሁን ሌላ ነገር ሽጦ ገንዘቡን መጠቀም ወይም በገንዘቡ ፋንታ ለሰራተኛ መስጠት አይቻልም! ቆዳውን ሳይሸጡ ለራስ መጠቀም ወይም ለአቅመ ደካማ በነጻ-ሰደቃ- መስጠት ግን ይቻላል። ዛዱል መዓድ https://telegram.me/ahmedadem
104
14
Sin texto...
721
15
የዕለተ ማክሰኞ የፊቅህ ተከታታይ ትምህርት - 4 #ትጥበት ማለት፦ ሸሪዓው በደነገገው መልኩ ሰውነት ላይ ውሀን መጠቀም ነው። ትጥበትን ግድ የሚያደርጉ ነገሮች ከሶስቱ አንዱ የተከሰተበት/ባት ሰው/ሴት ትጥበት ግድ ይለዋል/ይላታል። 1ኛ የዘር ፈሳሽ መፍሰስ 2ኛ ፆታዊ ግንኙነት ማድረግ 3ኛ ሀይድ/ የወሊድ ደም(ኒፋስ) መፍሰስ የዉዱእ እና ትጥበት ጥቅሞች የዉዱእ እና ትጥበት ጥቅሞች ብዙ ናቸው፤ ዋና ዋናዎቹም፦ 1. እስልምና መንፈሳዊም አካላዊም ንፅህናን የያዘ መሆኑን ያሳያል 2. ወንጀልን ያስምራል 3. የሰውነት ጤና እና ንፅህና እንዲሁም ንቃትን ይሰጣል 4. ከአላህ ጋር በምንገናኝ ጊዜ ባማረ ሁኔታ ላይ ሆነን እንድንገናኝ…
523
16
የማለዳ መልእክት #21 የሐጅ ምንዳን የሚያስገኙ ተግባራት - 3 ለወላጆች መልካምን መዋል عَنْ أَنَسِ بْنِ مَالِكٍ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُ قَالَ: أَتَى رَجُلٌ رَسُولَ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ، فَقَالَ: إِنِّي أَشْتَهِي الْجِهَادَ وَلَا أَقْدِرُ عَلَيْهِ، قَالَ: «هَلْ بَقِيَ مِنْ وَالِدَيْكَ أَحَدٌ؟» قَالَ: أُمِّي، قَالَ: «فَاتَّقِ اللَّهَ فِيهَا، فَإِذَا فَعَلْتَ ذَلِكَ فَأَنْتَ حَاجٌّ، وَمُعْتَمِرٌ، وَمُجَاهِدٌ». (رواه أبو يعلى والطبراني) ከአነስ ኢብኑ ማሊክ በተላለፈ ሐዲስ; እንዲህ ብሏል: «አንድ ሰው የአላህ መልእክተኛ ﷺ ጋር መጣና; እኔ ጂሀድ መሳተፍ እፈልጋለሁ ግን አቅሙ የለኝም አላቸው፥ እሳቸውም ﷺ " ከወላጆችክ (በህይወት)የቆየ አለን?” አሉት፤ እናቴ አለች አላቸው፤ እሳቸውም ﷺ “በሷ(በእናትክ) ጉዳይ አላህን ፍራ፤ ይህን ካደረክ አንተ ሀጅ ያደረገ፤ ዑምራ ያደረገ፤ እና በአላህ መንገድ ላይ የተዋጋ ሰው ነክ” አሉት» አቡ የዕላ እና ጦበራኒይ ዘግበውታል
535
17
የዕለተ ሰኞ የዓቂዳ ትምህርት ክፍል - 4 نواقض الإسلام - እስልምናን የሚያበላሹ ተግባራት የኪታቡ ፀሓፊ- ሸይኽ ሙሀመድ ኢብኑ ዐብዲልወሃብ النَّاقِضُ الثَانِي: مَن جَعَلَ بَيْنَهُ وَبَيْنَ اللهِ وَسَائِطَ، يَدْعُوهُمْ، وَيَسْأَلُهُمُ الشَّفَاعَةَ، وَيَتَوَكَّلُ عَلَيْهِمْ كَفَرَ إِجْمَاعًا. 2ኛው እስልምናን የሚያበላሽ ተግባር፦ ከአላህ እና ከእሱ መካከል ወሳኢጥ ያደረገ; እነሱን(ወሳኢጦቹን) የሚለምን፤ ምልጃ(ሸፋዓህ) የሚጠይቅ፤ በነሱ የሚመካ ሰው; በሁሉም ዑለሞች ስምምነት መሰረት ከእስልምና ይወጣል(ይከፍራል)። #ባለፈው ሳምንት እንዳየነው ከአላህ ውጪ ያሉ አካላትን ወደ አላህ መቃረቢያ(وَسَائِط) አድርጎ መያዝ ሁለት አይነት ነው፦ 1ኛ. የአላህን ትእዛዝ በመፈፀም ወደሱ ለመቃረብ፦ የነቢያትን እና የወራሾቻቸውን(ዑለሞች) ትምህርቶች በመማር በተማርነው እየሰራን ወደ አላህ ስንቃረብ፥ እነዚህ አካላት(ነቢያት ፣ ዑለሞች) በኛ እና በአላህ መካከል (وَسَائِط)/ የሚያቃርቡ ይባላሉ። #ይህ አይነቱ ወደ አላህ መቃረብ ሸሪዓችን የደነገገው ሲሆን; ይሄን መቃወም ከእስልምና ያስወጣል። 2ኛ. ከአላህ ውጪ ያሉ አካላትን በመለመን፤ ሸፈዓ(ምልጃ) በመጠየቅ፤ በኑ በመመካት… ወደ አላህ መቃረብ፦ ይህ ተግባር ለአላህ ብቻ የሚገቡ አምልኮዎችን(ዱዓ፣ ሸፈዓ፣ተወኩል…) ከአላህ ውጪ ላሉ አካላት መስጠት ስለሆነ የሚያከፍር ተግባር ነው። #ወደ አላህ መቃረብ የሚቻልባቸው መንገዶች የሚከተሉት ናቸው፦ 1. አላህን በስሞቹ እና በመገለጫዎቹ በመለመን 2. መልካም ስራን በመስራት ወደ አላህ መቃረብ 3. አላህ ለባሮቹ የዋለውን ውለታ በማውሳት ወደ አላህ መቃረብ; (ሙሳን ከፊርአውን ነፃ ያወጣኸው አላህ እኔንም….) 4. የሰራናቸውን መልካም ስራዎች በማውሳት ወደ አላህ መቃረብ; (እኔ ባለፈው እንዲህ ያደረኩት ላንተ ብዬ ከነበረ ይህን አርግልኝ…) 5. በህይወት ያሉ ሰዎች ዱዓእ ከዚህ ውጪ የሞቱም ይሁኑ በህይወት ያሉ ሰዎችን ወደ አላህ አቃርቡኝ ማለት ሺርክ ሲሆን፤ አላህን በነሱ ይሁንብክ እያሉ መጠየቅ ደግሞ ቢድዓህ ነው።
558
18
የማለዳ መልእክት #20 የሐጅ ምንዳ የሚያስገኙ ተግባራት - 2 ሰዎችን ሐጅ እንዲያደርጉ መምከር፣ ማነሳሳትና መገፋፋት عَنْ أَبِي مَسْعُودٍ عُقْبَةَ بن عَمْرٍو الْأَنصَارِيِّ رضي الله عنه قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللهِ ﷺ : «مَنْ دَلَّ عَلَى خَيْرٍ فَلَهُ مِثْلُ أَجْرِ فَاعِلِهِ» رواه مسلم. ከአቢ መስዑድ ዑቅበተ ብኒ ዓሚር አልኣንሷሪይ በተላለፈ ሐዲስ; እንዲህ ብሏል: የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል: «ወደ መልካም ነገር ያመላከተ ሰው (መልካሙን ነገር) የሰራውን ሰውዬ አጅር ያገኛል።» ሙስሊም ዘግበውታል። ማስታወሻ፦ (መልካሙን ነገር) የሰራውን ሰውዬ አጅር ያገኛል ሲባል፦ መልካሙን ነገር የሰራው ሰውዬ ምንም አያገኝም ወይም አጅሩን ያካፍለዋል ማለት አይደለም፤ ይልቁንም መልካሙን ነገር ያመላከተውም የሰራውም ሙሉ ሙሉ አጅር ያገኛሉ ማለት ነው የተፈለገበት።
520
19
የማለዳ መልእክት #19 የሐጅ ምንዳ የሚያስገኙ ተግባራት - 1 ሐጅ ለማድረግ ትክክለኛ ኒያ ማድረግ عَنْ أَبِي كَبَشَةَ عُمَر بن سَعدٍ الأَنمَاري رَضِيَ اللهُ عَنْهُ أنَّهُ سَمِعَ رَسُولَ اللهِﷺ يَقُولُ: «إِنَّمَا الدُّنْيَا لِأَرْبَعَةِ نَفَرٍ: عَبْدٍ رَزَقَهُ اللهُ مَالًا وَعِلْمًا، فَهُوَ يَتَّقِي فِيهِ رَبَّهُ، وَيَصِلُ فِيهِ رَحِمَهُ، وَيَعْلَمُ لِلَّهِ فِيهِ حَقًا، قَهَذَا بِأَفْضَلِ الْمَنَازِلِ. عَبْدٍ رَزَقَهُ اللهُ عِلْمًا وَلَمْ يَرْزُقْهُ مَالًا، فَهُوَ صَادِقُ النِّيَّةِ يَقُولُ: لَوْ أنَّ لِي مَالًا لَعَمِلْتُ بَعَمَلِ فُلَانٍ، فَهُوَ بِنِيَّتِهِ فَأَجْرُهُمَا سَوَاءٌ.» الحديث.أخرجه الترمذي وابن ماجة وأحمد. ከአቢ ከበሸተ ዑመር ኢብኑ ሰዕድ አልአንማሪይ በተላለፈ ሐዲስ; እሱ የአላህን መልእክተኛﷺ እንዲህ ሲሉ ሰምቷቸዋል: «ዱንያ ለአራት አይነት ሰዎች ትከፈላለች: አላህ ገንዘብን እማ ጠቃሚ እውቀትን የሰጠው አለ; ይህ ሰው በገንዘቡ አላህን ይፈራበታል፤ ዝምድናን ይቀጥልበታል፤ በገንዘቡ ውስጥ አላህ ያለውን ሐቅ ያውቃል፤ ይሄ ከሁሉም በላጭ ደረጃ ነው ያለው። ሌላኛው ባሪያ አላህ ጠቃሚ እውቀትን ብቻ ይሰጠዋል ገንዘብ እይሰጠውም; እሱም በትክክለኛ ኒያ “አላህ ገንዘብ ቢሰጠኝ እንደ እገሌ አይነት ስራ እሰራበት ነበር ይላል፤ ይሄ ሰው በኒያው ከላይኛው ሰወዬ ጋር አጅራቸው እኩል ነው።» ቲርሚዚይ፣ ኢብኑ ማጀህ እና አሕመድ ዘግበውታል. ማስታወሻ፦ በገንዘቡ አላህን ይፈራበታል ማለት፦ አላህ በገንዘቡ እንዲፈፅም ያዘዘውን ይፈፅማል እእዲከለከል ያዘዘውን ይከለከላል ማለት ነው። በገንዘቡ ውስጥ አላህ ያለውን ሐቅ ያውቃል ማለትም፦ ገንዘቡ የሱ ሳይሆን የአላህ መሆኑን አውቆ ገንዘቡን አላህ አውጣ ባለው ቦታ(እንደ ዘካ፣ ሐጅ እና ወ.ዘ.ተ) ያወጣል ማለት ነው። በዚህ ሐዲስ መሰረት; አንድ ሰው ገንዘብ ባይኖረውም ትክክለኛ ኒያ ኖሮት ገንዘብ ያለው ሰው የሚፈፅመውን ተግባር ከተመኘ; የዛን መልካም ስራ ምንዳ ያገኛል ማለት ነው። ከመልካም ስራዎች መካከል አንዱ ሐጅ በመሆኑ ገንዘብ ባይኖረንም ሐጅ የማድረግ ትክክለኛ ኒያ እና ምኞት ሊኖረን ይገባል።
587
20
የማለዳ መልእክት #18 ዚክር ﴿فَٱذْكُرُونِيٓ أَذْكُرْكُمْ وَٱشْكُرُوا۟ لِي وَلَا تَكْفُرُونِ﴾ (سورة البقرة: ١٥٢) {አስታውሱኝ አስታውሳችኋለሁ፤ አመስግኑኝ! በኔ አትካዱ}ሡረቱል በቀራህ: 152 ማስታወሻ፦ የአላህ ማስታወስ; ከመላኢኮቹ ጋር ስማችንን ማውሳት፤ በሚገጥሙን ጉዳዮች አጋዥ እና የሚረዳ መሆንን ያካትታል
114