የቀጠናው ተመልካች
Ir al canal en Telegram
በአለማችን ቀጠናዎች የሚከሰቱ ክስተቶችን ይዘግባል፣ ሳይቀዘቅዝ በትኩሱ። ለጥያቄና ለአስተያየቶች በኢሜል asuleyma246@Gmail.com ብላችሁ ፃፉልኝ።
Mostrar másEl país no está especificadoLa categoría no está especificada
4 312
Suscriptores
-124 horas
-167 días
-8330 días
Archivo de publicaciones
4 313
🇮🇶⚡️ — የኢራቅ ፀረ ሽብር ኃይሎች፣ በባግዳድ ግሪን ዞን የሚገኘውን እና ባለስልጣናትንና ቤተሰቦቻቸውን የያዘውን Sikma መኖሪያ ህንፃን ሰብረው ገብተዋል።
በድጋሜ፣ ባይረጋገጥም፣ በአሁኑ ሰዓት በኢራቅ መፈንቅለ- መንግሥት እየተደረገ ይመስላል።
4 313
🇮🇶 ሰበር ዜና፡ በባግዳድ በሚገኘው የመንግሥቱ መቀመጫ፣ Green Zone፣ በአሁኑ ሰዓት መፈንቅለ መንግሥት እየተደረገ ይመስላል።
ቤተ መንግሥቱ በታንኮች ተከቧል፣ ወታደሮች ሰብረው በውስጡ በመግባት እስካሁን ማንነታቸው ያልተረጋገጠን ሁለት ባለስልጣናትን ወስደዋል። በከተማው ከፍተኛ ተኩስ ይሰማል፣ የወታደሮች እንቅስቃሴ በስፋት ይታያል።
ዜናው አልተረጋገጠም፣ ነገር ግን በኢራቅ፣ መፈንቅለ-መንግሥት በመደረግ ላይ ይመስላል።
4 313
🇮🇷⚡️🇺🇸 በዛሬው ሌሊት የአሜሪካ ጦር ኃይሎች፣ በኢራን ባንደር አባስ፣ ከሽም፣ እና ካሪግ ደሴቶችን ክፉኛ እንደደበደቡ ታውቋል።
ድብደባው፣ ዛሬ ጠዋት ኢራን በበርካታ የንግድ መርከቦች ላይ ተኩሳለች፣ የሆርሙዝ ወሽመጥ መተላለፊያንም አስተጓጉላለች በሚል የተወሰደ "አፀፋዊ እርምጃ" ነው፣ ብሏል CENTCOM።
በምላሹ፣ ኢራን በባሕሬንና በኩዌት በሚገኙ የአሜሪካ የጦር ሰፈሮች፣ በኢሳ አየር ኃይል እና በአሊ አል ሳሊም፣ ላይ በድሮንና ሚሳዬሎች የታገዘ ጥቃት ከፍታለች።
የኢራን ጥቃት አሁንም አላባራም። በተመሳሳይ አንድ የአሜሪካ ከፍተኛ ባለስልጣን፣ የአሜሪካ የምሽቱ ድብደባ እንደተጠናቀቀ ለFOX NEWS ተናግሯል።
4 313
በዛሬው ሌሊት የአሜሪካ ጦር ኃይሎች፣ በኢራን ባንደር አባስ፣ ከሽም፣ እና ካሪግ ደሴቶችን ክፉኛ እንደደበደቡ ታውቋል።
ድብደባው፣ ዛሬ ጠዋት ኢራን በበርካታ የንግድ መርከቦች ላይ ተኩሳለች፣ የሆርሙዝ ወሽመጥ መተላለፊያንም አስተጓጉላለች በሚል የተወሰደ "አፀፋዊ እርምጃ" ነው፣ ብሏል CENTCOM።
በምላሹ፣ ኢራን በባሕሬንና በኩዌት በሚገኙ የአሜሪካ የጦር ሰፈሮች፣ በኢሳ አየር ኃይል እና በአሊ አል ሳሊም፣ ላይ በድሮንና ሚሳዬሎች የታገዘ ጥቃት ከፍታለች።
የኢራን ጥቃት አሁንም አላባራም። በተመሳሳይ አንድ የአሜሪካ ከፍተኛ ባለስልጣን፣ የአሜሪካ የምሽቱ ድብደባ እንደተጠናቀቀ ለFOX NEWS ተናግሯል።
4 313
🇮🇷⚡️🇮🇱🇺🇸 አሜሪካ በፋርስ ባሕረ ሰላጤ ቀጠና ያላትን ወታደራዊ ሰፈራ ለመቀነስ ወሳኝ የተባለ ግምገማ በማድረግ ላይ ናት ሲል The Wall Street Journal ዘግቧል።
▪️ ከአሜሪካ እና ከእስራኤል ጋር በተፈጠረው ግጭት ምክኒያት፣ የኢራን ሚሳዬሎች በፋርስ ባሕረ ሰላጤ በሚገኙ የአሜሪካ ወታደራዊ ተቋማት ላይ ከፍተኛ ውድመት አድርሰዋል፣ ይህም አሜሪካ በዚያ የመቆየቷን ሁኔታ እንድታጤን አስገድዷታል፣ WSJ በዘገባው።
4 313
🇷🇺⚡️🇺🇦 የፊንላንድ ፕሬዝዳንት አሌክሳንደር ስቱብ በሩሲያ-ዩክሬን ጦርነት ላይ፡ -
ሩሲያ በኢኮኖሚ ውስብስብነት ምክንያት ይህንን ጦርነት አታቆምም። ፑቲን በሩሲያ ወታደሮች ሞት ምክንያት ይህንን ጦርነት አያቆምም። ህዝቡ ከተነሳበት ይህንን ጦርነት ያቆማል።
4 313
🇸🇰 ⚡️🇺🇦 የስሎቫኪያው ጠቅላይ ሚንስትር ፊኮ፣ በኔቶ ስብሰባ ላይ ለዩክሬን አዲስ ወታደራዊ ዕርዳታ እንደሚከለክል ተናግሯል።
ፊኮ፣ ሀገሩ በመጪው የኔቶ ስብሰባ ላይ ለዩክሬን አዲስ ወታደራዊ ብድር ወይም የገንዘብ መዋጮ እንደማትደግፍ ተናግሯል። እንደ ፊኮ ገለጻ፣ ስሎቫኪያ "ለዩክሬን ወታደራዊ ወጪ አትከፍልም" እና አቋሙን "ይባባሳል" በሚል እና ሦስተኛው የዓለም ጦርነት ሊከሰት ይችላል በሚል አብራርቶታል።
*-*-*-
የሀንጋሪው ኦርባን ቪክተርም እንዲሁ ነበር፣ የአውሮፓ ሕብረት ለዩክሬን የሚያደርግ የነበረውን ድጋፍና እርዳታ አይሆንም እያለ ሲቃወም ነበር። ዩክሬኖች፣ እንግሊዞች ጥርስ ነክሰውበት፣ ምርጫው ሲመጣ እንዲወርድ አድርገውታል (በአሻጥር)። ዛሬ የመጣው የሀንጋሪ መሪ ሁሉም ለዩክሬን ይሁን የሚል ነው።
ፊኮ፣ የዛኔም ከኦርባን ጋር ነበር። ዛሬ ብቻውን ነው። ዩክሬኖች ቀን እየጠበቁለት ይመስለኛል።
4 313
+2
⚡️🇱🇧🇮🇷 የሊባኖስ የውስጥ ደህንነት ሃይሎች ባለፈው ሳምንት መጀመሪያ ላይ፣ ሂዝቦላህ በአውሮፕላን ማረፊያው መንገድ ላይ የሰቀላቸውን ሁሉንም የማስታወቂያ ሰሌዳዎች አስወግደዋል።
"ኢራን፣ እናመሰግናለን" የሚለውን መልእክት በመተካት "ሊባኖስ ትቅደም" በሚል መፈክር ተክቷል።
4 313
⚡️🇮🇷🇺🇸🇸🇦🇦🇪 የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የዩኤስ-ገልፍ ሀገራትን የጋራ መግለጫ "ጣልቃ ገብነት፣ ኃላፊነት የጎደለው እና ተንኳሽ" ሲል ውድቅ አድርጎታል።
በተጨማሪም፣ የፍልስጤም እና የሊባኖስ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎችን "የኢራን ወኪሎች ናቸው" የሚል ስያሜ መስጠቱን አውግዟል፣ እስራኤልን በቀጠናው ውስጥ ብቸኛዋ ወኪል አካል እንደሆነች አድርጎ ገልጿል።
ኢራን የሆርሙዝ ባሕር በኢራን እና በኦማን የግዛት ውሃ ውስጥ እንደሚገኝ እና ጦርነቱን ለማቆም የተደረሰው ስምምነት ለባሕሩ አስተዳደር መሠረት ሆኖ እንደሚያገለግል በድጋሜ አረጋግጧል። ስምምነቱ የውሃውን ባለቤትነት ለኢራን እና ለኦማን እንደሰጠ ይታወቃል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጨምሮ፣ በአካባቢው ያሉ አረብ ሀገሮች ከአሜሪካ ጋር መተባበር ከዚህ በፊትም እንዳልጠቀማቸው ሁሉ፣ ወደፊትም ብዙም እንደማያዋጣቸው እንዲያውቁ አሳስቧል።
4 313
⚡️🇮🇷🇺🇸🇸🇦🇦🇪 የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የዩኤስ-ገልፍ ሀገሮችን የጋራ መግለጫ "ጣልቃ ገብነት፣ ኃላፊነት የጎደለው እና ተንኳሽ" ሲል ውድቅ አድርጓል።
በተጨማሪም፣ የፍልስጤም እና የሊባኖስ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎችን "የኢራን ወኪሎች ናቸው" የሚለውን ስያሜ ውድቅ አድርጓል፣ እስራኤልን በቀጠናው ውስጥ ብቸኛዋ ወኪል አካል እንደሆነች አድርጎ ገልጿል።
ኢራን የሆርሙዝ ባሕር በኢራን እና በኦማን የግዛት ውሃ ውስጥ እንደሚገኝ እና ጦርነቱን ለማቆም የተደረሰው ስምምነት ለባሕሩ አስተዳደር መሠረት ሆኖ እንደሚያገለግል በድጋሜ አረጋግጧል። ስምምነቱ የውሃውን ባለቤትነት ለኢራን እና ለኦማን እንደሰጠ ይታወቃል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጨምሮ፣ በአካባቢው ያሉ አረብ ሀገሮች ከአሜሪካ ጋር መተባበር ከዚህ በፊትም እንዳልጠቀማቸው ሁሉ፣ ወደፊትም ብዙም እንደማያዋጣቸው እንዲያውቁ አሳስቧል።
4 313
⚡️🇺🇸🇸🇦🇮🇷 ሮይተርስ፡ የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ፣ የሦስት ቀን የባሕረ ሰላጤ ሀገሮች ጉብኝቱን አጠናቅቋል።
ሳዑዲ አረቢያ በሪያድ፣ በኢራን እና በባሕረ ሰላጤው አረብ ሀገራት መካከል የቀጠና እርቅ ድርድርን ለማስተናገድ በዝግጅት ላይ እያለች ሲሆን፣ ከአሜሪካ-ኢራን ድርድር የተለየ የሚሆነው ስብሰባ መተማመንን እንደገና በመገንባት እና ስለወደፊቱ የቀጠናው ደህንነት ማዕቀፍ ላይ በመወያየት ላይ ያተኮረ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።
ሩቢዮ፣ ከባሕረ ሰላጤው ትብብር ምክር ቤት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጋር ባደረጉት ስብሰባ፣ ከኢራን ጋር የሚደረግ ማንኛውም ስምምነት ለደህንነታቸው አደጋ እንደማያመጣ አጋሮቹን ለማረጋጋት ፈልጎ ነበር። ነገር ግን፣ አሁንም በፍራቻ ውስጥ እንዳሉ ለመገንዘብ ተችሏል። ዩኤስ እና የገልፍ ሀገሮች በሆርሙዝ ባሕር በኩል ያለ ክፍያ እና ገደብ፣ ነፃ እና ቅድመ ሁኔታ የሌለበት አሰሳንም ደግፈዋል።
የባሕረ ሰላጤው ሀገሮች ስምምነቱ የኢራንን የባለስቲክ ሚሳኤል ፕሮግራም የማይመለከት መሆኑ እና የቴህራንን ቀጠናዊ ተጽእኖ ሊያሰፋ ይችላል የሚል ስጋት አላቸው።
በአሜሪካ-ኢራን ድርድር ውስጥ ካሁን በኋላ አሜሪካ ገልፍ አረቦችን ብታማክራቸው እና ብታሳትፋቸው እንደሚወዱ ሩቢዮን አጥብቀው ጠይቀዋል።
4 313
🇱🇧🇺🇸🇮🇱🇱🇧🇮🇷⚡️ - የሂዝቦላህ ዋና ፀሃፊ ናይም ቃሲም -
በዋሽንግተን የተደረሰው ስምምነት አዋራጅ፣ አሳፋሪ እና ሕገ-ወጥ ስምምነት ነው። ይልቁንም፣ በሊባኖስ የተኩስ አቁም ሁኔታን በተመለከተ የኢራን-አሜሪካ መግባባት ድንጋጌዎች መተግበር እንዳለባቸው እናምናለን። የእስራኤልን ከደቡብ ሊባኖስ መውጣት፣ ከሂዝቦላ የጦር መሳሪያ መፍታት ጋር ማያያዝና ያንን ስምምነት ተፈራርሞ መምጣት እጅግ አሳፋሪ ነው። የሊባኖስ መንግሥት የት እንደቆመ፣ ለማን ጥቅም እየሠራ እንዳለ እና ከሕዝብ ተፃራሪ መሆኑን የሚያሳይ ነው። ማን ነው ሂዝቦላን መሳሪያ የሚያስፈታው? የሊባኖስ መንግሥት ነው? ማን ነውስ መሳሪያ የሚፈታው? ሂዝቦላ መሳሪያውን ለማንም አያወርድም! የእርስ በእርስ ጦርነት ቀመር ነው ፈርመው የመጡት።
4 313
🇮🇷🇺🇸⚡️ - UKMTO በንግድ መርከቦች ላይ ያገረሸውን ጥቃቶችን ተከትሎ በሆርሙዝ ወሽመጥ ውስጥ ያለውን የደህንነት ስጋት ደረጃ፣ ወደ "ተጨባጭ" ከፍ አድርጓል።
➡️ መርከበኞች የባሕር ኃይል ፈንጂዎች መኖራቸውን በማወቅ እንዲንቀሳቀሱ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል። በውሃ መንገዱ ላይም መጨናነቅ ሊኖር የሚችል መሆኑን እንዲጠብቁም መክሯል።
