es
Feedback
የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት-Ethiopian Archives and Library Service

የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት-Ethiopian Archives and Library Service

Ir al canal en Telegram

.ይህ የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ይፋዊ የቴሌግራም ቻናል ነው፡፡

Mostrar más
El país no está especificadoLa categoría no está especificada
514
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
Sin datos30 días
Archivo de publicaciones
መስከረም /2018 ዓ.ም “መስከረም ተፈጥሮም ራሷን የምታድስ ከሆነ እኛም ቆም ብለን ራሳችንን ለማየትና ለመረዳት ጥሩ ጊዜ ነው፡፡” (የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሠርፀ ፍሬስብሀት) የ2018 አዲስ ዓመት ምክንያት በማድረግ የእንኳን አደረሳችሁ ካርዶችን ለሰራተኛው በመስጠት አዲሱን ዓመት ተበስሯል፡፡ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ ነፊሳ አልማህዲ የ2018 አዲስ ዓመት በግል፣በቡድንና በተቋም ደረጃ አቅደን ያልተሳካልን እንዲሁም ደግሞ በሀገር ደረጃ ይሁን ብለን ተመኝተን ያልተሳካልንን በ2018 ላይ እንዲሳካልን በማለት ተመኝተው አክለውም በሀገራችን የምንመኘው ሰላም ወርዶልን ከህዳሴ ግድብ በተጨማሪ ስለ ወደባችን ደግሞ እያሰብን ስለሆነ የቀይባህር ጥያቄ የራሳችን አድርገን፤አጀንዳም ቀርጸን እና እዛ ላይ በጋራ ተወያይተን በህዳሴው ዳግም አድዋን እንደደገምን ሌላ አድዋን የምንደግምበት ጊዜ እንዲሆንም ተመኝተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሠርፀ ፍሬስብሀት በእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸው በግዜ ሂደት ውስጥ የማይለካ የማይፈተሸ ነገር የለም፤ በግዜ ዑደት ውስጥ የሚመጣው አዲስ ዓመት የሰለቸን የማደስ፣ የመረረን የማጣፈጥ ትልቅ ችሎታ አለው ብለው ኢትዮጵያ ተፈጥሮና የግዜ ቀመር ተስማምተው እውነት ዘመን ተቀይሯል የሚሉበት ሀገር እንደሆነች የአደይ አበባንና የመስቀል ወፍን አመላካችነት ገልጸው ተናግረዋል፡፡ አክለውም በመስከረም ተገናኝቶ ውብ ሃሳብ ተለዋውጦ ዓመቱ የሰላም ይሁንልን ብሎ ስራን መጀመር በጣም ደስ የሚል ስሜትን እንደሚፈጥር ተናግረው የምንሸምትና የምንሰፍረውን እቃ ልኬት ውስጥ ገብቶ እንደሚሰፈር እኛም የሰራነው ስራና የህይወታችን ረብህ ይለካል፤ ስለዚህ ምን ረብህ አተረፍን በህይወታችን ውስጥ ምን የሚበጅ ስራ ሰራን በተቋማችንና በሀገራችን ውስጥ የእኛ አስተዋጽዖ የትኛው ነው የሚለውን የሚያስለይ፣ የሚያስለካና የህይወት ሚዛን ውስጥ የሚከተን ጊዜ የሚባለው መመሪያ ነው ብለዋል፡፡ በ1946 ዓ.ም አካባቢ በአንድ ግለሰብ (በአቶ ታደሰ ታቼ) የኢትዮጵያ ህዳብ ግድብን እንዴት መገንባት እንደሚቻል በወቅቱ ለነበረው የመዘጋጃ ኃላፊ የተጻፈ ደብዳቤን መነሻ በማድረግና ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከተቋሙ ጋር ያለው ቁርኝትና መዛግብቱም በተቋማችን ተጠብቆ እንደሚገኝ ጠቁመው በሀገራችን ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ያቀድናቸውና የጀመርናቸው የልማት ስራዎች በግዜ ፍጥነት ተጠናቀው አገልግሎት እየሰጡም እንደሚገኝ በአዲስ ዘመን መባቻ የተጠናቀቀው የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አንዱ ማሳያም እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ በመጨረሻም በክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ ወ/ሮ ነፊሳ እጅ ለአጠቃላይ የተቋሙ ሰራተኞችና ስራ አስፈጻሚዎች የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ የተዘጋጀ የእንኳን አደረሳችሁ ካርድ ተበርክቶላቸዋል፡፡

ተቋሙ ለደብረ ሮሐ ቅዱስ ላሊበላ የአራቱ ጉባዔ አዳሪ ት/ቤት ግምታቸው ከ218 ሺህ ብር በላይ የሆኑ ለትምህርት የሚረዱ መጻሕፍት እና ቁሳቁሶች ድጋፍ አደረገ። የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የቅዱስ ላሊበላ ገዳም ቤዛ ኩሉ (የቅዱስ ላሊበላ) የአራቱ ጉባኤ አዳሪ ትርጓሜ ትምህርት ቤት ድጋፍ አድርጓል። ሀገራችን ኢትዮጵያ የራሳቸው የጽሑፍ ሥልጣኔ ካላቸው ጥቂት የአለማችን ሀገራት ውስጥ አንዷ ስትሆን፣ በአፍሪካ ደግሞ ከአረቦቹ ውጪ ብቸኛዋ ሀገር ናት፡፡ በኢትዮጵያ በተለያዩ አድባራት፣ ገዳማት፣ መስኪዶች ውስጥ በግዕዝ፣ በአማርኛ፣ በአረብኛ፣ እና በሌሎች ቋንቋዎች የተጻፉ፣ ሺህ ዓመታትን ያስቆጠሩ ዕድሜ ጠገብ የጽሑፍ ሥራዎች ተከማችተው እስካሁን ድረስ መገኘታቸው የዚሁ እውነታ አመላካች ነው፡፡ በዚህ የጽሑፍ ጥበብ፣ ኢትዮጵያ ታሪኳን፣ስልጣኔዋን፣ እምነቷን ፍልስፍናዋን ከትባ በማቆየት ለዚህ ትውልድ እንዲደርስ ከማድረግ ባሻገር፣የጽሑፍ ቅርሶቹን በአለም የጽሑፍ ቅርስነት /MOW/ እንዲመዘገብ ማድረግ ችላለች፡፡ በጥንታውያን የጽሑፍ ክምችታቸው ከሚጠቀሱ ቦታዎች ውስጥ አንዱ በአማራ ብሔራዊ ክልል በሰሜን ወሎ ዞን በላሊበላ ከተማ በሚገኘው እና በተባበሩት መንግስታት የትምሕርትና የሳይንስ ድርጅት /UNESCO/ በማይንቀሳቀስ ቅርስነት የተመዘገበው የደብረ ሮሀ ቅዱስ ላሊበላ አብያተ ቤተክርስቲያናት ይገኙበታል፡፡ ይህ ታላቅ ቦታ በ12መ/ክ በንጉስ ላሊበላ እንደተመሰረተው የሚነገር ሲሆን፤ በውስጡም የሀገር ቅርስ የኾኑ በርካታ የመረጃ ሀብቶች መገኛ ቦታ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ይህን አስተምሕሮት የጥንታዊ ይዘቱን ባለቀቀና የዘመኑን ሥልጣኔ ታሳቢ ያደረገ ቤዛ ኩሉ (የቅዱስ ላሊበላ) የአራቱ ጉባኤ አዳሪ ትርጓሜ ትምህርት ቤትን የሰሜን ወሎ ዞን ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል የሆኑት ብፁዕ አቡነ ቄርሎስ እስከ ቦታው በመምጣት በብፁእነታቸው ቡራኬ በ1995 ዓም የተቋቋመ ነው፡፡ አሁን ላይ ትምሕርት ቤቱ ሙሉ ወጫቸው ተሸፍኖላቸው በቋሚ የሚማሩ 30 መደበኛ እና 5 ተመላላሽ በድምሩ 35 ተማሪዎችን ተቀብሎ እያሰተማረ የሚገኝ ሲሆን፤ 3 ቋሚ እና እንደ አስፈላጊነቱ ሌሎች ተጋባዥ መምህራን አሉት፡፡ የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻህፍት አገልግሎት ከመንግስት በተሰጠው ሥልጣን መሰረት የሀገሪቱን የጽሑፍ ሀብቶች እንዲታወቁ፣ እንዲጠበቁ፣ እንዲጠኑ እና ለትውልድ እንዲተላለፉ ለማድረግ የመመዝገብ፣ ዲጂታላይዝ የማድረግ፣ ቅጃቸውን የማሰባሰብ፣ ሥልጠና እና ምክር የመስጠት እንዲሁም በቁሳቁስ የመደግፍ ሥራ ይሰራል፡፡ በ2018 በጀት ዓመት ነሐሴ ወር በአማራ ክልል በሰሜን ወሎ ዞን በላሊበላ የሚገኘው ቤዛ ኩሉ (የቅዱስ ላሊበላ) የአራቱ ጉባኤ አዳሪ ትርጓሜ ትምህርት ቤትን በጥንታዊ የኢትዮጵያ ትምህርቶች ላይ እየሰራ ያለውን ሥራ በቦታው በመገኘት ለመመልከት፣ የመጻሕፍት እና የቁሰቁስ ድጋፍ ለማድረግ፣ የምክር አገልግሎት ለመስጠት እና ለማበረታታት በታቀደው መሰረት፤የተቋማችን የአብያተመጻሕት መረጃ ሀብቶች አስተዳደር ኹለት ባለሙያዎች ከነሐሴ 25 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በቦታው በመገኘት አጠቃላይ የትምሕርት ቤቱን እንቅስቃሴ በመጎብኘት ትምሕርት ቤቱ ወደፊት በሚሰጠው ትምሕርት እና በሚያፈራቸው የሰለጠነ የሰው ኃይል ለጥንታውያን የጽሑፍ ሀብቶች ደህንነት ጥበቃ እና እንክብካቤ ትኩረት ሰጥተው እንዲሰራ በማሳሰብ፤ የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ለትምሕርት ቤቱ 4 ያገለገሉ ኮምፒዩተሮች /Desktop Computers/፣2 አይፎን /Tab Computers/ ፣90 አጋዠ መጻሕፍት እና ኮምፒዩተሮች በተዘጋጀው ክፍል ውስጥ በመገጣጠም እና ለአገልግሎት ዝግጁ በማድረግ እንዲሁም የጥንታውያን ጽሑፎች ደህንነት አጠባበቅ ላይ ምክር የመሥጠት ሥራ ተሰርቷል፡፡

የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት እንኳን ለ፳፻፲፰/2018 ዓ.ም በሰላም አደረሳችሁ እያለ መጪው አዲስ ዓመት በሀገራችን ብሎም በዓለም ሠላም ሰፍኖ ማሕበረሰቡ ሠላሙ ተጠብቆ የእለት ከእለት ተግባሩን ያለስጋት የሚከውንበትና መንግስታዊም ሆኖ መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት እንደቀድሞው በስፋት እቅዳቸውን የሚተገብሩበት እንዲሁም እንደ ቀደመው ታሪካችን ተቻችለን፤ ተከባብረን በጋራ በመኖር ሀገራችንን ወደተሻለ ደረጃ የምናሻግርበትንና በዚሁ አመት እንዳጠናቀቅነው እንደ ህዳሴው ግድባችን የጀመርናቸውን ታላላቅ የሀገር ለውጥ አምጪ ፕሮጀክቶችን ተባብረን የምንጨርስበት ዘመን እንዲሆን እየተመኘ...... የሪከርድና የመረጃ ሥራ አመራር በመዘርጋት መዛግብትን፣የጽሑፍ ቅርሶችንና የታተሙ እና ያልታተሙ የመረጃ ውጤቶችን በማሰባሰብ፣ በማደራጀት፣ጠብቆ፣ለትውልድ በማስተላለፍ ተደራሽ በማድረግና የእውቀት፣ የክህሎት፣ ማሳደጊያና የልዕቀት ማዕከል በመሆን በእውቀት የበለፀገ ማህበረሰብ መፍጠር ተልዕኮው በማድረግ ለ፳፻፲፰/2018 /አዲስ ዓመት በአገልግሎቱ ተጠብቀው ከሚገኙት ጥንታዊያን የጽሑፍ ቅርሶች መካከል የሀገራችን ኢትዮጵያን ዘመን አቆጣጠር በስፋት የሚዘረዝረው መጽሐፈ ባሕረ ሐሳብ እና አቡሻኸር በማስተዋወቅ ሀገራችን ለስልጣኔ ምን ያህል ቀደምት መሆኗንና የራሷ የሆነ የዘመን አቆጣጠር ያላት እንደሆነች  ከታሪኳ እንድትከታተሉ በአክብርኦት ስንጋብዞ......... 🕊🌻🌻🌻🌻🕊🌻🕊🌻🕊🌻🌻🌻🌻🌻️🕊🌾🌻🌾🌻🌾🌻🌾🌻 🌻🌻 መልካም አዲስ ዓመት!          🌻  🕊🌻🌻🌻🌻🌻️🕊 🌻🌻🌹⁣ 🌻🌻          🌻                🌻️ መጽሐፈ ባሕረ ሐሳብ ማለት ቁጥር ያለው ዘመን ወይም የዘመን አቆጣጠር ማለት ሲሆን ቀድሞ የነበረ፣አሁንም ያለ፣ ለወደፊትም የሚኖር፣ዘላለማዊ ፈጣሪ አምላክ በዚህች በአለንበት ዓለም ሳዲሳትን በኀምሲት፣ኀምሲትን በራዓቢት፣ ራዓቢትን በሣልሲት፣ሣልሲትን በካልዕት፣ ካልዕቲን በኬክሮስ፣ኬክሮስን በሰዓት፣ ሰዓትን በእለት፣እለትን በሣምንት፣ ሣምንትን በወር፣ወርን በዓመት፣ሌሊትን ማዓልትን እያፈራረቀ የሚመግበን ፈጣሪ መሆኑን በቁጥር በሥፍራ የሚያስረዳ መጽሐፍ ማለት ነው፡፡ ሌላው የዘመን አቆጣጠርን የሚናገረው መጽሐፈ “አቡሻኸር” ሲሆን ይሕ ደግሞ አጠቃላይ የዓለም ሀገራትን የዘመን አቆጣጠር የሚናገር መጽሐፍ ነው፡፡ መጽሐፉም የተሰየመው አቡሻኸርን በጻፈው ዩሐንስ አቡሻኸር በሚባል በ፲፫/13/ ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በነበረ ግብጻዊ ምሑር ነው፡፡ አቡሻኸር ከሌሎች በተሻለ ስለ ዘመን አቆጣጠር /ቁጥር/ በስፋትና በጥልቀት ተንትኖ እንዳስረዳና በስሙ በዐረብኛ ቋንቋ የሚነገርለት በጣም ትልቅ መጽሐፍም እንደሆነ ይነገራል። ዘመኑ በህብረ ብሔራዊ ማንነታችን ውስጥ አንድነታችንን የምናጠናክርበት፤ የምንከባበርበትና የምንደማመጥበት እንዲሆንና ሀገራችን ያቀደችውን ሀገራዊ የልማትና የእድገት እቅድ እንደ ህዳሴ  ግድባችን በጋራ በማሳካት ዓለምን  የምናስደምምበት ዘመን እንዲሆን ተቋማችን ይመኛል። ለመላው ኢትዮጵያዊያን መልካም አዲስ ዓመት!

በደቡብ አሪ ወረዳ ለሚገኙ ትምህርት ቤቶች የመጽሐፍት ስጦታ ተበረከተ:: ጳጉሜ 3/2017 ዓ.ም ደቡብ አሪ ፤ ሸጲ የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ት/ት ቢሮ እና ወርልድ ቪዥን በአዘጋጅነት የተሳተፉበት "የንባብ ባህል ለት/ት ጥራት!" በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው የንባብ ሳምንት የሚመለከታቸው የመንግስት ከፍተኛ ኃላፊዎችና  ታዳምያን በተገኙበት በደቡብ አሪ ወረዳ ሸጲ የመጀመርያ ደረጃ ትምህርት ቤት ተካሔዷል። የዕለቱ የክብር እንግዳ የሆኑት የአሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ አብረሃም አታ የትምህርት ግብዓቶች እጥረት በመንግስት ብቻ የሚፈታ ባለመሆኑ የሁሉንም አካላት ትብብር የሚፈልግ ነው በማለት በጥምረት ስለተዘጋጀው ሁነት አመስግነዋል። የኢትዮጵያ ደራስያን ማህበር ፕረዝዳንትና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ክቡር አቶ አበረ አዳሙ ባስተላለፉት መልዕክት እውቀት እርቦናል በንባብ እንጥገብ፤ በኢትዮጵያ ሁሉም በአንድ አብሮ የሚነሳበት የንባብ አብዮት ያስፈልገናል በሚሉ ሀሳቦች ላይ ገለፃ አድርገዋል። ዝግጅቱ  የተማሪዎች የጥያቄና መልስ ውድድር እና የሽልማት መርሀ ግብር አካቷል። የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት በደቡብ አሪ ወረዳ ለሚገኙ ሁለት አንደኛ፣ ሁለት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እንደዚሁም ለጂንካ የሕዝብ ቤተ-መጻሕፍት በስጦታ ያበረከተውን  368,482 ብር  ያወጡ 1,205 መጻሕፍት የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት  ለደቡብ አሪ ወረዳ ት/ት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ካሳሁን አሰግድ እና ለደቡብ አሪ ዞን ባህል ቱሪዝም ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ጠልክስ አስረክበዋል።

በጂንካ ከተማ የንባብ  ሳምንት፣ አውደርዕይ እና ተንቀሳቃሽ የሕፃናት  ቤተ-መጻሕፍት በይፍ ተከፈተ ። ጷጉሜ 2/ 2017 ዓ.ም ጂንካ "የንባብ ባህል ለት/ት ጥራት!" በሚል መሪ ቃል በጂንካ ከተማ አንድነት ፓርክ የተሰናዳው የንባብ  ሳምንት፣ አውደርዕይ እና ተንቀሳቃሽ የሕፃናት  ቤተ-መጻሕፍት በይፍ ተከፈተ ። አቶ የሰዉዘር በላይነህ በትምህርት ሚኒስቴር የሚኒስትር  ዴኤታ አማካሪና  የሚኒስትር ዴኤታ ተወካይ ፣ አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ፣ አቶ ሲሳይ ጋልሺ የጂንካ ከተማ ከንቲባ ፣ ወ/ሮ ጸሐይ ወራሳ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ት/ት ቢሮ ኃላፊ፣ አቶ ውብሸት ደግነት  የወርልድ ቪዥን ደቡብ ፕሮግራም ጽ/ቤት ኃላፊ እንደዚሁም ጥሪ የተደረገላቸው ታዳምያን ተንቀሳቃሽ የሕፃናት ቤተ- መጻሕፍቱንና አውደርዕዩን ጎብኝተዋል። በመቀጠል  አለም አቀፍ የንባብ ቀንን ምክንያት በማድረግ የፓናል ውይይት ተደርጓል። የዕለቱ የክብር እንግዳ የሆኑት በትምህርት ሚኒስቴር የሚኒስትር  ዴኤታ አማካሪና  የሚኒስቴር ዴኤታ ተወካይ  አቶ የሰዉ ዘር በላይ የት/ት ፍኖት ካርታ ጥናት በሚጠናበት ወቅት መሠረታዊ የት/ት ጥራት ችግር የንባብ ክህሎት ችግር መሆኑ በግልፅ እንደተለየና ሁሉም ዜጋ በአፍ መፍቻ ቋንቋው እንዲማሩና እንዲያነቡ ማድረግ የመፍትሄ ምክር ሐሳብ  ተብለው ከተቀመጡ ነጥቦች መካከል አንዱ መሆኑን ገልፀዋል ። በመርሐ ግብሩ መልዕክታቸውን ያጋሩት የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት የንባብ ክህሎትና የንባብ ባህል በሁለት አበይት ጉዳዮች፡-  ከመሰረታዊ ክህሎት አንዱ አካል በመሆኑና የእድሜ ልክ የማይቋጭ የየዕለት ተግባር በመሆኑ የሁላችን ዋና ጉዳይ ይሆናል ሲሉ ገልፀዋል። አክለውም የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት  ንባብ በአንድ አዳራሽ ተወስኖ የሚቀር ነገር ባለመሆኑ በመላ የሀገሪቱ ክልሎች በመዘዋወር የንባብ ባህልን በማስፍፍት ላይ እንደሚገኝ ገልፀዋል። የፓናል ውይይቱን መነሻ የንባብ ባህልን ስለማዳበር የሚያትት ጥናታዊ ፅሑፍ ዶ/ር ብርሀኑ ቦጋለ የኢትዮጵያ ብሔራዊ  የንባብ ጥምረት የቴክኒክ ቡድን መሪና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ  አቅርበው ውይይት ተደርጎበታል ። በጂንካ ከተማ የተዘጋጀውን የንባብ  ሳምንት፣ አውደርዕይ፣ ተንቀሳቃሽ የሕፃናት  ቤተ-መጻሕፍት እና የፓናል ውይይቱን የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ት/ት ቢሮ እና ወርልድ ቪዥን " የንበብ ባህል ለትምህርት ጥራት! " በሚል መሪ ቃል በመተባበር አዘጋጅተውታል ።

ለጂንካ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም ከ90 ሺህ ብር በላይ ዋጋ ያላቸው መጻሕፍት በስጦታ ተበረከቱ:: ጷጉሜ 2/2017 ዓ.ም ጂንካ የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ከሚመለከታቸው አጋር አካላት ጋር በመቀናጀት በመላ ኢትዮጵያ በመዘዋወር እያካሔደ የሚገኘው "የንባብ ባህል ለትምህርት ጥራት!" ንቅናቄ ዛሬ ጳጉሜ 2/2017 ዓ.ም በጂንካ ማረማያ ፖሊስ ተቋም መካሔዱን ቀጥሏል። በመርሐ ግብሩ ላይ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የማረምና ማነጽ ተሀድሶ ልማት ዲቪዥን ኃላፊ ኮማንደር ደመቀ እንዳለ የጂንካ ማረሚያ ቤት 600 በላይ ታራሚዎችን፥ በአካባቢው  ከሚገኙ አቅመ ደካማ የሕብረተሰብ ክፍሎች ደግሞ ከ50 በላይ ሕፃናትን እንደሚያስተምር ገልጸው ለመማር ማስተማር ሒደቱ ትልቁ ችግር የነበረው ከመሐል ሀገር የራቅን እንደመሆናችን የመጻሕፍት እጥረት ነው ብለዋል፡ ፡ ለዚህም ዛሬ የተደረገው ድጋፍ ይበልጥ ለመስራት እንደሚያግዝ ገልፀዋል፡፡ የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት የስራ አመራር ስራ አስፈጻሚ አቶ አብነት አበራ በበኩላቸው ዛሬ ጷጉሜ 2 በሕብር ቀን ብዝሐ ሕዝብ ባለባት በጂንካ ከተማ በመገኘታችን ደስተኞች ነን ብለው ማረሚያ ቤት ብዙ ታላላቅ ሰዎች የሚወጡበት ተቋም እንደመሆኑ በቆይታችሁ መጻሕፍት የማንበብ ባህል አዳብራችሁ መልካም ተፅዕኖ መፍጠር ትችላላችሁ ሲሉ መክረዋል፡፡ በመርሐግብሩ ስነ ፅሑፍ ላቀረቡ ታሪሚዎች የመጽሐፍት ሽልማት ተበረክቷል ። የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ለጂንካ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም ከ90 ሺህ ብር በላይ ዋጋ ያላቸው 300 መጻሕፍትን የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት የስራ አመራር ስራ አስፈጻሚ አቶ አብነት አበራ ለኮማንደር ደመቀ እንዳለ በስጦታ አበርክተዋል።

"የንባብ ባህል ለትምህርት ጥራት!" ንቅናቄ በጂንካ ከተማ መካሔድ ጀመረ ። ======================= ጷጉሜ 1 /2017 ዓ.ም ጂንካ የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ከሚመለከታቸው አጋር አካላት ጋር በመቀናጀት በመላ ኢትዮጵያ በመዘዋወር እያካሔደ የሚገኘው "የንባብ ባህል ለትምህርት ጥራት!" ንቅናቄ ዛሬ ጷጉሜ 1 /2017 ዓ.ም በጂንካ ከተማ መካሔድ ጀምሯል። የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ከደቡብ ኢትዮጵያ ት/ት ቢሮ እና ከወርልድ ቪዥን ጋር በመተባበር በጂንካ ከተማ አንድነት ፓርክ የተዘጋጀው ይህ መርሐ ግብር የዝግጅት ምዕራፉን አጠናቆ ጎብኚዎችን እየተቀበለ ይገኛል ። ነገ ጷጉሜ 2/ 2017ዓ.ም  የክብር እንግዶች እና ታዳሚዎች በተገኙበት በይፍ ይከፈታል።