es
Feedback
የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት-Ethiopian Archives and Library Service

የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት-Ethiopian Archives and Library Service

Ir al canal en Telegram

.ይህ የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ይፋዊ የቴሌግራም ቻናል ነው፡፡

Mostrar más
El país no está especificadoLa categoría no está especificada
509
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
Sin datos30 días
Archivo de publicaciones
የሰኞ ንጋት «እንገናኝ እንሰናኝ» ሁለተኛውን የሠራተኞች መድረክ  አገልጋይነትና በጎ ፈቃደኝነት ዙሪያ ውይይት ተደርጓል፡፡ ግንቦት 17/ 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ በዛሬው የሰኞ ንጋት «እንገናኝ እንሰናኝ» መድረክ በበጎ ፈቃደኛው መሐመድ ካሳ አቅራቢነት አገልጋይነትና በጎ ፈቃደኝነት ከተቋማዊ አሰራር፣ ከማህበራዊ እሴትና ከአለም አቀፋዊ ተሞክሮዎች አንጻር በስፋት ተዳሷል። በማንኛውም ዘመንና ሁኔታ ኃላፊነትን መወጣት፣ በቃል የነበረውን በወረቀት፣ የወረቀቱን ዲጂታይዝ አድርጎ በብዙ ውጣ ውረድ መጠበቅ፣ ዕውቀትን ከመጥፋትና ከመረሳት ታድጎ ከትውልድ ጋር ማሰናኘት የተቋማዊ አገልጋይነት ዐብይ ጉዳይ እንደሆነ ተነስቷል። የማህበራዊ እሴቶቻችን ለምሳሌ፦ የእርቅ ሥርዓቶች፣ የሐዘን የማርዳት ልማድ፣ እንግዳ ተቀባይነት፣ እንዲሁም የልምድ አዋላጆችና የወጌሻዎች ጥበብ የአገልጋይነት ትልቅ ማሳያዎች ናቸው። እነዚህ ተግባራት ማን እንዳደረገልን እስክንረሳ ድረስ ከታይታ በራቀ መልኩ በበጎነት የሚከናወኑ መሆናቸው ተብራርቷል። በኢትዮጵያ ዓለም ስለ ሰብዓዊ መብት ማቀንቀን ከመጀመሩ በፊት የላቀ ሰብዓዊነት ይተገበር እንደነበር የአድዋ ጦርነትን በማጣቀስ ተገልጿል። በጦር ሜዳ የወደቁ የጠላት ወታደሮችን አስክሬን በሰብዓዊነት እስከ መቅበር፣ አልፎ ተርፎም ለቤተሰቦቻቸው የፍቅር ደብዳቤ በሚመስል ትሕትና የሐዘን መርዶ እስከ መላክ የደረሰ የላቀ ማንነት እንደነበረን ተወስቷል። አገልጋይነት ለሰዎች የግል ስብዕና መቃናት፣ ለክህሎት ማደግና ለዕውቀት መበልጸግ የሌሎችን ምቾት ሳይነሱ የራስን አስተዋጽዖ ማበርከት ነው፤ ሁሌም በላጩ ሰው እንደሆነ ለሰዎች መልካም ነገርን በበጉ ፈቃደኝነት በመስራት ማሳየት አለብን የሚሉት በመድረኩ ትኩረት የተደረገባችው ርዕሰ ጉዳዮች ነበሩ። በጎ ፈቃደኛ መሐመድ ካሳ ሰፊ የአገልጋይነትና የበጎ ፈቃደኝነት ተሞክሮ ያላቸው ሲሆን  ከነዚህም መካከል፦ በአፍሪካ የበጎ ፈቃደኝነት አምባሳደር በመሆን ማገልገላቸው፣ «ጥበብ ለተፈጥሮ» የሚል የአካባቢ ጥበቃ ላይ የሚያተኩር ንቅናቄን መምራታቸው፣ በመላው ኢትዮጵያ ለወጣቶች የበጎ ፈቃደኝነት ስልጠና መስጠታቸውና የ«ጉዞ አድዋ» መስራቾች መካከል አንዱ መሆናቸው ይጠቀሳሉ።   ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!! ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/ ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572 ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr ትዊተር:https//@wemezekr ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/

"እንገናኝ እንሰናኝ!" የሠራተኞች የሠኞ ንጋት መድረክ በየኹለት ሳምንት የሚቀርበው መድረካችን ሁለተኛ ዙሩን ነገ ግንቦት 17/2018 ዓ.ም ማለዳውን ያካሒዳል። ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!! ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/ ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572 ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr ትዊተር:https//@wemezekr ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/

የቻይና የትምህርት ዘርፍ ልዑካን በባህልና በእውቀት ላይ ከተቋሙ ጋር ለመስራት ተነሳሽነታቸውን ገለጹ ኢትዮጵያ እና ቻይና ቀደምት የሆነ የስልጣኔ ታሪክ ያላቸው እንደመሆናቸው ይህንን ስልጣኔ በእኩል እይታ በጋራ ማሳደግ እንዳለባቸው የገለጹት የቻይና የባህል እና የትምህርት ዘርፍ ልዑካን ግንቦት 14 ቀን 2018 ዓ.ም ተቋሙን በጎበኙበት ወቅት ነው። በዚህም ከኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት የንባብ፣ የታሪክና የመረጃ ሀብቶች ጋር በተያያዘ በጋራ ለመስራት ዕቅድ እንዳላቸው አስታውቀዋል። የቻይና ልዑካኑ ዛሀኦ ዚያንሺ በቻይና የትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ቴክኖሎጂ እና የትምህርት መርጃ ልማት ማዕከል ምክትል ዋና ዳይሬክተር፣ ሊ ጂንፔንግ በቻይና የትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ቴክኖሎጂ እና የትምህርት መርጃ ልማት ማዕከል የዲቪዥን ዳይሬክተር፣ ሺን ዩን በቻይና የትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ቴክኖሎጂ እና የትምህርት መርጃ ልማት ማዕከል የዲቪዥን ዳይሬክተር እና ኪን ዚዩቢንግ የቻይና ኢምባሲ በኢትዮጵያ የባህል ቢሮ ተቀዳሚ ጸሐፊ ናቸው። ልዑካኑ በኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ጉብኝታቸው በጣም መደሰታቸውንና ኢትዮጵያ በዩኔስኮ ያስመዘገበቻቸው የጽሑፍ ቅርሶች የተቋሙ አካል ሆነው በማየታቸው አድናቆታቸውን ገልጸዋል። በተለይም በጥንታዊ የስነ ጽሑፍ ሀብቶች ላይ በተቋሙ የተሰራው የማሰባሰብ እና የመጠበቅ ስራን የበለጠ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተናግረዋል። የልዑካን ቡድኑ ከተቋሙ በጋራ ለመስራት የሚያግዙ ሁኔታዎችን ለመፍጠር እንዲቻል በጉብኝቱ ማብቂያ ላይ ከዋና ዳይሬክተር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አባተ ካሳው እና ከሰነድና መዛግብት አስተዳደር መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ሰለሞን ጠና ጋር ውይይት አድርገዋል። ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!! ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/ ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572 ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr ትዊተር:https//@wemezekr ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/

የኃላውን ያላወቀ የወደፊቱን ለማወቅ ይከብደዋል፡፡ የቀድሞ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕረዘዳንት (ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ) ግንቦት 14/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ለታላቁ የጥበብ ፈርጥ የበርካታ ግጥምና ዜማዎች ፕሮዲውሰር ያየህይራድ አላምረው እህት ወ/ሮ ሒሩት አላምረው  እና ለአቶ ዘላለም አላምረው (ሼፍ ዚ) የምስጋና የምስክር ወረቀት አበረከተ፡፡ የዛሬዎቹ ተመስጋኞቻችን ወ/ሮ ሒሩት አላምረው እና ዘላለም አላምረው (ሼፍ ዚ) በዚሁ ዓመት በታኀሣሥ 22/2018 ዓ.ም የታላቅ ወንድማቸውን የታላቁን የጥበብ ፈርጥ የበርካታ ግጥምና ዜማዎች ፕሮዲውሰር ያየህይራድ አላምረው በሕይወት ዘመኑ ያሰባሰባቸውን ከአምስት ሺህ በላይ መጻሕፍት፣ ጋዜጣ፣የጽሑፍ እና የሙዚቃ ኅትመት ውጤቶችን ውድ ስብስቦች ራሱን የቻለ ቦታ በመስጠት የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት በስሙ የተሰየመ የንባብ ክፍል በማዘጋጀት አደራጅቶ ለንባብ ክፍት በማድረግ ለተተኪው ትውልድ የሚጠቅም ታላቅ ስራ መሰራቱ የሚታወስ ነው፡፡ ዛሬ ግንቦት 14/2018 ዓ.ም ወ/ሮ ሒሩት አላምረው እና አቶ ዘላለም አላምረው (ሼፍ ዚ) የታላቁን የጥበብ ፈርጥ የበርካታ ግጥምና ዜማዎች ፕሮዲውሰር ያየህይራድ አላምረው የጽሑፍ ሀብቶች በክብር ተጠብቆ ለአንባቢ ክፍት ወደተደረገበት እና በስሙ ለተሰየመው ቤተመጻሕፍት ለሚያነቡ ተገልጋዮች በቀላሉ የሚጠቀሙበት ግምታቸው ከ1ሚልየን ብር በላይ የፈጁ ሁለት ኮሙፒውተር ለተቋሙ በስጦታ  አበርክተዋል፡፡  በእውቅና መርሐ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎትን በመወከል ንግግር ያደረጉት አቶ መኮንን ከፋለ ተቋሙ በርካታ የአገር ሀብትን ጠብቆና ሠንዶ ለትውልድ የሚያስተላልፍ ሀገራዊ  ተቋም በመሆኑ የዛሬ ተመስጋኞች የታላቁ አገር ወዳድ የታላቁ የጥበብ ፈርጥ የበርካታ ግጥምና ዜማዎች ፕሮዲውሰር ያየህይራድ አላምረው ቤተሰቦች ይሄንን ለአገር እና ለትውልድ የሚጠቅም ስራ በመስራታችሁ ተቋማችን ከልብ ያመሰግናችኋል ብለዋል። የምስጋናና የእውቅና መርሐ ግብሩ ላይ በእንግድነት የተገኙት የቀድሞ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕረዘዳንት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ ዛሬ ያየህይራድ በህይወት ባይኖርም ለትውልዱ በማሰብ የሰበሰባቸው ሀብቶቹ የሀገር ሀብት እንዲሆኑ ጠብቆ ያቆያቸውን ቤተሰቦቹ በዚህ መልክ ወደዚህ ሀገራዊ ተቋም ወደሆነው ግዙፍ ተቋም ተጠብቆ ለትውልዱ እንዲያገለግል በማድረጋችሁ ክብር ይገባችኃል። አክለውም ለንባብ ክፍት የተደረገው በወንድማችሁ ስም ለተሰየመው ቤተመጻሕፍት ቤት አንባቢ እንዲጠቀምበት ዘመኑን የማከለ ኮምፒውተር እንደሚያስፈልገው አውቃችሁ ለዚህ አገራዊ ተቋም በወንድማችሁ ስም በማበርከታችሁ ለእናንተም ለወንድማችሁም ትልቅ ደስታን ይሰጣል ብለዋል።የኃላውን ያላወቀ የወደፊቱን ለማወቅ ይከብደዋል። ወ/ሮ ሒሩት አላምረው ተቋሙ ላደረገላቸው ሁሉ አመስግነው በስጦታ ከተሰጠው ኮምፒውተሮች በተጨማሪ በወንድማቸው  ስም ለተሰየመው ቤተመጻሕፍት አስፈላጊ ናቸው የሚባሉ ቁሳቁሶችን ሁሉ ከሟሟላት ወደኃላም እንደማይሉ ቃል ገብተዋል። በመጨረሻም ከተቋሙ የተዘጋጀውን የእውቅና የምስክር ወረቀት ለሁለቱም በማበርከት ዝግጅቱ ተጠናቋል፡፡ በእውቅናና የምስጋና መርሐ ግብሩ ላይ የቀድሞ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕረዘዳንት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ፣ የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ተወካይ እና የተቋሙ የአብያተ መዛግብትና አብያተ መጻሕፍት ስልጠናና ምክር መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ መኮንን ከፋለ፣ የተቋሙ የማኔጅመንት አባላት፣ወ/ሮ ሒሩት አላምረው እና አቶ ዘላላም አላምረው እንዲሁም የቅርብ ወዳጆቻቸው ተገኝተዋል። ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!! ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/ ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572 ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr ትዊተር:https//@wemezekr ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/

የሕትመት ቅጂ ለቤተመዛግብት አገልግሎት እንዲቀርብ ተጠየቀ ግንቦት 13 ፣ 2018 ዓ.ም ሀገሬ ቴቪ :- የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት የትኛውም ዓይነት ህትመት 3 ቅጂ እንዲሰጠው
የሕትመት ቅጂ ለቤተመዛግብት አገልግሎት እንዲቀርብ ተጠየቀ ግንቦት 13 ፣ 2018 ዓ.ም ሀገሬ ቴቪ :- የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት የትኛውም ዓይነት ህትመት 3 ቅጂ እንዲሰጠው በህግ የተደነገገ ቢሆንም አሳታሚዎች ህትመቶቻቸውን ለተቋሙ እየሰጡ አለመሆኑን አስታውቋል። ቀደም ባሉ ዓመታት የህግ ቅጣትን በመፍራት እንዲሁም ህትመቶች ቅርስ ሆነው እንዲቀመጡ በማሰብ አታሚ ድርጅቶች እንዲሁም ግለሰቦች ለወመዘክር የምስል፣ የመጻሕፍት እንዲሁም የትኛውንም የሕትመት ውጤት 3 ቅጂ ያቀርቡ እንደነበር የኢትዮጵያ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰርጸ ፍሬስብሐት ገልፀዋል። በቀጣይ እንደ ሀገር ቅርሶችን የማዳን ዘመቻ መጀመር እንዳለበት የገለጹት ዳይሬክተሩ፤ ቅጂዎች ከያሉበት ተሰብስበው መሰነድ እንዳለባቸው አሳስበዋል። የትኛውንም ቅጂ ለተቋሙ መስጠት እንደሚያስፈልግ በተለያየ መንገድ ግንዛቤ እየተሰጠ ስለመሆኑም የተገለጸ ሲሆን፤ በቀጣይ የሕግ እርምጃዎች እንዲጀመሩ ግፊት እንደሚደረግ ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል። በማሕበራዊ መገናኛዎቻችን መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ: https://www.facebook.com/hagerietv ትዊተር: https://twitter.com/HagerieT ኢንስታግራም:https://www.instagram.com/hagerie_television ቴሌግራም: https://www.t.me/Hagerie_TeleVision ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/hagerietv ዌብሲይት: https://www.hagerie.tv

በሕትመት ውጤቶች አሰባሰብና በአዋጅ ቁጥር 179/91 ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ ተካሄደ ግንቦት 13/ 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት አሳታሚዎች፣ ደራስያን፣ የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች፣ የመንግሥትና የግል ተቋማት ተወካዮች እና የተለያዩ ማህበራት በተገኙበት የሕትመት ውጤቶችን ማሰባሰብና በአዋጅ ቁጥር 179/91 አፈጻጸም ዙሪያ ያተኮረ ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ የምክክር መድረክ አካሄደ። የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት በመድረኩ መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ "የተቋማችን ማንነት የቆመው እናንተ የፈጠራ ውጤት ውስጥ፣ እናንተ አእምሮ ውስጥና እዚህ ይቀመጥልን ብላችሁ በምታስቀምጡት ሀብት ላይ ነው" በማለት የባለሙያዎችንና የባለድርሻ አካላትን አስተዋጽኦ አጉልተዋል። የመረጃ ሀብቶች አስተዳደር መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ስለሺ ሽፈራው በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ የራሷ ፊደልና ጥልቅ የሥነ-ጽሑፍ ታሪክ ቢኖራትም እስካሁን የተሰባሰቡ የሕዝብ የአእምሮ ሀብቶች ካለን እምቅ አቅም አንጻር በቂ እንዳልሆኑ ገልጸዋል። ለዚህም ዋነኛው ምክንያት በአዋጅ ቁጥር 179/91 የተቀመጠው የሕትመት ውጤቶችን ለብሔራዊ ቤተ-መጻሕፍት የማስረከብ ግዴታ በተሟላ ሁኔታ ተፈጻሚ አለመሆኑን ጠቁመዋል። በመድረኩ ላይ አዋጅ ቁጥር 179/91 በደራስያንና አሳታሚዎች ላይ ጫና ለመፍጠር ሳይሆን፡- የቅርስና የፈጠራ ባለቤትነትን ለማረጋገጥ፣ ፍትሐዊና ማዕከላዊ የመረጃ ተደራሽነትን ለመፍጠር፣ የዲጂታል ሕትመቶችን በማካተት የሀገሪቱን የዕውቀት ሀብት ሙሉ በሙሉ ለመመዝገብ የታለመ እንደሆነ ተብራርቷል። የኦዲዮ ቪዥዋል ቅርስ ጥበቃ እና በሕግ ሥርዓት የማስቀመጥ ጠቀሜታ በአቶ ሠርፀ ፍሬ ስብሐት፣ ዲበ ውሂብ፡ ለሕትመት ጥራት እና ተደራሽነት በዶ/ር ደርብ አዶ፣ እንደዚሁም የመረጃ ሀብቶች አሰባሰብ ሥርዓት ከአዋጅ 179/1991 አኳያ በአቶ እስራኤል በዙ የቀረቡ ጥናታዊ ጽሑፎች ለውይይቱ መነሻ የሆኑ ሲሆን፤ ተሳታፊዎችም ተቋሙ ሥራዎቹን ይበልጥ ማስተዋወቅ እንዳለበት፣ የአዋጁ ተፈጻሚነት እስከ መጨረሻው የሕግ አግባብ መከተል እንደሚገባውና መሰል መድረኮች በቋሚነት እንዲቀጥሉ ምክረ-ሐሳብ አቅርበዋል። በመጨረሻም ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ሠርፀ ፍሬ ስብሐት እንደገለጹት ተቋሙ የኢትዮጵያን የ2030 የዲጂታይዜሽን ግብ ለማሳካት ከኢኖቬሽንና ሳይንስ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ዘመናዊ የዲጂታይዜሽን ማሽኖችን አስገብቷል። ይህም በተቋማችን የሕትመት ውጤቶችን ዲጂታይዝ የማድረግ ሰፊ ስራ ሲጠናቀቅ ጥበበኛው ሥራውን መስጠት ብቻ ሳይሆን ከሥራው መጠቀም የሚያስችለውን አሠራር ያካተተ መሆኑ ተገልጿል። መድረኩ በአውዲዮ ቪዥዋል አውደ-ርዕይ ጉብኝት ተጠናቋል።   ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!! ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/ ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572 ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr ትዊተር:https//@wemezekr ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/

ታላቅ ሙያዊ የምክክር መድረክ በኢትዮጵያ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት የሕትመት ውጤቶች ጥበቃና ሕጋዊ ርክክብ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ሊካሔድ ነው፡፡ የሀገራችን የታሪክና የእውቀት አሻራዎች ሳይጠፉ ለቀጣዩ ትውልድ እንዲተላለፉ የበኩላችሁን ድርሻ እየተወጣችሁ ነው? የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ከተመሰረተበት 1936 ዓ.ም ጀምሮ የሀገሪቱን የጽሑፍ፣ የድምፅ እና የምስል መረጃዎችን በመሰብሰብና በማደራጀት ለትውልድ እንዲተላለፉ በታማኝነት ሲያገለግል የቆየ አንጋፋ ተቋም ነው። ተቋሙ በአዋጅ ቁጥር 179/1991 የተሰጠውን ኃላፊነት መሠረት በማድረግ፣ ማንኛውም አሳታሚ፣ ደራሲ፣ የማተሚያ ድርጅት እንዲሁም የመንግሥትና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት የሚያዘጋጇቸውን የሕትመት ውጤቶች (መጻሕፍት፣ መጽሔቶች፣ ጋዜጦች፣ የድምፅና ምስል መረጃ ሀብቶች) ሦስት (3) ቅጂዎችን የመረከብ ሥልጣን አለው። ሆኖም በአተገባበር ሂደት ላይ የሚታዩ የግንዛቤ ክፍተቶችን ለመቅረፍ ተቋማችን የአንድ ቀን የግንዛቤ ማስጨበጫ የፓናል ውይይት ግንቦት 13 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30  ጀምሮ ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ትልቅ የምክክር መድረክ አዘጋጅቷል። 🎯 ዓላማ፦        👉🏽በአዋጅ ቁጥር 179/1991 ላይ ግልጽ ግንዛቤ መፍጠር፤        👉🏽ከባለድርሻ አካላት ጋር የተሻለ የአሠራር ሥርዓት መዘርጋት፤   የሕትመት እና የጥበብ ውጤቶች ለቀጣዩ ትውልድ የማስተላለፍ ሀገራዊ አደራ የሁላችንም በመሆኑ፣ የሚመለከታችሁ ባለድርሻ አካላት ሁሉ በዕለቱ ተገኝታችሁ የመፍትሔው አካል እንድትሆኑ በአክብሮት እንጋብዛለን።         📅ቀን፦ ግንቦት 13 ቀን 2018 ዓ.ም         🕒ሰዓት፦ ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ         🏛ቦታ፦ በተቋሙ ቅጥር ግቢ ውስጥ በሚገኘው መርስዔ ኃዘን ወልደ ቂርቆስ አዳራሽ ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!! ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/ ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572 ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr ትዊተር:https//@wemezekr ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/

የማህበረሰብ ዕድገት መሰረቱ እውቀት ነው።እውቀት ደግሞ የሚቀሰመው ከንባብ ገጾች ነው።   ግንቦት 8/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት "የንባብ ባህል ለትምህርት ጥራት!" በሚል መሪ ቃል አዲስ ህይወት በሃያት የጋራ መኖሪያ ቤቶች የሕጻናት የንባብ ሳምንት ተካሒዷል። የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የጋራ መኖሪያ ቤቱ የልማት ኮሚቴው ጸሐፊ ወ/ሮ ጸደይ አለነ  የዛሬው እለት ለማኀበረሰባችን ትልቅ ትርጉምና የላቀ እሴት ያለው ታላቅ በመሆኑ ይህን የንባብ ባህል ለማጎልበት፣ሕጻናትና ወጣቶች ከመጽሐፍት ጋር ያላቸውን ትስስር ለማጥበቅ፣እንዲሁም በእውቀት የዳበረ ትውልድ ለመቅረጽ በጋራ በመቆማችን ታላቅ ኩራትና ደስታ ይሰማናል። "አንባቢ ሕዝብ የበለጸገ ሕዝብ ነው" እንደሚባለው የማህበረሰብ ዕድገት መሰረቱ እውቀት ነው።እውቀት ደግሞ የሚቀሰመው ከንባብ ገጾች ነው።መጽሐፍት የአስተሳሰብ አድማስን ያሰፋሉ፤ የሰውን አርቆ አሳቢነት ያሳድጋሉ፤ሰውን ወደላቀ የሕይወት ምዕራፍ እንደሚመሩ በተለይም ለሕጻናት ንባብ የፈጠራ ችሎታና የአእምሮ ዕድገት መሰረት፣ለወጣቶች ደግሞ ጊዘዜያወቸውን በአዎንታዊና  ፍሬያማ በሆነ መንገድ እንዲጠቀሙበት የሚያስችል ታላቅ መሣሪያ እንደሆነ ተናግረዋል። የተቋሙ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ሀገሬ መኮንን በመክፈቻ ንግግራቸው እንደዚህ ዓይነት ኃላፊነት በሚኖርባቸው ጠንካራ አመራሮች ባሉበት ስለሕጻናት የሚያስቡ ለነገ ሀገር  ተረካቢ ተተኪ ይሁኑልን የምትሉ እና የምትተሳሰቡ ነዋሪዎች ባላችሁበት ተቋሙ አልፎ አልፎ የሕጻናት የንባብ ሳምንታቶችን እንደሚያዘጋጅ እና ከጥቂቶቹ አንዱ በመሆናችሁ የእናንተ ልጆች እድለኞች ናቸው ብለዋል። አክለውም ለልጆቻችሁ የምትቆረቆሩ ወላጆች እና በተለይ አመራሮቹ በሕጻናት ላይ መስራት ቀላል አይደለምና ከዚህ በተሻለ ከጠነከሩ ከዚህ ውስጥ ዶክተሮች፣መምህራኖች፣ኢንጅነሮች ወዘተ የሚፈጠሩት ከዚህ መሐል በመሆኑ የተሻለች ኢትዮጵያንና  ሀገር ተረካቢ ዜጋን ለመፍጠር የሁላችንንም ርብርብና ተጋግዞ መስራት እንደሚጠይቅ ተናግረዋል። ወጣቶች ላይ የንባብ ክህሎታቸውን ለማምጣት እኛም መላጆች በማንበብ ልምድ ለልጆቻችን ማካፈል እንደሚኖርብንና ቀድመን እኛ ስንለወጥ ልጆችንንም አንባቢ ማድረግ እንችላለን ብለዋል።  ተቋሙ ከዚህ በፊት አዲስ ህይወት በሃያት የጋራ መኖሪያ ቤቶች ስር ለሚገኘው የሕዝብ ቤተ-መጻሕፍት የተለያዩ ይዘት ያላቸው በበጀት ከ300 ሺህ ብር በላይ የፈጁ  600 መጽሐፍት በስጦታ በማበርከት በአሁን ወቅት በርካታ ተማሪዎች የሚገለገሉበት እንዲሆን እንዳስቻለም ተነግሯል። በዝግጅቱም የሕጻናት መጽሐፍት ለእይታና ለንባብ ሲበቁ፣የህጻናት ስዕል መሳል፣ የአሸንጉሊት ትርኢት፣ በኮሜድያን አስረስ በቀለ የተዘጋጀ አስተማሪ አጭር ጭውውት፣ተረት እና ጥያቄ ለሕጻናቱ ቀርቧል። በመጨረሻም ግጥም ላቀረቡ፣ በንቃት ሲከታተሉን ጥያቄ ሲመልሱ ለነበሩ ሕጻናቶች ከተቋሙ የተዘጋጀ መጽሐፍ በስጦታ ተበርክቶላቸው ከዚህ በፊት በጋራ መኖሪያ ቤቱ ለተደራጀው ቤተመጻሕፍት አጠቃቀም ከባለሙያዎች ሃሳብ በመስጠት የተደራጀውን ቤተመጻሕፍት በተሳታፊዎች ተጎብኝቶ መርሐ ግብሩ ተጠናቋል። ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!! ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/ ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572 ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr ትዊተር:https//@wemezekr ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/

ለልጆችዎ የንባብና የደስታ ግብዣ! የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት አንዱ ዓላማ ትውልዱ በእውቀትና በክህሎት የዳበረ እንዲሆን የንባብ ባህልን ማስፋፋት ነው ። ይህንኑ ተልዕኮ ለማሳካት ተቋሙ ከግንቦት 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ አዲስ ሕይወት  በሃያት የጋራ መኖሪያ ቤቶች ልዩ የሕጻናት የንባብ ሳምንት ለማካሄድ ዝግጅቱን አጠናቋል ። 👥የዝግጅቱ ታዳሚዎች፡- ከተለያዩ ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ የአንደኛ ደረጃ መምህራንና ተማሪዎች፣መልዕክት ያላቸውን ስራቸውን የሚያቀርቡ የህጻናት መጽሐፍ ጸሐፊ ደራሲያን፣ትምህርት አዘል የኪነ ጥበብ ስራዎቻቸውንና ሰርከስ የሚያቀርቡ ቡድኖች፣የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት፣የሚድያ አካላት እና ጥሪ የተደረገላቸው እንደሆኑ ተጠቁሟል። 🎯የዝግጅቱ ዓላማ፦ በትምህርትና በንባብ ላይ የተሰማሩ ባለድርሻ አካላትን በንባብ ላይ የጋራ ቅንጅታዊ ሥራ ለመስራትና በቀጣይ የሕጻናት የንባብ ባህል እንዲያድግና እንዲስፋፋ ለማስቻል ነው። 💡የዝግጅቱ አስፈላጊነት፦ 👀የንባብ ባህል ለማዳበር 👀በንባብ ባህል የታነጸ አንባቢ ትውልድ በመፍጠር ሀገሩን የሚወድ ዜጋ ለመፍጠር 👀ከባለድርሻ አካላት ጋር ተቀራርቦ በጋራ በመስራት ባለድርሻ አካላት ዘርፉን በማልማት ረገድ ያላቸውን ከፍተኛ ሚና ለማጎልበት በዝግጅቱ የሚቀርቡ✨ 🤸🏾‍♂️ አስደናቂ የሰርከስ ትርኢት፤ 📖 በታዋቂ ደራሲያንና የዘርፉ ባለሙያዎች የሚቀርብ የንባብ ተሞክሮ፤ 📝 አዝናኝ ተረቶች፣ ግጥሞች እና ትምህርታዊ ንባቦች፤ 🧠 በተቋሙ ድህረ ገጽና በሚዲያ የሚተላለፉ የተማሪዎች የጥያቄና መልስ ውድድር 🎁 ለተማሪዎች የሚበረከቱ የመጽሐፍ ስጦታዎች 🎭 የሕጻናት የንባብ ባህልን ለማሳደግ የሚያግዙ መዝሙሮች፣ ድራማዎች እና አዝናኝ ትምህርት ሰጪ ቀልዶች ይህ ዝግጅት በታዋቂ ደራሲያን፣ በተማሪዎችና በባለሙያዎች ደምቆ በሃያት የጋራ መኖሪያ ቤቶች በድምቀት ይካሄዳል ። 📅 ቀን፦ ግንቦት 8 / 2018 ዓ.ም 📍 ቦታ፦ አዲስ ሕይወት በሃያት የጋራ መኖሪያ ቤቶች ልጆችዎን ይዘው በመምጣት የዕውቀት በዓሉ ተሳታፊ ይሁኑ! 👨‍👩‍👧‍👦📚✨    ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!! ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/ ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572 ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr ትዊተር:https//@wemezekr ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/