Never give up
Ir al canal en Telegram
Mostrar más
El país no está especificadoLa categoría no está especificada
473
Suscriptores
+124 horas
+107 días
+930 días
Archivo de publicaciones
#የጸሎት_ለውጥ°°°
ለፍተህ ጥረህ ብላ
የሚል ትዕዛዝህን ህግህ ተከትዬ፤
እጠባበቃለሁ
የማጥመጃ መረብ ከባህሩ ጥዬ፤
እንግዲያው ፈጣሪ
የኔ አቅም ይህቺ ነች፤
ገመድ አጠላልፎ
ባህር ላይ ከመጣል በላይ ያልዘለለች፤
በል ጸሎቴን ስማ...
በጣልኩት መረብ ላይ የዓሳ ዘር ይሙላ፤
ወገኔ ይደሰት እስኪጠግብ ይብላ፤
..
ብዬህ ነበር
..
አሁን ግን...
የጣልኩትን መረብ መልሼ ሰበሰብኩ፤
ጠግቤ ለማደር ሌላ መንገድ አሰብኩ፤
ምክንያቱም..
እኔ መረብ ጥዬ
ዓሣ ስጠኝ እያልኩ እየተማፀንኩኝ፤
ከመረብ ጠብቀኝ
ብሎ የፀለየውን ዓሣውን አሰብኩኝ፤
...
የባህሩ ዓሣ
እንዲህ ሲለምንህ እኔ እሱን ባጠምደው፤
ያንተን ጠባቂነት ነውና ማወርደው፤
ስለዚህ አምላኬ…
አዲሱን ልመና ፀሎቴን አድምጠኝ፤
የነፍሳትን ፀሎት
ማይጋፋ እንጀራ ምረጥና ስጠኝ።
እመነኝ ወዳጄ
ከዘንድሮ ፍቅርህ ያየችው ከሚያምራት
የትላንቷ ሚሚ
የቃቃነት ሚስትህ ሲበዛ ታማኝ ናት
ትዳር መያዝ ካሻህ
እሷኑ ፈልገህ እቤትህ አስገባት፡፡
የፍቅር ሞት !
ለካ ለዚህ ነበር ከአርያም የመጣህ፣
ጥፋት ሳይኖርብህ ለእኛ የተቀጣህ።
፡
...ግን እኔ የምልህ...
፡
ለፍቅር፥ ሞተህ ተቀብረሃል፣
ትውልዱ፥ ፍጹም አፍቅሮሃል፤
በሞት ማግኘት አለ፤ ብለህ ካስተማርከን፣
አንተ ሞተህልን እኛን ካገኘኸን፤
፡
ታድያ አምላኬ ሆይ፤ ሞት ፍቅር ካለው፣
እኔንስ ከሞትኩኝ እሷን¹ አገኛለው?
ይድረስ #ለኢየሱስ_ክርስቶስ
ምሽት በረንዳ ላይ
አገር ምድሩ መሽቶ
ሌቱ ምጣድ ሆኖ ፥ በኮከብ ተሟሽቶ
የጎዳናው መብራት ፥ጨለማው ላይ ሲገን
ከመስኮት አምልጦ ፥የወጣ ወጋንን
ሳር ቅጠሉን ሲያሳይ
አጥብቄ ስፈልግ ፥የእለት ያይኔን ሲሳይ
የሌት አይኔን ሲሳይ
በኩርማን ገላዋ፤ እራፊ ደርባ
የራሷ ሻጭ ሆና ፤ለሸመታ ቀርባ
በሌት ይፋ ሆና፥ በቀን ልትደበቅ
ያልቀጠረችውን ፥የምትጠባበቅ
አንዲት ሴት እያየሁ
አሰላስላለሁ ፤
“ አብረዋት ያደጉ፤ ብጤዎቿ ሁሉ
በድሜና በውበት እሷን የሚያክሉ
ተድረው እንደ ሴት፥ ተከብረው እንደ ሰው
የባሎቻቸውን ደረት ተንተርሰው
ፍቅር ሲያጣጥሙ
ወይ በንቅልፍ ሲሰጥሙ
ይች ወገን አልባ
የሌሊት አበባ
በቀትር ተኝታ ለውድቅት የነቃች
የቱን ፍሬ በልታ ለዚህ ፍዳ በቃች ?”
እያልሁ አስባለሁ፥
ደሞ ከደጃፌ ትንሽ ማዶ ርቆ
የመሸበት ለማኝ ፤ መንገዱ ዳር ወድቆ
በግልጥ ይታየኛል
“ ረፍትን ላክልኝ ፥ወይ እንጎቻህን ጣል
በራብ እና በንቅልፍ ሰው እንዴት ይቀጣል"
የሚል ይመስለኛል ፤
በረንዳ ላይ ቆሜ፥ በሌሊት ስምሪት
ከመስኮት በወጣ፥ የብርሀን ቅሪት
አይቼ ማልዘልቀው
ያገሬ ጎዳና የት ላይ ነው የሚያልቀው
መከራና ውበት የሚያፈራርቀው::
ሠሚ ያጣ ግጥም
እስቲ ልግጠምልህ
ከመድረክ ወጥቼ ልንጎራደድልህ
መድረኩ ይሰየም
አንተም በዛ ክተም
ፍቅሬን ልግለፅልህ
ብዬ ብጠራህም....................
ግጥም የት አባቱ
ጠፋብኝ ዉበቱ
ቤት አንመታም ብለዉ
ቃላቶች ዘበቱ
ላንተ ሲሆን ጊዜ
ፊደላት ምቀኛ
ሀረጋት ፌዘኛ
ሆሄያት ሸረኛ
ሆነዉ አበሩብኝ
ፊደልን አስማምቶ
ሀሳብ አቀናጅቶ
ሆሄያት ሰድሮ
ቀለማት መጥኖ
ካንተ አወዳድሮ.........
ቤት መምቻ ቤትመድፊያ
ቁጥብ ቅኔ ልፊያ
ሚስጥር ማካፈያ
ብዬ ያመንኩት ግጥም
ላንተ ሲሆን ጊዜ............
ሁሉም አሽቃበጡ
የማያዉቁኝ መስለዉ እርቃኔን ገለጡ
ግን ባክህ አዘጋጅ
መድረኩም አይፍረስ
ተደራሲዉ ይፍሰስ
አንተም አትቅርብኝ
ግጥሙም ያብርብኝ
ብዕሬም ይንጠፍጠፍ
የምለዉን ልጣ ከዛ ሁሉ መሀል
ፊቴም ቅልት ይበል ድምብርብሬ ይዉጣ
ያኔ ይገባሀል.............
ብዕሬም ቃላቴም
ቤት መምቻ ቤት መድፊያ
ቀለም ምጥን ምቴም
አንተ እንደነበርከኝ
ግጥሜ ሙዚቃ ነዉ
ከልቤ ሲመታ አንተ ጨፍርበት
እስክስታና ሬጌ ሂፓፕ ዉረድበት።
አንደበቴ ከድቶኝ ልሳኔ ቢዘጋም
ፊቴን አይተህ እወቀዉ ፍቅር ቤት አይመታም
ፍቅር ቤት አይደፋም
ቃላት አይፈልግም
ቀለምም አያሻም
ቅኔ ምስጢር ይሉት ከሱ አይስማማም።
ፍቅር ቤት አልባ ነዉ ተቀባይ አያሻም
ታዳሚ አይፈልግም
መድረክም አያዉቅም
ፍቅር መንገደኛ
ግጥምን አይደለ በቤት ተወስኖ ለአፍታም አይተኛ።
ጠፋባት ይላሉ ታዳሚያን ሁሉ
ሁሉም ሰዉ ይንጫጫል
መድረክ አዘጋጁም ከመድረክ እንድወርድ ባይኑ ይጣቀሳል
ትግስት ያጣዉ ወጣት በድፍረት ያፏጫል።
እኔ እኮ አልጨረስኩም እንዴት ብዬ ልዉረድ
አይንህን ከአይኔ ለአፍታም ሳላወርድ
ስገጥምልህ ነበር
አንዱ ክንዴን ጨምቆ ባያስወጣኝ ከበር
😡 ገላሽን አጫርተሽ 👍
ጭንሽን ለሁሉም ገልጠሽ ስታበቂ
እንባሽ ምርኩዝ ላይሆን አትነፋረቂ
ካጣሁሽ አልኖርም
ያለሽም ሰው ሁሉ በፍፁም ያላንች
ሊቀየር ይችላል ለሀለሉም ስትከፍች
እንዳያታልልሽ ይሄ ግብዝ አለም
ጭን ስላለ ብቻ ካገኙት
መጋደም ሴትነት አይደለም
ገላሽ ከለመደ ካገኘው ሰው ሁሉ ከሆነ ሚጋራ
ጣፋጭሽን መጠው የትም ይጥሉሻል ልክ እንደ ሸንኮራ
ማይገባሽ ቦታ
ማይመጥንሽ ቦታ በፍፁም አትቁሚ
ጆሮ ተሰቶሻል ትሰሚ እንደሁ ስሚ 🎤
☺️☺️☺️☺️☺️☺️☺️☺️☺️☺️☺️☺️☺️
ላለመግደል ማኩረፍ
አቅፌአት ተኝቼ.....
ድንገት ፈግግ ስል ፣ ጥርሴን አየችና፣
"ገዳይ ነህ" አለችኝ.....
ያ'ሁሉ ሙገሳ ማር ፣ፍቅር ቀረና፣
እኔም ከዚያ ወዲህ.....
እንዳትሞት ሰግቼ ጥርሶቼን ብደብቅ፣
"ለምን ታኮርፋለህ"?
አለም ትበራለች አንተ እኮ ስትስቅ፣
የሚል ቃሏን ማመን አቅቶኝ መቀበል፣
ይሄው አኩሪፌአለሁ ሰውን ላለመግደል።
⏳⏳⏳⏳⏳⏳⏳⏳⏳⏳⏳⏳⏳
ጫማዬን ጠርጌ
የክቴን አድርጌ
አምሮብኝ ለወጉ ወዳንቺ ልመጣ
ከቤቴ ስወጣ
የቸኮለ እግሬን እንቅፋት ነደለኝ
አንቺን እያስብኩኝ ምንም አልመሰለኝ፡፡
እሱን እፎይ ሳልል የሰፈርሽ ውሻ ትንፋሼን ጨረሰው
እንደ አትሌት በረርኩኝ እየገረመው ሰው፡፡
ከዛም ሳላርፍ ደሞ ልደርስ አካባቢ
ጥቂት እንደቀረኝ ለበራቹ ግቢ
ጠበኛው ወንድምሽ አየሁት ሲወጣ ደረቱን አስፍቶ
ያልተጣለው በሩን በጁ በሃይል ገፍቶ
ይሄኔ ደንግጬ ልሮጥ እንደዞርኩኝ መንገዴን ሳላየው
ከቆመ ፖል ጋራ በቁሜ ተጋጨው
ወንድምሽ አላየኝ ቀጠለ መንገዱን
እጄም አሸት፣ አሸት ደግፎ እብጠቱን፡፡
ከዛ
ጣጣዬን ጨረስኩኝ ተገላገልኩ ብዬ ላንኳኳ በርሽን
ስትከፍቺ ግዜ እንዳየው ሳቅሽን
‹ሰርፕራይዝ› ብዬ ወይንም ደሞ ላቅፍሽ
ጉንጭሽን ልስምሽ
ወደ ደጅሽ ጠጋ…. ቆርቆር፣ ቆርቆር በሩን
እየጠበቅኩ ወጉን
ደመቅመቅ ፊቴን፣ ሰፋ ሰፋ እጄን
ሰማሁ መሰል ኮቴ ሊከፈት ነው በሩ
እጆቼ ለማቀፍ ተንከርፈፈው ቀሩ
በሩ ተከፈተ 🫵
ጥምጥም ⏳⏳⏳⏳⏳
ከጉንጭሽ ላይ ግጥም!...(የት አባቱ!)
ግን ቆይ….. ምነው ኮሰኮሰኝ የጉንጭሽ ላይ ነገር
ለስላሳ ነው እኮ ሌላ ሌላው ቢቀር……
እያልኩኝ ከራሴ ሙግቴን ሳልጨርስ
ጠይቄ ሳልመልስ
ጉንጬን ከደነብኝ አንዳች ነገር ድንገት
ዐይኔን ብገልጥ እኔም ምንድን ነው ለማለት
ተበላሽቷል ነገር ሆኖ የማይሆነው
በሩን የከፈተው ለካስ አባትሽ ነው 🙈
🚟🚟🚟🚟🚟🚟🚟❤️🚟🚟🚟🚟🚟🚟🚟
👏 የህልሜ ትርጉማት 👏
ከኔ ጋር ተጣልተን ወር እንኳ ሳይሞላ
ሰዎች አወሩልኝ ጠብሷል ብለው ሌላ
አልበቃ ቢላቸው ነግረው ያናደዱኝ
ይባስባት ብለው ፎቶዋን አሳዩኝ
ያን እያሰላሰልኩ አልተኛሽ ብሎኝ
በግድ አባብየው ሸለብ እንዳረገኝ
ስላዲሷ ፍቅርህ አንዳች ህልም አሳየኝ
ቅድድድ ባለ ልብስ ገላዋን ሸፍና
ሰው የሌለበት ቤት ለብቻዋ ሁና
ላንተ ነው መሰለኝ እያፈላች ቡና
አላስችልሽ ብሎኝ ምን ሁነሽ ነው ብላት, ,,,,,
ስትወጣ ስትገባ በነገር ገርፈሀት
ራስ ወዳድ ሁነህ እሷን ረስተሀት
ፍቅር እንደራባት ደስታም እንደጠማት
አልቅሳ አወራችኝ ሆድም አንደባሳት
እኔም የህልሜን ፍች ጓጉቸ ለመስማት
ሲነጋ ጠብቄ ላያቴ ብነገራት
ቀለል አርጋ ፈታ,,,በከበዱ ቃላት
ስትል አረዳችኝ ....
ቅናት እንደሆነ የህልሜ ትርጉማት 😋😋😋
🟢🟠🔴🟢🟠🔴🟢🟠🔴🟢🟠🔴🟢🟠🔴
🇪🇹 ቀለም አልባ ምስል 🇪🇹
;;
እየሄዱ መቆም… እየቆሙ መሄድ!
እየለዩ መጥላት… እየለዩ መውደድ።
በማስመሰል መዳፍ … እየማሉ ማማት!
እየበሉ መራብ… እየጠጡ መጥማት።
;
እያነቡ እስክስታ… እያረሩ መሳቅ!
እየሞሉ መጉደል… እያቀፉ ማነቅ።
እየካቡ ማፍረስ…
ድስት ጥዶ ማልቀስ…
ሰርግ ላይ መነፍረቅ ሀዘን ቤት ዳንኪራ!
ግራ ያልነው በቀኝ ቀኝ ያሰብነው ግራ።
;
አይን ፈጦ እንቅፋት…
በቁም ማንቀላፋት…
የምናየው ሁሉ… በከለር ተፅፎ!
ላያችን ማራኪ… ወስጣችን ግን ቀፎ።
ጣፋጭ እየገፉ… መራራውን መዋጥ!
መድረሻ አልባ ጉዞ… ተቀምጦ መሮጥ።
;
ለእውነት ዝምታ… በሃሰት መመስከር!
ያለን እየካዱ… የሌለውን,, ነበር።
የምንም ላይ ብዜት… የዜሮ ላይ ዜሮ!
ሃቁ ቢመረንም… ይህ ነው የኛ ኑሮ ።
ቀለም አለባ ምስል… ሁሉም ነገር ግምት!
አናሳዝንም ወይ…
የውሸት እየኖርን… የእውነት ስንሞት።
ግን አንድ ሰው አለ
እርጅና ሲጫንሽ
እድሜ ተጠራቅሞ፥ እንዳስም ሲያፍንሽ
ሽበት እንዳመዳይ
በጭንቅላትሽ ላይ
በድንገት ሲፈላ
ያይንሽ ከረጢቱ፥ በንቅልፍሽ ሲሞላ
ምድጃ ዳር ሆነሽ
መጣፍሽን ከፍተሽ
ያለፈውን ዘመን፥ ገልጠሽ ስታነቢ
የኔን ቃል አስቢ፤
ሰንቶች አፈቀሩት፥ በሐቅ በይስሙላ
የገጽሽን አቦል፥ የውበትሽን አፍላ
ግን አንድ ሰው አለ
ከሌሎች ወንዶች ጋር፥ ያልተመሳሰለ
በዕጹብ ድንቋ ነፍሰሽ፥ ፍቅር የነደደ
የመልክሽ ጸደይ ሲያልፍ
ልክ እንደ መስቀል ወፍ፥ ጥሎሽ ያልነጎደ።
ዕድሌ ነው...
.
ዕድሌነው...
በሚስትልወሰን፣ እኔ ትዳር ሲያምረኝ፤
ሳታገባ 'ምትቆይ፣ አንድም ሴት አትገኝ
.
ዕድሌነው...
እኔዲግሪ ስይዝ፣ ዲግሪ ዋጋ ያጣል፤
ገንዘብ ያለው ሁሉ፣ ዶክትሬት ያመጣል
.
ዕድሌነው...
እኔመድረክ ስይዝ፣ ይፈታል ጉባኤ፤
እኔ መጾም ሲያምረኝ፣ ይሆናል ትንሣኤ።
.
ዕድሌነው...
በቁርባንለመኖር፣ ንሰሐ ስገባ፤
አቁራቢው ፖትልኮ፣ ቤተመንግሥት ገባ።
.
ዕድሌነው...
እኔኳስ ስገዛ፣ ሜዳው ይታረሳል፤
እኔ ቤት ሲኖረኝ፣ ሰፈሬ ይፈርሳል።
.
ዕድሌነው...
ለተሾመሁሉ፣ እንዳልኖርሁ ስለፋ፤
እኔ አለቃ ስሆን፣ የሚታዘዝ ጠፋ።
.
ዕድሌነውና...
ከዕለታትአንድ ቀን፣ መንገሤ ባይቀርም፤
እኔ ንጉሥ ስሆን፣ ሀገሪቱ አትኖርም።
😉 𝐒𝐡𝐚𝐫𝐞 በ ፍቅር 🙏
━━━━━━━✦🌹✿🌹✦━━━━━━━
#ተጣልተናል_እኮ
.
እንደማንመለስ ምለን በታቦቱ፣
ንግግር ካቆምን አልፈዋል ወራቱ፣
ኧረምን ወራቱ አመታቱም ነጉዷል፣
ሌላ ወድጃለው እሱም ሌላ ወዷል፣
ግና....
ቁልምጫ በሚሉት እዳ ተለክፌ፣
ሙሉ ስሙን መጥራት አለመደም ኣፌ፣
ተጣብቆብኝ አንዴ የቁልምጫው ነገር፣
ስለሱ ስጠየቅ ለሰዎች ስናገር፣
ውዴ፡ ማሬ፡ ፍቅር፡ ላለማለት ስጥር፣
ይቀድመኛል ኣፌ ባስታዎስኩት ቁጥር።
የት አባሽ
የጋገርሽው እንጀራ ምጣዱ ላይ ተጣብቆ ይቅር
ያፈቀርሸው ሰው ሁሉ ይግፋሽ አይቅናሽ ፍቅር
ተከጂ ተከጂ እንባሽ አይቁም ለአፍታ እንኳን
ልብሽ እረፍት ይነፈግ ይጋረድ በሀዘን ድንኳን
አቦ ወንድ አይውጣልሽ ያጋጥምሽ ጨባሽ አጫሹ
ለአፍታ እንኳን እንዳትስቂ ሁሉ ግዜ ሀዘን ደጋሹ
የት አባሽ የት አባሽ ልበል እስኪ እኔም ቀን ይውጣልኝ
እልፍ አፍቅሬሽ ከእንባ ባህር ገፍተሽ እንደጣልሽኝ
እሰይ እልል ስለቴ ሰመረ
እንደገፋሽኝ ትገፋ ብዬ ነግረው ነበረ
እሰይ እልል ሳቅሽ ይሁን ሲቃ
እረፍት ይንሳሽ ልብሽ ከህመም አይንቃ
አስፋልቱ ገደል ይሁንሽ
ኮብሉን ፒስታ ያርግልሽ
ገደል ግቢ ተደናቅፈሽ
ያንን ቆሻሻ ልብሽን አቅፈሽ
ገጣሚ = ብሩክ✍
🚟🚟🚟🚟🚟🚟🚟🚟🚟🚟🚟🚟🚟
እየተጠራሁ ነው❗️
😵💫 እውነተኛ ታሪክ 😵💫
አቶ በጋሻው እና ወይዘሮ ሽቶ ትዳር መስርተው አንድ የ10 አመት ልጅ ወልደው በፍቅር እየኖሩ ሳለ በአንዲት ባልታደለች ቀን ወይዘሮ ሽቶ በመንገድ ላይ ለጉዳይዋ ስትሄድ ፍሬን የበጠሰ መኪና ገጭቶ አለፋት። በአቅራቢያው ወደ ሚገኘው ክሊኒክ ቢወስዷትም በቶሎ ይህችን አለም ተሰናበትች። አቶ በጋሻው እና ልጃቸው ብርሃኑ ብቻቸውን ለአራት ዓመት ኖሩ። ከዚህ በኋላ አቶ በጋሻው ብቸኝነቱ ከብዶት ሌላ ሚስት አገባ።ልጅም ወለዱ ብርሃኑ ግን ሁለተኛ እናቱ ከመጣች እና ቤተሰቡን ከተቀላቀለች ቀን ጀምሮ ሃሳብ ገባው። ይህች ሁለተኛ እናቱ ብርሃኑን ትጨቁነዋለች እና አይወዳትም።
ያለ ምንም ጥፋቱ ቀኑን ሙሉ ፆሙን እንዲውል ስታደርገው ወደ ጓደኞቹ አቅንቶ ያገኘውን በልቶ ይውላል።
ሁሉ ጊዜ ብርሃኑን ያለ በደሉ ለአባቱ በጋሻው ትከሰዋለች። አባቱም ሚስቱን ያምናታል እና ብርሃኑን በርበሬ ያጥነዋል ሲገረፍም ያድራል።
ብርሃኑ አሁን ሁሉም ነገር ፊቱን ስለ አዞረበት ከቤቱ እንደ ምንም ብሎ የገብስ ዱቄት ይሰርቅ እና ጎረቤት አስቀምጦ ቂጣ እየጋገረ በውሃ እያማገ ይበላል።
የዚህ አይነት ግፍ እየደረሰበት በእንጀራ እናቱ ተጨቁኖ ህይወቱን እያኖረ የሚገኘው ብርሃኑ ጎደኞቹ ከፍለውለት በቤተክርስቲያን የሚዘጋጀውን የጉዞ መርሐ ግብር ሊካፈል ተዘጋጀ።ጉዞው ወደ ሸንኮራ ዮሐንስ ሲሆን በእለቱ ጠዋት ከቤቱ ሲወጣ ምንም ምግብ እንዳልበላ ያወቁት ጎረቤቶቹ ቁርስ በልተህ ትሄዳለህ ቢሉት ''አይይ እኔ እየተጠራሁ ነው'' ቶሎ መሄድ አለብኝ ብሎ ምንም ሳይበላ የጉዞውን መኪና ተሳፈረ።
እየዘመሩ ከተጓዙ ከሰአታት በኋላ የጉዞው መድረሻ ቦታም ደረሱ። ከዚህ በኋላ ነበረ ከሁለት ጓደኞቹ ጋራ ፀበሉ ወደ ሚገኝበት ቦታ ሲያቀና የቀሩት ጓደኞቹ ፀበል ይዘህልን ተመለስ ብለው ሃይላንድ ቢሰጡት ''እኔ አልመለስም እና አልቀበላችሁም'' ብሎ መለሰላቸው። ከዚያም ወደ ፀበሉ አቀና። በቦታው ደርሰው መታጠብ ጀመሩ ድንገት ግን ያልታሰበው ነገር ደረሠ። ብርሃኑ እየታጠበ ሳለ የቆመበት ቦታ አዳለጠው እና ወደ ውንዙ ገባ።አብረውት የነበሩት ጓደኞቹም ጮኹ ሁሉም ተሰባሰቡ ብርሀኑን ግን ሊያድኑት አልቻሉም ላይመለስ ተጠርቷል እና በዚያው ዳግም ወደ ማይመለስበት ከተማ ተጓዘ።
አስክሬኑም ሲፈለግ ቆይቶ በሁለተኛው ቀን ተገኘ። እነዚያ ሲዘምሩ የሄዱት ዛሬ ግን ተክዘው እና በነፍስ የተጓዘው የብርሃኑን አስክሬን ይዘው ወደ ሃገራቸው ተመለሱ።
ሃዘኑ በረታ ትካዜው በሁሉም ልብ ውስጥ ገብቶ የሁሉንም ልብ ሰበረው። ያቺ የምትጠላው እና ልታየው የማትፈልገው እንጀራ እናቱ ዛሬ ላይ በብርሃኑ ስትፈፅም የነበረውን ግፍ እያሰበች ትፀፀታለች።
የአካባቢው ሰዎች እና ጎረቤቶች ደግሞ የብርሃኑን ጭንቀት ስለሚያውቁ በቁጭት ወይኔ ያኔ እኔጋ አስጠግቼው ባሳደኩት የሚሉ እና የሚናገሩ ብዙዎች ናቸው።ብርሃኑ ግን ይህንን ሳያይ ሄዷል።
🌟 ሰዎችን መርዳት ካለብን በጊዜው እንርዳቸው ጊዜው ካለፈ ትርፉ ዋይታ እና ቁጭት ብቻ ነው
💔 "የጠፋው ሬሳ" ❤️🔥
💝ልብ አንጠልጣይ ተከታታይ ታሪክ💝
#ክፍል_፩
7 Periodሜርሲ
_እባላለሁ ቤተሰቦቼ እጅግ የናጠጡ ሀብታም ናቸው የተወለድኩ ወድምም እህትም የሌለኝ የቤቱ ብቻ ልጅ ነኝ 3 Periodያልኩት ይደረግልኛል አንዲትም ሳትቀር በጣም ይሽቆጠቆጡልኛል ዛሬም ዕለቱ የትምህርት ማቆሚያ የክረምቱ ደግሞ መጀመሪያ ስለሆነ ከጓደኞቻችን ጋር ወጣ ብለን የመለያያ ፕሮግራም ለማድረግ እየተዘገጃጀሁ ነው ለሳምት እንቆያለን ስለተባለ ልብሶቼን በሻንጣ በውል አዘጋጀሁ 3 Period"ሜርሲ ሜርሲ" አለች የቤት ምግብ አብሳያችን አቤት ስንዱ አልኳት የመኝታ ክፍሌን መዝጊያ እየከፈትኩ "አቶ አላዛር ሊያናግሩሽ ይፈልጋሉ" አለችኝ "እሺ መጣሁ" አልኳት አቶ አላዛር ማለት ውዱ አባቴ ነው 3 Periodየመኝታ ቤቱን እያንኳኳሁ "ልግባ አባቢ" አልኩት "ግቢ የኔ ልጅ" አለኝ በምላሹ እኔም ወደ ውስጥ ገባሁ "እንዴት አደርሽልኝ የኔ ልዕልት ነይ እስቲ" ብሎ ግንባሬን ሳመኝ "የቀኖቹ ባለቤት እሱ ይመስገን ዛሬም አዲስ ቀን አየሁ" አልኩት "የኔ አንደበተ ማር ቃሎችሽ እኮ እንደ ከርቤ ዕጣን ያውዳሉ"አለኝ አልጋው ጎን ተቀምጬ ፀጉሬን እየነካካ "አባቢ ደሞ ምን የተለየ ነገር ተናግሬ ነው" አልኩት "እኔ ያልኩትን ራሱ ብትደግሚልኝ እንደ አዲስ ብርቅ ሆኖብኝ ነው ምሰማው" ብሎ ፈገግ አለ "ማሚስ የት ሄዳ ነው በጠዋት" ብዬ ጠየኩት "ጉዞ ሄዳለሁ ብለሽ የለ ከስንዱ ጋር ለጉዞሽ የሚሆን ስንቅ እየሰሩልሽ ነው የሆቴል ምግብ እንደማትጠቀሚ እያወቀች ዝም ብላ አትለቅሽ" አለኝ "እውይ የኔ እናት ሄጄ ልጠምጠምባታ" ብዬ ከአልጋው ስነሳ "የተጠራሽበትን ዋና ጉዳይ ሳልነግርሽ ወዴት ልትሄጂ ነው" አለኝ "እሺ ንገረኝ" አልኩት ወድያውኑ "ት/ት ቤት የሚያመላልስሽ ሹፌር አብሮሽ እንዲሆን ነግሬዋለሁ ከከተማ ውጪ ማንም አጠገብሽ ሳይኖር ብቻሽን ልተውሽ አልፈልግም አሁን ይመጣል"አለ "አረ አባቢ ችግር የለውም ጓደኞቼ እኮ አሉ ብዙ ነን የኔ አሳቢ አባቴ አመሠግናለሁ በነፃነት እንድዝነናና ፍቀድልኝ አባቢ ይሄን ብቻ ተቸገርልኝ ደሞኮ አድጌያለሁ"አልኩት "እሺ እንዳልሽ ስልክሽ ግን ሁሌም ክፍት አርጊው በምንም አይነት ሁኔታ ዝግ እንዳይሆን እንደውላለን አንቺም ደውዪ" አለኝ ማስጠንቀቂያ በሚመስል ትዕዛዝ "እሺ የኔ አባት አታስብ" ብዬ ግንባሩን ስሚው ከክፍሉ ወጣሁ ከዛ ማሚ ከኔ ክላስ ስትወጣ አየሗት የኔ እናት ብዬ ጥምጥም አልኩባትና ጉንጯን ሳምኳት "አረ ቀስ ወዜን እንዳትመጪው" አለችኝ እቅፍ አርጋ እየሳመችኝ 3 Period"የኔ ልጅ በጣም ተጠንቀቂ እሺ ነገሮችን በማስተዋል አድርጊ" አለችኝ ለኔ እጅግ እንደምትሳሳ አይኗ ላይ ይነበባል "እሺ የኔ እናት አታስቢ እኔ ያንቺ ልጅ አድጌልሻለሁ እኮ" አልኳት "ፈጣሪ ይመስገን ጎርምሰሽልኛል መልካም መንገድ የኔ ልጅ ታዲያ ቶሎ ቶሎ ደውዪ እሺ እድንጨነቅ አታርጊን" አለችኝ "እሺ እናቴ" ብዬ ወደ መኝታ ክፍሌ ገባሁ ተለቅ ያለ አገልግል ጠረጴዛዬ ላይ ተቀምጧል አይ የኔ እናት 3 Periodለጉዞዬ የመረጥኩትን ልብስ ለበስኩኝ እጅግ አማረብኝ ስለ ራስሽ አወራሽ አትበሉኝና 3 Periodእጅግ በጣም ቆንጅዬ ሴት ነኝ የናቴ ልጅ ራሴን በጣም ነው ማቆለጳጵሰው ሌላ ማን ያቆለጳጵሰኛል "ስንዱ ዕቃዬን ታግዢኛለሽ" አልኳት ድምፄን ከፍ አድርጌ በሩን ከፍቼ አንገቴን አስግጌ ጠራሗት "እሺ ሜርሲዬ" ብላ መጣች እሷ ሻንጣውን እኔ ደግሞ አገልግሉን ይዤ ወደ መውጫው ጉዞ ጀመርን "የኔ አባት እና የኔ እናት ትናፍቁኛላችሁ እስክንገናኝ ምወደው ፈጣሪዬ ምወዳቹን ይጠብቅልኝ"አልኳቸው ድምፄን ከፍ አድርጌ "እሺ ሰላም ግቢልን የኛ ልጅ" አለ አባቢ ማሚ መዳፏን እያወዛወዘች በፈገግታ ሸኘችኝ 3 Periodየሳሎኑን በር ዘግቼ ወጣሁ የግቢ ጠባቂያችን "አምጪው ሜርሲዬ" ብሎ አገልግሉን ተቀበለኝ "አመሠግናለሁ አስራት አምላክ ይባርክህ" አልኩት "አሜን አለኝ በምላሹ "እና ምን አዲስ ነገር አለ" አልኩት "ምንም ሜርሲዬ ይነጋል ይመሻል ድጋሜ ይነጋል ድጋሜ ይመሻል" አለኝ በውስጤ "አይ የሰው ልጅ ምን አዲስ ነገር አለ ሲባል ምንም ይላል የዛሬውን ቀን ከዛሬ በፊት ያየውና ውሎ ያደረበት ይመስል"እላለሁኝ ግን ለአስራት መልስ አልሰጠሁትም ነበር 3 Periodጓደኞቼ ድረስ የሚያደርሰኝ ሹፌሬ ደጅ ላይ ቆሞ እየጠበቀኝ ነው "ሰላም አደርክ" አልኩትኝ ኮፈኑን እንዲከፍትልኝ በእጄ እየጠቆምኩት ወዲያው ከፈተው "አስራት አገልግሉን ከውስጥ አርገው ስንድዬ ሻንጣውን እዚ አስገቢው"አልኳቸው ሁለቱም "እሺ አሉኝ 3 Periodእቅፍ አርጌ ሳምኳቸውና ሰላም ያገናኘን ብዬ ወደ መኪናው ገባሁ 3 Period
✎ክፍል 2 ይቀጥላል
➖➖➖➖➖➖🫥➖➖➖➖➖➖
#አሜን_አሜን_በይ_ልመርቅሽ. 😄
ካልሽ እንግዲህ አቦል ጀባ
ያብብ መልክሽ እንደአበባ
ያውድ ጥሩ ቴሌግራም ቤትሽ
በ Hi ይሙላ Inbox ደጅሽ 😅
እንዳማረው ሸክላ ጋቻ
ጀንጃኝ አትጭ አግኝ አቻ 😘
በይ አሜን በይ ልመርቅሽ,,,,
ካርድ አትጪ ዳትሽ ይብራ 😄
ላይክ አድራጊሽ ይበል ጎራ
ሼር ፣ ኮሜንትሽ አያባራ 😜
በይ አሜን በይ ልመርቅሽ
ይሰውርሽ ከጂል ፍሬንድ ከዘረኛ
የሰው እምነት ከሚሳደብ በሽተኛ
በፖሰትሽው ከሚናደድ ቀናተኛ
ከአዲስ ጀንጃኝ ከሆነ አዛ 🤏
ማሬ ፣ ማሬ ከሚያበዛ
ይጠብቅሽ ከሞዛዛ 🤔
በይ አሜን በይ ልመርቅሽ
ስልክ ቁጥር ላኪ ከሚል 😟
ቢሰጡትም ከማይደውል 😩
በባዶ አንጀት ከሚያደርቅሽ 😕
ልብ ጠቢ ይጠብቅሽ 🤲
በይ አሜን በይ ልመርቅሽ,,,,
እንደፈላው ቆንጆ ቡና 😍
የኔ አይነት ልጅ መልከ ቀና 😌
ላግባሽ ብሎ ይላክልሽ ሽምግልና
አቦ እፎይ በይ በቃ አግብተሽ 😀
ስልክሽ አርፎ አንችም አርፈሽ
ቶሎ ተኝ ዳታ አጥፍተሽ 😗
በባልሽ ክንድ ብሎክ ሁነሽ 😂
😁 አሜን በል 😂
➖➖➖➖➖ ❤️ ➖➖➖➖➖
