es
Feedback
የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት-Ethiopian Archives and Library Service

የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት-Ethiopian Archives and Library Service

Ir al canal en Telegram

.ይህ የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ይፋዊ የቴሌግራም ቻናል ነው፡፡

Mostrar más
El país no está especificadoLa categoría no está especificada
509
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
Sin datos30 días
Archivo de publicaciones
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት ከብፁዕ ካርዲናል ብርሃነ ኢየሱስ ሱራፌል ጋር የቤተክርስትያንዋ የጽሑፍ ቅርሶች እንዲሁም የድምጽና የምስል ሀብቶች ጠብቆ ለትውልድ ከማሻገር አንጻር ጥልቅ ውይይት አደረጉ። ሰኔ 10/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎትም ወደ ካቴድራሉ ሲያቀና ዓላማ ያደረገው እንደ ሀገር የተሰጠውን ስልጣንና ኃላፊነት ተግባራዊ በማድረግ የቤተክርስትያኗ መዛግብቶች ካሉበት ተሰብስበው በተቋሙ በቤተክርስቲያኗ ስም ስያሜ ቦታ ተሰጥቷቸው  ለተመራማሪዎች፣ ለአንባቢያን ተደራጅተው እንዲቀመጡ በማድረግ እና ሰንዶ ለመጪው ትውልድ በማቆየት እንዲሻገሩ ለማስቻል እንዲሁም ከታሪክ ተጠያቂነት ለመዳን እንደሆነ አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት ለብፁዕ ካርዲናል ብርሃነ ኢየሱስ በስፋት አስረድተዋል። የይፋዊ ውይይቱ ዋነኛ ዓላማንም አቶ ሠርፀ ለብፁነታቸው ሲያስረዱ ሦሥት ትላልቅ ጉዳዮችን ዓላማ ያደረገ እንደሆነ አንደኛው የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያንን ታሪካዊ መዛግብት፣ መጻሕፍት፣ ፎቶግራፎች፣ ኦዲዮ ቪዥዋል ቅርሶች እና የኀትመት ውጤቶች በጋራ በመለየት ወደ ብሔራዊ ቤተመዛግብት በማምጣት ዘላቂ ጥበቃ እንዲደረግባቸው ማድረግ በሁለተኛነት በቤተክርስቲያኒቱ የሥነ-መለኮት ዩኒቨርሲቲዎች እና በቅድስት መንበረ ቫቲካን ባለው የኢትዮጵያ ገዳም የሥነ መለኮት የሚካሔዱ የምርምር ሥራዎችን ለተመራማሪዎች እንዲደርሱ በማድረግ በብሔራዊ የዕውቀት ክምችት ማበልጸግ እና በ3ኛነት ኃላፊው ያቀረቡት ተቋሙ ካለው የረዥም ጊዜ ልምድ በመነሳት ለቤተክርስትያኑቱ የቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት ክፍል የቴክኒክ ድጋፍ እና ሥልጠና ለመስጠት ዝግጁ መኾኑን አስረድተዋል። ብፁዕ ካርዲናል ብርሃነ ኢየሱስ ሱራፌል፣ ከኢትዮጵያ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በጽሕፈት ቤታቸው በነበራቸው የውይይት ጊዜ፣ የቤተክርስቲያኒቱን ጥልቀት ያለው ታሪክ በሰፊው አስረድተዋል። በተለይም፥ "የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ታሪካዊ ጉዞ እና የካቶሊክ ሃይማኖት በኢትዮጵያ ያለው ታሪክ ጥልቅ፣ ውስብስብ እና የኢትዮጵያን የፖለቲካና የባህል ታሪክ በቅርበት የተሳሰረ ነው። ፖርቹጊዞች የፕሪስተር ጆንን ሀገር ከመፈለግ ጉዟቸው፣ በተለይም ከፍራንሲስኮ አልቫሬዝ ጀምሮ በትልቅ ፍላጎት እና አድናቆት የታየች ሀገር ናት።  የካቶሊክ ሃይማኖት  በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ በተለይም በ16ኛው እና በ17ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ከፖርቱጋልና ከስፔይን በመጡ ጄዝዊት ሚሽነሪዎች አማካኝነት ነበር።"ይላሉ ብፁዕ ካርዲናል ብርሃነ ኢየሱስ። በ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የክሪስቶቫዎ ዳጋማ የጦር ሠራዊት መምጣት እና ከጦር ኃይሉ ጋር አብረው የገቡት የካቶሊክ ሚሽነሪዎች (ጄዝዊት)፣ እንደ ፔድሮ ፓኤዝ ያሉ ሚሽነሪዎች በጎርጎራ፣ በደንቀዝ እና በሌሎች የጎንደር አካባቢዎች አብያተ ክርስቲያናትን በመገንባት፣ የሕንፃ ጥበብን በማስተዋወቅ ትልቅ ተጽዕኖ ፈጥረው ነበር።" "የካቶሊክ ሃይማኖት የአዲግራት እና የዓድዋ አካባቢ እንደ ፍሬሞና በመሳሰሉ ቦታዎች የካቶሊክ እምነት የትምህርት እና የሃይማኖት ማዕከል ኾነው አገልግለዋል። በተለይም በአሊተና እና በኢሮብ አካባቢዎች የካቶሊክ እምነት ከባህላዊው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ጎን ለጎን ተቀባይነትን በማግኘት፣ የራሱ የኾነ አሻራ ዐሳረፈ። የኤርትራው ከረንም የካቶሊክ ሚሽነሪዎች በጤና እና በትምህርት መስክ የገቡበት ትልቅ ማዕከል ነበር። በዘመኑ የነበረው የኅትመት ውጤቶች፣ እንደ እምኩሉ የካቶሊክ ማተሚያ ቤት ያሉ ተቋማት፣ ሃይማኖታዊ መጻሕፍትን በማሳተም ረገድ ትልቅ ሚና ተጫውተዋል።" "በ19ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በሐረር ከተማ በአባ እንድርያስ ጃሮሶ አማካኝነት የተነሳሳው የካቶሊክ ሃይማኖት መንፈሳዊ መነቃቃት፣ ካቶሊካዊነት ከሰሜን ወደ ምስራቅ ኢትዮጵያ እንዲስፋፋ አድርጓል።" "ኾኖም የካቶሊክ ቤተክርስቲያን በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ፈታኝ ወቅቶችን አሳልፋለች። የጣሊያን ወረራ (1928-1933 ዓ.ም.) አንዱ ወሳኝ ወቅት ነበር። ጣሊያኖች የካቶሊክ እምነትን ለፖለቲካ ዓላማቸው በመጠቀም፣ ከሌሎች አገራት የመጡ ሚሽነሪዎችን በማባረር፣ የራሳቸውን ጣሊያናዊ ሚሽነሪዎች ብቻ እንዲሰብኩ በማድረጋቸው በቤተክርስቲያኗ ላይ ጥላ ሆኖ ቀርቷል። በዚህ ሒደት ውስጥ፣ በተለይም የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን አማኞች በሕዝብ ዘንድ ጥርጣሬ ውስጥ እንዲወድቁ የተደረገበት እና የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን እንደ "ወራሪ" መሣሪያ እንድትታይ የተደረገበት አስቸጋሪ ጊዜ ነበር።" "የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን በኢትዮጵያ የትምህርት ታሪክ ውስጥ ያላት አስተዋጽዖ ተወዳዳሪ የለውም። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ (የቀድሞው ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ) ሲቋቋም የካቶሊክ ሚሽነሪዎች፣ በተለይም አሜሪካዊያኑ የኢየሱሳውያን አባቶች (Jesuits) የነበራቸው ሚና የመሠረተ ድንጋይ ዓይነት ነበር። የልደታ ካቴድራል እና ሌሎች አብያተ ክርስቲያናት አካባቢ የተገነቡ ትምህርት ቤቶች ለሀገሪቱ የሰው ኃይል ግንባታ ትልቅ ድርሻ አበርክተዋል። የጤና ተቋማት፣ ሆስፒታሎች እና የሰብአዊ ተራድዖ ሥራዎች ቤተክርስቲያኗ እንደ ማኅበረሰብ ግንባታ ማዕከል እንድትታይ አድርገዋታል።" የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ታሪክ የኢትዮጵያ ታሪክ አካል ኾኖ በምርምር እና በጽሑፍ ተጠብቆ እንዲቆይ ማድረግ ብሔራዊ ግዴታ ነው። የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን መሪ የኾኑት ብፁዕ ካርዲናል ብርሃነ ኢየሱስ ሱራፌል ይህንን ጉዳይ በሰፊው ያንፀባርቃሉ። ብፁዕ ካርዲናል እንደሚሉት፣ በዘመናት ውስጥ የተፈጠሩት የቤተክርስቲያኗ ታሪካዊ ሠነዶች፣ መጻሕፍት፣ የካርታ መረጃዎች፣ የሕክምና እና የትምህርት ተቋማት መዛግብት የኢትዮጵያ ሀብት ናቸው። እርሳቸው እንደሚያስረዱት፣ እነዚህን አያሌ የታሪክ ማስረጃዎች በኢትዮጵያ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ውስጥ ተሰብስበው እና ተደራጅተው መቀመጣቸው የኢትዮጵያ ታሪክ ሙሉ እንዲኾን ያደርጋል። ይህ የትውልድ ቅርስ የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያንን ሃይማኖታዊ ትግል ብቻ ሳይኾን፣ ለሀገር ግንባታ ያበረከተችውን አወንታዊ አስተዋጽዖ ለቀጣዩ ትውልድ በግልጽ ለማሳየት ያስችላል ብለዋል። በመጨረሻም አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት ብፁዕነታቸው የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎትን እንዲጎበኙ በመጋበዝ እና የካቴድራሉን የአገልግሎት ክፍሎችን በመጎብኘት ተጠናቋል። ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!! ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/ ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572 ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr ትዊተር:https//@wemezekr ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/

ተቋማት በህጋዊ መንገድ ሰነዶችን በማስወገድ መዛግብትን ለትውልድ በማስተላለፍ ምቹ የስራ አካባቢን ሊፈጥሩ እንደሚገባ ተገለጸ። ተቋማት በህጋዊ መንገድ ሰነዶችን በማስወገድ መዛግብትን ለትውልድ በማስተላለፍ ምቹ የስራ አካባቢን ሊፈጥሩ እንደሚገባ የተገለጸው በአዋጅ ቁጥር 179/91 በተለይም በአንቀጽ 14:1 በግልጽ በተቀመጠው መሠረት ሰነዶችን የማስወገድ ስልጣን የተሰጠው ለኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት መሆኑን በመገንዘብ ሰነዶቻቸው እንዲወገዱላቸው ለተቋሙ ላቀረቡ ሁለት ተቋማት ሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም የውገዳ ማረጋገጫ ሰርተፍኬት በተሰጠበት መድረክ ነው። የቆዩ እና ከአገልግሎት ውጪ የሆኑ ሰነዶቻቸው እንዲወገዱላቸው ያቀረቡት የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሲሆኑ፤ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን  107.4.5 ሊንየር ሜትር (193 አቃፊ _ 573 ጥራዝ) እንዲወገድላቸው አቅርበው ከዚህም 7 አቃፊ ወደ መዛግብት ክምችት መካተቱንና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ለሁለተኛ ዙር 514 ሊንየር ሜትር እንዲወገድላቸው አቅርበው 12 ሰነድ ወደ መዛግብት ክምችት መዘዋወሩን የገለጹት የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት የአብያተ መዛግብትና አብያተ መጻሕፍት ስልጠናና ምክር መሪ ስራ አስፈጻሚ እንዲሁም የብሔራዊ ሰነድ አስወጋጅ ሰብሳቢ አቶ መኮንን ከፋለ ናቸው። በተጨማሪም የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት 16.8 ሊኒየር ሜትር የሚወገዱ ሰነዶች ቀርበው ሁለት አቃፊዎች የቆይታ ጊዜያቸውን እስኪጨርሱ መቀመጣቸውን አቶ መኮንን አሳውቀዋል። የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣንን ወክለው የተገኙት ወ/ት ቆንጂት ታምራት እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክን ወክለው የተገኙት አቶ ዳዲ መኮንን ሰነዶቹ በህጋዊ መልኩ እንዲወገዱ በመደረጉ የስራ አካባቢያቸውን ምቹ እንዳደረገላቸውና በዘርፉ ላይ ከተቋሙ ጋር በስልጠናም ሆነ በስራ የሚኖራቸው ግንኙነት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። ተቋማቱ ሰነዶቹን በህጋዊ መንገድ እንዲወገዱ በማምጣታቸው በውገዳ ሂደቱ በምዘናና መረጣ የተለዩት መዛግብት ወደ ክምችት በመውሰድ ለተቋማቱ የመዛግብት ስብስብ ኮርነር አዘጋጅተን ለአጥኚዎችና ለተመራማሪዎች አገልግሎት እንሰጣለን ያሉት አቶ መኮንን፤ ተቋማቱ እነዚህን ሰነዶች ለማስቀመጥ ቦታ ቢከራዩ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ከ1.03 ሚሊዮን ብር በላይ በአመት እንዲሁም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከ4.93 ሚሊዮን ብር በላይ በአመት ሊያወጡ ይችሉ እንደነበር ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አባተ ካሳው ለሁለቱም ተቋማት ህጋዊ የሰነድ ውገዳ ማረጋገጫ ሰርተፍኬት በሰጡበት ወቅት ተቋማቱ በህጋዊ መልኩ ሰነዶችን በማስወገዳቸው ለእራሳቸው ምቹና ፅዱ የስራ አካባቢ ከመፍጠራቸው ባለፈ ተቋሙ ለትውልድ ባህል፣ወግ፣እሴትንና ታሪካችንን የሚያስተላልፈው በሰነድ እንደመሆኑ እያንዳንዱ ተቋም ምን ሰራ? የሚለውን አደራጅተን ለማቅረብ በምናደርገው ጥረት የእራሳቸውን አሻራ ስላሳረፉ ሊመሰገኑ እንደሚገባ ገልጸዋል። ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!! ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/ ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572 ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr ትዊተር:https//@wemezekr ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/

የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ታላቅ የዲጂታይዜሽን ፕሮጀክት በይፋ አስጀመረ ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር፣ የ«ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030» ስትራቴጂካዊ ግብ አካል የሆነውን ዘመናዊ የዲጂታይዜሽን ፕሮጀክት በይፋ አስጀምሯል። በምረቃ መርሐግብሩ ላይ የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት ባስተላለፉት መልዕክት፤ የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) ባለፉት 83 ዓመታት እጅግ ውድ የሆነውን የሀገሪቱን የጽሑፍ ሀብት በብሔራዊ ደረጃ ለመሰብሰብ፣ ለመጠበቅና ለትውልድ ለማሻገር ዕድል ያገኘ ቀዳሚ ተቋም መሆኑን ገልጸው ኢትዮጵያ የጽሑፍ ታሪኳ ጥንታዊና የስልጣኔ ምልክት የታየባት ቀዳሚ ሀገር ብትሆንም፣ የጽሑፍ ሀብቷን በሥርዓት የሚሰበስብ ዘመናዊ ስርዓት በማደራጀት በኩል ግን የታሪኳን ያህል ፈጣን እንዳልነበረች አንስተዋል። ይሁን እንጂ ይህንንም የታሪክ ምዕራፍ የሚቀይርና ያለንን ታሪካዊ ሀብት ወደ መላው ዓለም በዲጂታል መረብ የምታገናኝበትን የቴክኖሎጂ ሽግግር ዛሬ ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ ማብሰሯን ገልጸዋል። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶ/ር በለጠ ሞላ በበኩላቸው፤ በሀገራችን ትናንት በርካታ ታሪካዊ ክንዋኔዎች መፈጸማቸውን፣ ብዙ እውቀቶች መመንጨታቸውንና ድርሳናት መጻፋቸውን አስታውሰዋል። እነዚህ ውድ ሀብቶችና እውቀቶች ዕድሜያቸው ሲገፋ ተበላሽተውና ወድቀው እንዳይቀሩ ወደ ነገ ማሻገር እንደሚገባ ጠቁመው፤ ቴክኖሎጂ የሰጠንን ትልቅ አቅም ተጠቅመን የትናንትን አድሰን ወደ ነገ ማሻገር መቻላችን ትልቅ ስኬት መሆኑን አብራርተዋል። ሚኒስትሩ አክለውም ዲጂታል ኢትዮጵያ ስንል ከዛሬና ከወደፊቱ ጉዟችን ባሻገር ወደኋላም ተመልሰን ታሪካችንን በዲጂታል ማዕቀፍ ውስጥ ማካተትን ይጨምራል። ትናንትን በማደስ፣ ዛሬን በማጎልበትና ነገ ደግሞ አዳዲስ እውቀቶችን በተግባር ላይ በማዋል የተሟላ የዲጂታል ኢኮኖሚ ለመገንባት የሚያስችል ትልቅ ፕሮጀክት ነው ብለዋል። በመርሃ-ግብሩ ላይ የተገኙት የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ወ/ሮ ሸዊት ሻንካ በበኩላቸው፤ ዛሬ የተበሰረው ፕሮጀክት በኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ ተግባር የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን ታላቅ ሀገራዊ ግብ እውን ለማድረግና ለትውልድ የምትተርፍ ሀገር ለመገንባት ትልቅ አበርክቶ ያለው በመሆኑ፣ ፕሮጀክቱ እስከሚጠናቀቅበት ጊዜ ድረስ በተሟላ ቁርጠኝነትና በትጋት እንዲሰራ በአደራ ጭምር አሳስበዋል። ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር በርካታ የመንግሥትና የግል ተቋማት የቴክኖሎጂ ድጋፍ ጥያቄ አቅርበውለት የነበረ ቢሆንም የመረጃ ሀብቶቹን ወደ ዲጂታል የመቀየርን አስቸኳይነት በከፍተኛ ትኩረት በመገንዘብ ለቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ቅድሚያ በመስጠት እውን ያደረገው ፣  ዓለምአቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ እጅግ ዘመናዊ የዲጂታይዜሽን ቴክኖሎጂዎችን፣ ሶፍትዌሮችንና የሀርድዌር ሥርዓቶችን ያካተተ፣ ከእነዚህም መካከል ለጥንታዊ መጻሕፍት ልዩ ጥንቃቄ የሚያደርጉ ዘመናዊ የመጻሕፍት ስካነሮች፣ የሰነድና የካርታ መዛግብት ስካነሮች እንዲሁም የተደራጁ የኮምፒውተር አውታረ-መረብ መሰረተ-ልማቶች በአጠቃላይ 792,422 (ሰባት መቶ ዘጠና ሁለት ሺህ አራት መቶ ሀያ ሁለት) የአሜሪካ ዶላር ወይም በወቅታዊ ምንዛሬ 126,787,520 (መቶ ሀያ ስድስት ሚሊዮን ሰባት መቶ ሰማኒያ ሰባት ሺህ አምስት መቶ ሀያ) የኢትዮጵያ ብር ወጪ የተደረገበት ነው። ይህ የተዘረጋው ቴክኖሎጂ በተቋሙ ውስጥ ያሉትን የጽሑፍ ሀብቶች በሙሉ አቅም ወደ ዲጂታል ለመቀየር የሚያስችል ቋሚ መሰረተ-ልማት ሲሆን፤ ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር በተያዘው በዚህ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ምዕራፍ ላይ 20 ሚሊዮን ገጾችን ወደ ዲጂታል የመቀየር ሥራ በፓይለት ፕሮጀክትነት በተሳካ ሁኔታ ለማጠናቀቅ ዕቅድ ተይዟል። ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!! ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/ ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572 ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr ትዊተር:https//@wemezekr ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/

በተቋሙ በሚገኙ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት የሜታዳታ አመዘጋገብ ዙሪያ በዘርፉ እየሰሩ ለሚገኙ ባለሙያዎች ሦሥተኛ ዙር የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሠጠ። ሰኔ 7/2018 ዓ.ም አዳማ ጥራት ያለው ሜታዳታ የተሻለ መዳረሻ፣የተሻለ ጥበቃ እና የተሻለ ዕውቀት ማጋራትን ያረጋግጣል ተባለ። የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት በተቋሙ የሚገኙ የሀገር መረጃዎችን ጥራት ያለው ሜታዳታ ውስጥ በማስገባት ሰዎች ወደ ተቋሙ መምጣት ሳይጠበቅባቸው መረጃ ማግኘት እንዲችሉ በዘርፉ ለሚሰሩ ባለሙያዎች አንድ ዓይነት አረዳድ እንዲኖራቸው የሚያስችል የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል። በግንዛቤ ማስጨበጫው በመገኘት መልዕክት ያስተላለፉት የተቋሙ ሥራ አመራር አቶ አብነት አበራ ይሄ ስልጠና ለሦሥተኛ ዙር እንዲሰጥ የተፈለገው በዘርፉ የሚሰሩ ባለሙያዎች የተለያየ እና የተዘበራረቀ የመረጃ አሞላል  እንዳላቸው በመገንዘብ የተዘጋጀ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና እንደሆነ ተናግረው  ይሄንን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ካገኙ በኃላ ስራውን የሚሰሩ ባለሙያዎች አንድ ዓይነት አረዳድ ኖሯቸው በዲጅታል 2030 ዓ.ም በመንግስት ደረጃ ለተያዘው ዲጂታል ኢትዮጵያ ትኩረት የተሰጠውን እንደ እኛ ተቋም የሚገኙ የሀገር መረጃዎች ሜታዳታ በትክክል መሙላት እንዲችሉ እና የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ለማበርከት እንደሚያስችላቸው ጠቁመዋል። ጥራቱን የጠበቀና ግልጽ የሆነ ሜታዳታ ካልያዝን እንደ ተቋም ከተመረጡ ተቋሞች ውስጥ ላንገባ ስለምንችል ይሄንን ስልጠና በማግኘታችሁ መረጃውን ወጥ በሆነ መልኩ መያዝ እንድንችልና ጥራት ያለው ሜታዳታ ተመዝግቦ መረጃው ለመረጃ ፈላጊዎች ግልጽ ሆኖ መቀመጥ እንዲቻል ለዘርፉ ባለሙያዎች እየተሰጠ የሚገኘው የግንዛቤ ማስጨበጫው ስልጠና ወቅቱን ያማከለ እንደሆነም ተናግረዋል። ይህንን ጊዜውን የዋጀ ስልጠና አዘጋጅቶ እየሰጠ የሚገኘው የኢንፎርሜሽን ኮሚኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ አቶ ግዛው ዋቅጅራ በግንዛቤ ማስጨበጫው የሜታዳታ ምንነት፣ በቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት ውስጥ የሚገኙ መጻሕፍት፣ሰነዶች፣ ፎቶ ግራፎች፣ካርዶች፣ዲጅታል ፋይሎች እና ሌሎች ሀብቶች ለመግለጽ ለማደራጀት፣ ለሚፈልግ እና ለሚጠብቅ የሚያገለግል የተዋቀረ መረጃ መሆኑን ሲያስገነዝቡ የሜታዳታ አስፈላጊነትንም የመረጃ ፍለጋን እንደሚያሻሽል፣ የስብስብ አስተዳደርን እንደሚያቀላጥፍ፣ ዲጅታል ጥበቃንም እንደሚያጠናክር፣የመረጃ ልውውጥንም እንደሚያሳልጥ ጠቁመው የሚታዩ ተግዳሮቶችን በተመለከተ የባለሙያ እጥረት፣ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ውስንነት፣የሜታዳታ ቁጥጥር አለመዘርጋት፣መመዘኛ /መስፈርት/አለመኖር፣የመረጃ ጥራት ችግርም እንደሚገጥም ዳታ ጀምሮ የማቋረጥ ነገርም እንደሚኖር ተናግረዋል። ስራ አስፈጻሚው ባቀረቡት የግንዛቤ ማስጨበጫ ጽሑፋቸው በማጠቃለያነት ሜታዳታ በቤተ መዛግብትና ቤተመጻሕፍት ውስጥ የመረጃ አስተዳደር ፍለጋ፣ጥበቃ እና የመረጃ ልውውጥ መሠረታዊ መሣሪያ እንደሆነም ጠቁመው አክለውም ሜታዳታ በመረጃ አስተዳደር ተደራሽነት እና ጥበቃ መሠረት መሆኑንም ገልጸዋል። በመቀጠል በአብያተ መጻሕፍት መረጃ ሃብቶች መሪ ስራ አስፈጻሚ የማደራጃ ዴስክ ከፍተኛ ባለሙያ ወ/ሮ ሂሩት ካሳ ILARMs Essentials: Standard Cataloging Training እና የመዛግብት ማደራጃ ዴስክ ኃላፊ በአቶ አብይ ብሩክ ደግሞ በመዛግብት አደረጃጀት ከምዘና መረጣ ጅምሮ፣ አደረጃጀቱን፣ የመግለጫዎች አዘገጃጀቱን፣ ለመዛግብቱ እንክብካቤና ጥበቃ በማድረግ እንዴት አገልግሎት ላይ እንደሚውሉ እንዲሁም መዛግብት በ Integrated Library, Archives and Records Management System (ILARMS) Software እንዴት መዛግብቱ እንደሚደራጁ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጥቷል። በቀረቡት ሰነዶች ላይ ጥያቄ፣ሃሳብ አስተያየት ሲቀርብ ሰልጣኞቹ ስልጠናው ከበፊቱ በተሻለ እውቀት ኖሯቸው እንዲሰሩ በባለሙያዎች በታገዝ ዳታ እንዲያስገቡ ልምምድ ሲያደርጉ፤ከዚህ ቀደም በእቅድ ተለክቶ የተሰጣቸውን ዳታ የማስገባት ስራም በተቀመጠው እቅድ መሰረት አጠናክረው እንዲሰሩ ስራውን ከሚከታተሉ ሥራ አስፈጻሚዎች መልዕክት ሲተላለፍ በስልጠናው የዲጂታላይዝድ ባለሙያዎችም መሳተፍ እንደነበረባቸው ተመላክቷል። ስልጠናውን ለሰራተኞቹ ያመቻቸው የተቋሙ የሰው ሀብት አስተዳደር እና ብቃት  የሥራ ክፍልም ስልጠናዎች መዘጋጀት ያለባቸው ከባለሙያው የአቅም ክፍተት በመነሳት እንደሆነ ዛሬ ከነበረው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መረዳት እንደተቻለ ተጠቁሟል። ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!! ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/ ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572 ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr ትዊተር:https//@wemezekr ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/

በሥነ ጥበብ ታሪክ ውስጥ ደማቅ አሻራ ላኖረው ታላቁ የጥበብ ሰው እውቅ ተሰጠ። የኢትዮጵያ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት በኢትዮጵያ ሥነ ጥበብ ታሪክ ውስጥ ደማቅ አሻራ ያኖረው፣ ብዕራዊ ለዛው ፍጹም አቻ ያልነበረው ባለቅኔ፣ ጸሐፌ ተውኔት እና የዘፈን ግጥም ደራሲ ሙሉጌታ ተስፋዬ ተወልዶ ባደገባት በወልዲያ ከተማ በስሙ የተሰየመ ቤተመጻሕፍት በቅርቡ ተመርቆ ለአንባቢያን ክፍት መደረጉ፥ ተቋማችን ትልቅ ዕውቅና የሚሠጠው በእጅጉ የሚመሰገን ተግባር ነው። ይህ በወልዲያ ከተማ አስተዳደር የባህል፣ ቱሪዝም እና ስፖርት መምሪያ አማካኝነት የተገነባው ዘመናዊው "የባለቅኔ ሙሉጌታ ተስፋዬ የሕዝብ ቤተመጻሕፍት"፤ ባለቅኔው ለኢትዮጵያ ሥነ ጥበብ ካለምንም ምንዳ ያበረከተውን ውድ የጥበብ ሥጦታ ለማሰብ የተቋቋመ የመጀመሪያው ታላቅ መታሰቢያ መኾኑን ተቋማችን ይገነዘባል። "ሰው የተፈጠረው ንጉሥም ቅዱስም ለመኾን ነው፤" በሚለው ጥልቅ ፍልስፍናው እና በዕውቀትም በመንፈስም በበሰለ ማንነቱ የሚታወቀው ሙሉጌታ ተስፋዬ፤ በኢትዮጵያ ሥነ ጥበብ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ቦታ የሚሠጠው ጠቢብ ነው። በተለይም በ1977 ዓ.ም. በወሎ የተከሰተውን ድርቅ ተከትሎ፣ "እውነት ከመንበርህ የለህማ!" በሚለው ግጥሙ የገለጸው ጥልቅ ሰብዓዊ ሩኅሩኅ ስሜት፣ እውነተኛውን የጠቢብነት ባሕርዩን የሚመሰክር ነው። ባለቅኔው በሙዚቃው ዘርፍም የነበረውን ታላቅ ቅኔያዊ ዐቅም፤ ለአበበ ተካ፣ ለጼዴንያ ገ/ማርቆስ፣ ለሐና ሸንቁጤ፣ ለብጽዓት ሥዩም፣ ለዣን ሥዩም ኄኖክ፣ ለፍቅረዐዲስ ነቅዓ ጥበብ፣ ለማርታ አሻጋሪ እና ለአበበ ብርሃኔ ባበረከታቸው የዘፈን ግጥሞች በተግባር አስመስክሯል። ተቋማችን ይህንን ታላቅ የጥበብ ሰው የሚዘክር ቤተመጻሕፍት በመገንባት ለባህል፣ ለጥበብ እና ለዕውቀት በሀገር ደረጃ የሚታወቅ ሥራ ላበረከቱ ኢትዮጵያውያን መታወሻ የማቆም ተግባርን በምሣሌነት ላሳየው ለወልዲያ ከተማ አስተዳደር አድናቆቱን እየገለጸ፤ ይህ ቤተመጻሕፍት የበርካታ አንባቢዎች የዕውቀት ማዕከል ኾኖ እንዲያገለግል ተቋማዊ ድጋፋችን እንደማይለያቸው በዚሁ አጋጣሚ ይገልጻል። ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!! ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/ ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572 ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr ትዊተር:https//@wemezekr ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/

የሰኞ ንጋት «እንገናኝ እንሰናኝ» መድረክ፦ ትስስራችንን እናጠንክር፣ በርኅራኄ  እንተያይ ሰኔ 1/ 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ በ3ኛው ዙር «እንገናኝ እንሰናኝ» የሰኞ ንጋት መድረክ የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት «ትስስራችንን እናጠንክር፣ በርኅራኄ እንተያይ» በሚል መሪ ሐሳብ ለተቋሙ ባልደረቦች ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በመድረኩ ላይ አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት እንደገለጹት፣ ሕዝቦች በተሳሰረ ማንነትና በትብብር አብረው አገርን እንደሚገነቡ እንጂ አንድ ወገን ብቻውን ቆሞ አገር ማቅናት እንደማይችል አስገንዝበዋል። ይህንን እውነት ወደ ተቋማዊ አሠራር ስናመጣውም፣ በተቋሙ ውስጥ ቀድሞ የነበረውም ሆነ ዘግይቶ የተቀላቀለው ሠራተኛ ሁሉ «ተቋም» በሚለው የጋራ ጥላ ሥር የየራሱን አሻራ እንደሚያሳርፍና ለጋራ ስኬት እንደሚሠራ አብራርተዋል። ዋና ዳይሬክተሩ በትብብርና አብሮነት ጉዞ ውስጥ ወሳኝ የሆኑትን Apathy (ግዴለሽነት)Sympathy (አዘኔታ) እና Empathy (የስሜት ተካፋይነት) የተሰኙ ሦስት ቁልፍ ፅንሰ-ሐሳቦችን በጥልቀት ዳስሰዋል። የቃላቱ ትርጉምና በተቋማዊ ግንባታ ላይ ያላቸው ሚናም በመድረኩ ላይ በሚከተለው መልኩ ተብራርቷል፦ Apathy (ግዴለሽነት)፦ የሌሎችን ሁኔታ፣ ችግርም ሆነ ደስታ ምንም ዓይነት ስሜት ሳይሰጡ በቸልተኝነት ማለፍ ሲሆን፣ ይህ ዓይነቱ አመለካከት የተቋምን ትስስር የሚጎዳ እንደሆነ ተገልጿል። Sympathy (አዘኔታ)፦ የሌላውን ሰው ችግር ወይም ስቃይ ከውጭ ሆኖ ማዘንና «አይዞህ» ማለት ሲሆን፣ ምንም እንኳ መልካም ቢሆንም ብቻውን ግን በቂ እንዳልሆነ ተብራርቷል። Empathy (የስሜት ተካፋይነት)፦ እራስን  በሌላው ሰው ቦታ ተክቶ፣ ያ ሰው ያጋጠመውን ችግር በእራስ ላይ እንደደረሰ አድርጎ የመረዳት ጥበብ ነው። አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት  አክለውም፣ «Empathy (የስሜት ተካፋይነት) ማለት የኛን ዕርዳታ ወደሚፈልግ ሰው አንድ እርምጃ ጠጋ ማለትን፣ በዚያ ሰው ጫማ ውስጥ ሆኖ የማሰብ ጥበብ ነው» ብለዋል። በመጨረሻም፣ የእያንዳንዱ ሠራተኛ አዎንታዊ አስተዋጽዖ በሌላው ላይ እየተጨመረ ለሚገነባው አገርና ተቋም፣ እርስ በርስ የመተሳሰር እና በርኅራኄ የመተያየት ክህሎትን ማዳበር እንደሚገባ አጽንዖት ተሰጥቶበታል። በተለይም በሕዝብ አገልግሎት (Public Service) ዘርፍ ላይ የተሰማሩ የተቋሙ ባልደረቦች፣ እርስ በርስ ክህሎትን የመጋራትና የመደጋገፍ (የመተናነጽ) ባህልን ይበልጥ ሊያጠነክሩ እንደሚገባ በማሳሰብ መድረኩ ተጠናቋል። ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!! ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/ ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572 ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr ትዊተር:https//@wemezekr ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/

ግንቦት 29/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት "እንገናኝ እንሰናኝ!" የሠራተኞች የሠኞ ንጋት መድረክ በየኹለት ሳምንት የሚቀርበው ሦሥተኛ መድረካችን ሰኞ ሰኔ 1/2018 ዓ.ም ማለዳውን ይካሒዳል። በየኹለት ሳምንት የሚቀርበው ሦሥተኛው የሠራተኞች መወያያ መድረካችን በአጋጣሚ ሰኔና ሰኞ የገጠመበት ነው። ሰኔና ሰኞ በኢትዮጵያ ባህል ውስጥ ሁለት መጥፎ ወይም አስቸጋሪ ነገሮች በአንድ ጊዜ መገጣጠማቸውን የሚገልጽ ተወዳጅ ፈሊጣዊ አነጋገር ነው።  አነጋገሩ በዋናነት ሁለት ትርጉሞች አሉት። ቀጥተኛ ትርጉም፦ ሰኔ፦ በኢትዮጵያ የቀን አቆጣጠር የዓመቱ አስረኛ (10ኛ) ወር ሲሆን፣ የክረምቱ መግቢያና የዝናብ ወቅት ነው። ሰኞ፦ ከእሑድ እረፍት ቀጥሎ ሳምንት የሚጀመርበት የመጀመሪያው ቀን ነው። ዘይቤያዊ ትርጉም፦ አንድ ሰው ችግር ውስጥ እያለ ሌላ ተጨማሪ ፈተና ሲገጥመው «ነገሩ ሰኔና ሰኞ ሆነብኝ» ይባላል።  ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!! ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/ ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572 ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr ትዊተር:https//@wemezekr ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/