es
Feedback
የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት-Ethiopian Archives and Library Service

የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት-Ethiopian Archives and Library Service

Ir al canal en Telegram

.ይህ የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ይፋዊ የቴሌግራም ቻናል ነው፡፡

Mostrar más
El país no está especificadoLa categoría no está especificada
514
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
Sin datos30 días
Archivo de publicaciones
የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣የአብሮነት እንዲሆንላችሁ ይመኛል። ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!! ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/ ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572 ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr Twitter:https//@wemezekr    መልካም የትንሳኤ በዓል።

የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት በዓል አደረሳችሁ ይላል። ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት በዓል አደረሳችሁ ይላል። ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!! ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/ ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572 ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr Twitter:https//@wemezekr

https://www.youtube.com/watch?v=hiUcTAQhe84 ይህ መረጃ በኢትዮጵያ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር ) ከሚሰሩ በርካታ ተግባራቶች መካከል ከፊል ምልከታ የተቃኘበት ነው፡፡

መጋቢት 26/2018 ዓ.ም ብላቴን ጌታ ኅሩይ አዳራሽ የፕሮፌሰር አበበ ዘገየ "Sites of Remembering" ዐዲስ መጽሐፍ ተመረቀ። "Sites of Remembering" በፕሮፌሰር አበበ ዘገየ
+7
መጋቢት 26/2018 ዓ.ም ብላቴን ጌታ ኅሩይ አዳራሽ  የፕሮፌሰር አበበ ዘገየ "Sites of Remembering" ዐዲስ መጽሐፍ ተመረቀ።                      "Sites of Remembering" በፕሮፌሰር አበበ ዘገየ የተጻፈ፣ እጅግ አስተማሪ የኾኑ ጽሑፎች (Articles) ስብስብ መጽሐፍ የአፍሪካ ጥበብን ለዓለም አቀፍ ሥነ ጥበባዊ አስተሳሰብ ባበረከተው አስተዋጽዖ ምን ያህል ሥፍራ እንዳለው ለመመርመር የሚያነሳሱ ቀስቃሽ ጥያቄዎችን የያዘው መጽሐፍ በኢትዮጵያ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ተመርቋል። በፕሮፌሰሩ የመጽሐፍ ምርቃት ላይ የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት፣ አድናቂዎቻቸውና ጥሪ የተደረገላቸው ተሳታፊዎች ተገኝተውበታል። ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!! ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/ ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572 ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr Twitter:https//@wemezekr

ቅዳሜ መጋቢት 26 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 10:30 ጀምሮ በኢትዮጵያ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር)- በብላቴን ጌታ ኅሩይ አዳራሽ አይቀርም፡፡ ትንሽ ስለ ፕሮፌሰሩ ፕሮፌሰር
ቅዳሜ መጋቢት 26 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 10:30 ጀምሮ በኢትዮጵያ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር)- በብላቴን ጌታ ኅሩይ አዳራሽ አይቀርም፡፡ ትንሽ ስለ ፕሮፌሰሩ ፕሮፌሰር አበበ ዘገየ ማናቸው? የማስተማርና ስልጠና ማዕከል ተባባሪና መሥራች ዳይሬክተር፤ ኢትዮጵያ ውስጥ በሥርዓተ ትምህርቱ ዘርፍ በብርቱ አነጋጋሪ፤ አሳሳቢና መፍትሔ የሚፈልግ ሆኖ ስላለው የትምህርት ጥራት ደረጃና ተደራሽነት ተግዳሮቶችና አማራጭ የመፍትሔ ሃሳቦችን አንስተው አተያያቸውን የሚያጋሩ ለሀገር ይጠቅማል ብለው ከሚያነሷቸው ሃሳቦች አንኳሮች፡- • የትምህርት ጥራት ተደራሽነት • አንኳር የሥርዓተ ትምህርት ችግሮች • ፖሊሲ ቀረፃና ትግበራ • ጎሣ ተኮር የትምህርት ፖሊሲ • ብሔራዊ የማስተማሪያ ቋንቋ • ሥራና ምሩቃንን ማገናኘት የሚሉት በጥቂቱ ናቸው፡፡ ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!! ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/ ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572 ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr Twitter:https//@wemezekr

የአማራ ክልል ባሕል፣ቱሪዝም እና ስፖርት ቢሮ ከአጋር አካላት ጋር በመኾን የተፈጥሮ ጸጋዎችን ለቱሪዝም እድገት መጠቀም እንደሚገባ የዘርፉን ባለሙያዎች ለማብቃት በባሕር ዳር ከተማ በተዘጋጀ መርሐ ግብር ላይ ኢትዮጵያ ትልቅነቷ የሚገለጽበት የራሷ የኾነ የፊደል እና የጽሑፍ ሃብት ያላት ሀገር ናት (የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተ መዛግብት እና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት) https://web.facebook.com/share/p/1EWP2xTuGt/

መጋቢት 24/2018 ዓ.ም በባህር ዳር ዘላቂ የቱሪዝም ልማት ለማኅበረሰብ ተጠቃሚነት እና ለሁለንተናዊ ዕድገት በሚል መሪ ቃል ለቅርስ ጥበቃ እና ቱሪዝም ልማት ባለድርሻ አካላት የሥልጠና እና የንቅናቄ መድረክ በባህር ዳር ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። በንቅናቄ መድረኩ የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት፣የቱሪዝም ሚኒስትር ድኤታ አቶ ስለሽ ግርማ፣ ከዞንና የከተማ አሥተዳደሮች እንዲሁም ከወረዳዎች የተውጣጡ የዘርፉ ባለሙያዎች እና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛሉ። በንቅናቄ መድረኩ ንግግር ያደረጉት የአማራ ክልል ባህል ቱሪዝም እና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ መልካሙ ፀጋዬ የአማራ ክልል የበርካታ ቋሚ እና ተንቀሳቀሳሽ ቅርሶች ባለቤት መሆኑን ገልፀው እነዚህ ቅርሶች ለክልሉም ሆነ ለኢትዮጵያ ሕዝብ መለያ በመኾን ጥንታዊነትን፣ ታሪካዊነትን፣ ቀደምትነትን እና ታላቅነትን ሲያንጸባርቁ የኖሩ እና የሚኖሩ እውነተኛ ምስክሮች ናቸው ብለዋል፡፡ ኃላፊው አክለውም የክልሉን የቱሪዝም እንቅስቃሴ ለማነቃቃት በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝና የቱሪዝም ዘርፍ ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ ሚናው የጎላ መሆኑን አስታወሰው በክልሉ ያለውን እምቅ የቱሪዝም ሀብት ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመቀየር የሁሉንም ቅንጅት እንደሚጠይቅም ተናግረዋል። ለዚህም ከፌዴራል እና ከክልል ተቋማት ጋር በቅንጅት በመሰራቱ በመዳረሻ ልማት እና በቅርስ ጥገና ሥራዎች ዙሪያም ውጤታማ ሥራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል። ስልጠናው በቅርሶች ጥበቃና ቱሪዝም ልማት በትብብር በመስራት ውጤት ለማምጣት ያለመ እንደሆነም ተመላክቷል፡፡ ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!! ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/ ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572 ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr Twitter:https//@wemezekr

የፕሮፌሰር አበበ ዘገየ "Sites of Remembering" ዐዲስ መጽሐፍ ምረቃ፥ * ቅዳሜ መጋቢት 26 ቀን 2018 ዓ.ም. * ከቀኑ 10:30- 12:30 * በኢትዮጵያ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር)- በብላቴን ጌታ ኅሩይ አዳራሽ ይመረቃል። ኹላችሁም ተጋብዛችኋል። ***************** "Sites of Remembering" በፕሮፌሰር አበበ ዘገየ የተጻፈ፣ እጅግ አስተማሪ የኾኑ ጽሑፎች (Articles) ስብስብ ነው። መጽሐፉ የአፍሪካ ጥበብን ለዓለም አቀፍ ሥነ ጥበባዊ አስተሳሰብ ባበረከተው አስተዋጽዖ ምን ያህል ሥፍራ እንዳለው ለመመርመር የሚያነሳሱ ቀስቃሽ ጥያቄዎችን ይዟል። የባህል እና የዘመናዊነት፣ የአካባቢያዊ ሥር መሠረት እና የዓለም አቀፍ ውይይት መስተጋብርን በሚያሣዩ ኢትዮጵያውያን አርቲስቶች ምሣሌነት ይህንን ጽንሰ ሐሳብ ያፍታታዋል። 1- የሙላቱ አስታጥቄ "ኢትዮ-ጃዝ" በፖል ጊልሮይ "ጥቁር አትላንቲክ" (Black Atlantic) ጽንሰ ሐሳብ ውስጥ በሰፊው ተተንትኗል። ይህም የኢትዮጵያን የሙዚቃ ስሜት ከምዕራባዊ ጃዝ እና ከአፍሪካ ዲያስፖራ (እንደ አፍሮ ኪውባ) ካሉ ሙዚቃዊ ሥልተ ምቶች ጋር በማዋሐድ የተፈጠረውን የዲያስፖራ ድምፅ ያሳያል። የሙላቱ አስታጥቄ ሥራዎች፤ ድብልቅ የባህል መግለጫዎች ኾነው፣ እንደምን ዘረኛ እና ብሔርተኛ ድንበሮችን ሊፈታተኑ እንደሚችሉ፣ እንዲሁም ከአካባቢያዊ ቅርስ እና ከዓለም አቀፋዊ ወቅታዊ ኹኔታዎች ጋር የተጣጣመ አፍሪካዊ ማንነትን እንዴት ሊፈጥሩ እንደሚችሉ ዕይታ ይሠጣል። 2- መጽሐፉ፥ የሠዓሊ ዘሪሁን የትምጌታን የጥበብ ሥራንም ይዳስሳል። የዘሪሁን ሥዕሎች የኢትዮጵያን ጥንታዊ መንፈሳዊ ወጎች እና የክርስትና ምሥሎችን በመጠቀም ወቅታዊ ማኅበራዊ እና ፖለቲካዊ እውነታዎችን ይጋፈጣሉ። 3- የሠዓሊ ኤልያስ ስሜ ሥራዎች በዚሁ መጽሐፍ ውስጥ ይቃኛሉ። የኤልያስ "የድብልቅ ሚዲያ" (mixed-media) ሥራዎች የተጣሉ የቴክኖሎጂ ቁሳቁሶችን በመጠቀም፣ የሥነ ምኅዳራዊ ቀውስን ማሳየት እና የኅልውና ነጸብራቅ ትንሣኤን የሚያመላክቱ ምሥላዊ መልእክቶችን ይፈጥራሉ። ይህ መጽሐፍ በዘመናዊ የአፍሪካ ጥበብ ላይ እየተካሔደ ላለው የጥናት እና ምርምር ዘርፍ፣ መንገድ አመላካች ትልቅ አስተዋጽዖ ይኖረዋል። የጥበብ ታሪክን፣ የጥበብ ቲዎሪን፣ የባህል እና የድኅረ-ቅኝ ግዛት ጥናቶችን በመገዳደር ረገድ፥ ምሁራዊ ዋጋቸው እጅግ ከፍ ያሉ ሐሳቦችን ይዟል። በዚህ መጽሐፍ ምረቃ ላይ ለመገኘት አልጓጉም? የቅዳሜ 10:30 ቀጠሮዎ በኢትዮጵያ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) ብላቴን ጌታ ኅሩይ አዳራሽ ይኹን። የኢትዮጵያ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!! ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/ ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572 ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr Twitter:https//@wemezekr

ከፊውቸር ታለንት ት/ቤት የመጡ የቤተ-መጻሕፍት ክበብ አባላት ጉብኝት መጋቢት 18/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎትን ከፊውቸር ታለንት ት/ቤት የመጡ የቤ
+8
ከፊውቸር ታለንት ት/ቤት የመጡ የቤተ-መጻሕፍት ክበብ አባላት ጉብኝት መጋቢት 18/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎትን ከፊውቸር ታለንት ት/ቤት የመጡ የቤተ-መጻሕፍት ክበብ አባላትና የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ጎብኝተዋል። ተማሪዎቹ በተቋሙ የሚገኙ ስብስቦችን ለመቃኘት እና የሀገርን ታሪክ የመጠበቅ ወሳኝ ተግባራትን ለመማር ወደ ብሔራዊ ተቋም እንደመጡ ገልጸውልናል። በጉብኝታቸውም ጥንታዊ የብራና ጽሑፎች፣ ዘመናዊ የሥነ-ጽሑፍ ሀብቶች፣ በማይክሮ ፊልም፣ በድምጽና በምስል የሚገኙ የመረጃ ሐብቶችን እንዲሁም ታሪካዊ መዛግብትን በማየት በተቋሙ የሚገኙትን የዕውቀት ክምችት ለመረዳት ችለዋል። በህጻናት ቤተ-መጻሕፍት ክፍል በነበራቸው ቆይታም እነሱ ሲያነቡ ያደጉትን መጻሕፍት ለተቋሙ ለመለገስ ቃል ገብተዋል። ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!! ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/ ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572 ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr Twitter:https//@wemezekr

የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት በሚንስቴር መስሪያ ቤቱ ባልደረባ ወ/ሮ ራሄል ብርሃኑ ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለጸ ለወዳጅ ዘመዶቿና ለሥራ ባልደረቦቿ መጽናናትን
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት በሚንስቴር መስሪያ ቤቱ ባልደረባ ወ/ሮ ራሄል ብርሃኑ ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለጸ ለወዳጅ ዘመዶቿና ለሥራ ባልደረቦቿ መጽናናትን ይመኛል።

https://ethiopianreporter.com/153790/“ የንባብ ችግኝ በቀዳማይ ልጅነት መትክል!” በሚል መሪ ቃል መጋቢት /2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ በተካኤደ በስድስተኛው ዓመታዊ የሕጻናት የንባብ ጉባዔ ላይ የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሠርፀ ፍሬስብሃት የንባብ ልምድ ከሕጻንነት ጀምሮ መሠረት ካልተጣለበት፣ ሳይቃና ጊዜው እንዳለፈበት ችግኝ፣ ያልተስተካከለ ቁመና ይዞ የዜጎች የትምህርት አቀባበል ላይ ከፍተኛ ችግር ሊፈጥር ይችላል፡፡ የልጅነት ዘመንን ስናልፈው ምን እንወቅ፣ እንዴት እንወቅ፣ ያወቅነው ሁሉስ ይረባል? ብለን መጠየቅ እንጀምራለን ያሉት አቶ ሠርፀፍሬ፣ እርግጥ ነው ይህ ጥያቄ ዘመናት ያታከተ ጥያቄ ነው፣ ዕውቀት በምልዓት አወቅኩት ሊያስብል የሚችል ዕርካታ አለው ወይ? የሚለው እጅግ ጥልቅ ጥያቄ ነው፣ ይህንን ከሰው አዕምሮ ሊጠፋ የማይችል ጥያቄ በአንፃሩ እያቻቻለ፣ ከዕድሜ ጋር ተጋግዞ እየገራ ልክና መልክ ያለው ውል የሚያስይዘው ንባብ ነው ሲሉ መናገራቸውን ሪፖርተር ከዘገበው ……. የተወሰደ፡፡ ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!! ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/ ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572 ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr Twitter:https//@wemezekr

መጋቢት 8/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ ========= በአዲስ መልክ በተዘጋጀ መግባቢያ ሠነድ ዙሪያ ምክክር ተደረገ፡፡ የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ከአማራ ባህል ኪነ-ጥበብና ዝክረ ታሪክ ጽ/ቤት ጋር የክልሉን የባህል፣የኪነጥበብ እና የታሪክ ፍላጎቶችን በማሟላት ለህዝብ ተደራሽ ለማድረግ በአዲስ መልኩ የቀድሞዎችን የሙሉአለም የባህል ማዕከልንና የአማራ ህዝብ ዝክረ ታሪክ ማዕከልን በማዋሃድ በክልሉ አስፈጻሚ አካላት እንደገና ማቋቋሚያ፣ ሥልጣንና ተግባራት ላይ ከሚመለከታቸው የሥራ ክፍል ኃላፊዎች ጋር የእርስ በርስ ምክክር መድረክ አካሂደዋል፡፡ የምክክር መድረኩን ያስጀመሩት የአገልግሎቱ የጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አባተ ካሳው የአማራ ባህል ኪነ-ጥበብና ዝክረ ታሪክ ጽ/ቤት በአዲስ መልክ በዚህ ስም ተዋቅሮ መምጣቱ ይበል የሚያሰኝና ለእኛም ተቋም ምቹ ሁኔታን የፈጠረ እንደሆነና የዚህ ተቋም አስፈላጊነት በክልሉ የሚገኙ መዛግብቶች ተደራጅተው፣ተጠብቀው ለትውልድ ተሻጋሪ ለማድረግ ክልሉ ለዘርፉ ትኩረት በመስጠት የክልል ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት በዚህ መልክ እንዲደራጅ በክልል ምክር ቤት በአዋጅ አጽድቆ ማደራጀቱ ሊመሰገን እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ በዕለቱ የምክክር ሠነዱን ያቀረቡት በአማራ ባህል ኪነ-ጥበብና ዝክረ ታሪክ ጽ/ቤት የሙዚየም ቤተመጻሕፍት ዝክር ዳ/ዳይሬክተር ወ/ሮ አብነት ካሳሁን የጽ/ቤቱን ተልዕኮ በተመለከተ የክልሉን ህዝብ ባህል፣ኪነ-ጥበባትና የታሪክ ስራዎችን በማጥናት፣ በማደራጀትና በማስተዋወቅ ጥበባዊ እንቅስቃሴ ተሻሽሎ በባህሉ እና በታሪኩ የሚኮራ፣መልካም እሴቶችን የሚጠብቅና የሚያስተዋውቅ ንቁና ሁለንተናዊ ስብዕናው የተስተካከለ ዜጋ በመፍጠር የክልሉን መልካም ገጽታ በመገንባት ሁለንተናዊ ዕድገትን ለማምጣት ቁልፍ ሚና መወጣት ሲሆን ራዕይ የአማራ ባህል፣ ኪነ-ጥበብ እና የታሪክ እሴቶች ለምተው እና ተጠብቀው በ2027 በአገር አቀፍ ደረጃ ተመራጭ ተቋም ሆኖ ማየት እንደሆነም አስገንዝበዋል፡፡ የውይይቱን አስፈላጊነት በተመለከተ ዳይሬክተሯ ሲያቀርቡ ተሙ የያዛቸውን ግቦች ለማሳካት አጋር አካል ከሆነው ከኢትዮጵያ ቤተ መጻሕፍትና ቤተ መዛግብት አገልግሎት ጋር እንደ ሀገር ብሎም እንደ ክልል ስራዎችን በጋራ ለመስራት የጋራ ስምምነት ላይ ለመድረስ እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡ በዕለቱ የነበሩ የመወያያ ነጥቦች፡- ክልላዊ ቤተ መዛግብት ለማደራጀት በአዋጅ፣በስጦታ፣በግዥ፣በምርምር እንዲሁም በህግ የተገኙትን የአማራ ህዝብ ታሪክና ባህል ይዘት ያላቸውን ጽሑፎች፣ቀረጸ ድምጽና ቀረጸ ምስል እና የግለሰቦች የባዮግራፊ መረጃዎችን ድጋፍ፤የማህበረሰቡን የንባብ ባህል ለማሳደግ የማይቆራረጥ የንባብ ሳምንት በጋራ ማካሄድ፤በ2018 ዓ.ም በተያዘው የንባብ ሳምንት መሳተፍ፤የቤተ-መጻሕፍት፣ቤተ-መዛግብት እና በተለያዩ ቁስ ያሉ የጽሑፍ ቅርሶችን አሰባሰብ፣አደረጃጀት፣አያያዝና አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ለሚመለከታቸው ባለሙያዎች ስልጠናና ሙያዊ ድጋፍ፤ቤተመጻሕፍቱን ከ9ኛ እስከ ከፍተኛ ትምህርት ተማት ያሉ አጋዥ መጽሐፎችንና የአዲሱን የሥርዓተ ትምህርት መርጃ መጻሕፍት ድጋፍ፤የጽሑፍ ሰነዶች የዲጅታል /ማይክሮ ፊልም ቀጣይነትን በተመለከተ ነበር፡፡ በምክክር መድረኩ የተቋሙ የጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አባተ ካሳው፣የተቋ ሥራ አመራር አቶ አብነት አበራ፣የአማራ ባህል ኪነ-ጥበብና ዝክረ ታሪክ ጽ/ቤት ም/ኃላፊ ወ/ሮ የሺ ካሴ እና የሚመለከታቸው የስራ ክፍል ኃላፊዎች ተገኝተውበታል፡፡ በመጨረሻም በቀረበው የምክክር ሠነድ ዙሪያ የአሰራር ስርዓቱ ላይ በሁለቱም ጎን ሰፊ የመፍትሔ አቅጣጫ የሚባሉትን በመስማማት ምክክሩ ተጠናቋል፡፡ ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!! ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/ ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572 ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr Twitter:https//@wemezekr

የሀዘን መግለጫ የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጋሞ ዞን፣ ጋጮ ባባ ወረዳ፣ ላካ ቀበሌ በተከሰተ የመሬት መንሸራተት አደጋ፤ በዜጎቻችን ላይ በደረሰው ሞት እና መፈናቀል እጅግ ጥልቅ ሀዘኑን እየገለጸ። በዚህ አሰቃቂ አደጋ ህይወታቸውን ላጡ ቤተሰቦች፣ለወዳጅ ዘመዶቻቸው፣ ለጋሞ ዞን እና ለመላው የአገራችን ሕዝቦች መጽናናትን ይመኛል። ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!! ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/ ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572 ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr Twitter:https//@wemezekr

እንኳን ለዓለም አቀፉ የሴቶች ቀን ማርች 8 አደረሰን/አደረሳችሁ! የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ለተቋሙ ሴት አመራሮችና ባለሙያዎች ለመላው ኢትዮጵያውያን ሴቶች እንኳን ለዚህ ታላቅ ቀን አደረሳችሁ ይላል። በ50ኛው ዓመት የሴቶች ድምፅ ለእኩልነትና ለበለፀገች ኢትዮጵያ! በሚል መሪ ሃሳብ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ115ኛ በሀገራችን ኢትዮጵያ ለ50ኛ ጊዜ እየተከበረ ለሚገኘው የዘንድሮው የሴቶች ቀን (ማርች 8) እንኳን አደረሰን። አደረሳችሁ ይላል። መልካም የሴቶች ቀን! ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!! ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/ ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572 ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr Twitter:https//@wemezekr