CANOPY 2013 2014 2015 2016
Open in Telegram
This channel is for students , parents and Asko school community
Show more2 404
Subscribers
-424 hours
-227 days
-6530 days
Posts Archive
Repost from Addis Ababa Education Bureau
+7
የ2019 የትምህርት ዘመን አጀመማር ስኬታማ እንዲሆን በትኩረት መስራት እንደሚገባ ተገለጸ::
(ነሀሴ 29/2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ጥላዬ ዘውዴ ቢሮው ለአራት ተከታታይ አመታት ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ ላመጣው ውጤት የሱፐርቪዥን አካል ትልቁን ሚና የተጫወተ መሆኑን ገልፀው ይህን የስራ ድል በጀመርነው በጀት ዓመት በተሻለ መንገድ ለመድገም በክፍለ ከተማና በተዋረድ ያሉ የሱፐር ቪዥን አካላት ድጋፍ የራሱ ትልቅ አስተዋፅኦ ያለው መሆኑን አብራርተው፡፡
ሱፐርቫይዘሮች ተቆጥሮ የተሰጣቸዉን ሥራ በውጤት ለማጠናቀቅ መምህሩ ካሪኩለሙና ተማሪው መገናኘታቸውን በማረጋገጥ የመማር ማስተማር ስራውን ስኬታማ የማድረግ እንዲሁም የመጨረሻ ግብ የሆነውን የትምህርት ጥራትን ማስጠበቅ ላይ ኃላፊነት መወጣት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል:: የሚደረጉ የሱፐርቪዥን ስራዎችን በጥራት በመስራት ትክክለኛ መረጃ በማምጣት ፤ በመደገፍ ለሚመለከተው አካል የመረጃ ምንጭ በመሆን መስራት ይገባል ብለዋል::
የዳይሬክቶሬቱ ሱፐር ቪዥን ቡድን መሪ ወ/ሮ ባንቺዓለም ጌታቸው የ2019 የትምህርት ዘመን የቅድመ ዝግጅት ሥራን አስመልክቶ በክፍለ ከተማ ደረጃ በተዘጋጀ ቼክ ሊስት መሰረት የድጋፍና ክትትል ሥራ ሲሰራ መቆየቱን አስታውሰው ትምህርት ቤቶች በቅድመ ዝግጅት ሥራ ማለትም በግብዓት ፣ በመምህር መሟላት ፣ እቅድ ዝግጅትና ለመጀመሪያ ቀን የትምህርት አጀማመር (Day one Class one) ዝግጁ መሆናቸዉ ማረጋገጥ ከሱፐርቪዥን መዋቅሩ መረጋጥ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc
Repost from Addis Ababa Education Bureau
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ጥላዬ ዘውዴ በበኩላቸው ስትራቴጂው ተማሪዎች የመማር ብቃታቸውን አሳድገው በሀገር አቀፉ የ2ኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና ውጤታማ እንዲሆኑ የሚያስችል መርሀግብር መሆኑን ገልጸው ትምህርቱ በክረምት ወቅት እየተሰጠ እንደመሆኑ ተማሪዎች ትርፍ ጊዜያቸውን አላስፈላጊ ቦታ እንዳያሳልፉ የሚያደርግ መሆኑን አብራርተዋል::
የማጠናከሪያ ትምህርቱ በ63 ክላስተር ማዕከላት ከመንግስትና ከግል ትምህርት ቤቶች ለተውጣጡ የ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች እየተሰጠ የሚገኝ ሲሆን 1,420 መምህራን የማጠናከሪያ ትምህርቱን በማስተማር ላይ እንደሚገኙ በውይይቱ ተጠቁሟል።
በመርሀ ግብሩ ከውጤት ማላቂያ ስትራቴጂው ባሻገር የ90 ቀን እና የ2019 ዓ.ም የተማሪ ምዝገባ አፈጻጸም ሂደት ግምገማ ተካሂዷል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc
Repost from Addis Ababa Education Bureau
+7
የ2ኛ ደረጃ ተማሪዎችን ውጤት ለማላቅ በክረምት መርሀግብር እየተሰጠ የሚገኘው የማጠናከሪያ ትምህርት በሚፈለገው ደረጃ ውጤታማ እንዲሆን በቀሪ ቀናት አስፈላጊውን የድጋፍና ክትትል ስራ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ።
(ነሀሴ 8/2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ስትራቴጂክ ካውንስል አባላት ከክፍለ ከተማ ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊዎች እና ከአዳሪ ትምህርት ቤት ርዕሳነ መምህራን ጋር በጋራ በመሆን የ2ኛ ደረጃ ተማሪዎችን የሀገር አቀፍ ፈተና ለማላቅ ተዘጋጅቶ ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኘውን የክረምት የማጠናከሪያ ትምህርት አተገባበርን ተመልክተዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊና የቢሮ ኃላፊ ተወካይ አቶ ሳምሶን መለሰ የ2ኛ ደረጃ ተማሪዎችን የሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት ለማላቅ ታስቦ ተግባራዊ የሆነው ስትራቴጂ አፈጻጸም በየወቅቱ ሲገመገም መቆየቱን አስታውሰው ስትራቴጂው በሚፈለገው ደረጃ ውጤታማ እንዲሆን በቀሪ ቀናት በየክላስተሩ በመገኘት አስፈላጊውን የድጋፍና ክትትል ስራ መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
Repost from Addis Ababa Education Bureau
የመምህርነት የስራ ቅጥር ማስታወቂያ!
(ሀምሌ 21/2018 ዓ.ም) መመዝገቢያ ሊንኮች
1. ለ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች
https://docs.google.com/forms/d/1RRFzFMb2HEoCyRp_ye5E-joooyGYzpAMfEvFBQdbJJs/edit
2. ከቅድመ አንደኛ ደረጃ እስከ 8ኛ ክፍል ላሉ ትምህርት ቤቶች
https://docs.google.com/forms/d/1exSs8OJs3UzYpyzcqQ8e13-JiczbyGR1ohmYFpdHJOY/edit
3. Barnoota Sadarkaa 1ffaan duraa hanga kutaa 8ffaa isa jala jiraniif Bara Barnootaa
https://docs.google.com/forms/d/1UXIAIH736rY4YoENoRNSmNsYkZsOJFrh6o7-G3qz53E/edit
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc
Repost from Addis Ababa Education Bureau
+7
የ2ኛ ደረጃ መልቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት ማላቂያ ስትራቴጂ የክረምት መርሃ ግብር አፈፃፀም ስኬታማ እንዲሆን ሁሉም ባለድርሻ አካላት የሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተገለፀ።
(ሀምሌ 8/2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የ 2ኛ ደረጃ መልቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት ማላቅ አላማው ያደረገ ስትራቴጂ ተቀርፆ ተግባር ላይ መዋሉ የሚታወቅ ሲሆን በክረምት የማጠናከሪያ ትምህርት መርሃ ግብሩ ስኬታማ እንዲሆን ሁሉም አካል በትጋት መስራት እንዳለበት ተገልፃል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ጥላዬ ዘውዴ የክረምት የልዩ ማጠናከሪያ ትምህርቱን አስመልክቶ ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን በሪፓርታቸው ውጤታማ ስራ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል::
አቶ ጥላዬ አያይዘውም በትምህርት አሰጣጥ ሂደቱን በአግባቡ በመምራት ትምህርቱ የሚያመጣውን ለውጥ በማለም በተቀመጠው ልክ ውጤታማ ለማድረግ ብሎም ተማሪዎች ትምህርቱን ወደውት እንዲማሩ ምቹ ሁኔታ በመፍጠር ለተሻለ ውጤት ጥቅም አለው የሚል ግንዛቤ ይዘው እንዲማሩ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ይጠበቃል ብለዋል::
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳምሶን መለሰ በ 2019 በጀት ዓመት በሚደረገው የ 90 ቀናት ሥራዎችውስጥ ትምህርት ለትውልድ ፣ የክረምት ትምህርትና ጎልማሶች ትምህርት ፣ የቤት እድሳት እንዲሁም የደም ዩኒት ማሰባሰብና ማዕድ ማጋራት ላይ በእቅዱ መሰረት የተቀመጠለትን ጊዜ ጠብቆ እየተከናወነ መሆኑን አብራርተው ስራውን አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ ተናግረዋል::
Repost from Addis Ababa Education Bureau
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ጥላዬ ዘውዴ ሰነዱን ባቀረቡበት ወቅት ተማሪዎችና መምህራን ትምህርቱን ሲያጠናቅቁ የእውቅና ሰርተፍኬት እንደሚሰጣቸው የገለፁ ሲሆን ተማሪዎች በዋናነት ለሀገር አቀፍ ፈተና ዝግጁ እንዲሆኑ የሚያደርግ መሆኑን ገልፀዋል::
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc
Repost from Addis Ababa Education Bureau
+7
በሀገር አቀፍ ፈተና የላቀ ውጤት ማስመዝገብ እንዲቻል የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት በተመረጡ ክላስተር ማዕከላት ከሐምሌ 6 ጀምሮ መሰጠት እንደሚጀምር ተገለፀ።
(ሀምሌ 4/2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ከ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ለተመረጡ ቶፕ 30 የ2ኛ ደረጃ ተማሪዎች በክረምት መርሐ ግብር ማጠናከሪያ ትምህርት ለመስጠት በቂ ዝግጅት በማድረግ ሰኞ ሐምሌ 6 በተመረጡ የክላስተር ማዕከላት ትምህርቱ መሰጠት ይጀምራል::
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ክቡር ዶክተር ዘላለም ሙላቱ በከተማ አስተዳደሩ በሀገር አቀፍ ፈተና የላቀ ውጤት ማስመዝገብ እንዲቻል የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርቱ እንደሚሰጥ ገልፀው ፤ ትምህርቱ በሳምንት 5ቀን ለክረምት ወቅት ብቻ በተዘጋጀ ኮንደንስድ ካሪኩለም እንደሚሰጥ ገልፀው በማስተማሪያ ስነዘዴው x ን የማረም ስትራቴጂ ተግባራዊ በማድረግ ተማሪዎች ስህተቶቻቸውን እያረሙ በርካታ ጥያቄዎች የሚሰሩበት እንዲሁም ትርፍ ጊዜያቸውን አልባሌ ቦታ እንዳያውሉ የሚያደርግ መሆኑን አብራርተዋል::
ዶክተር ዘላለም በመርሃ ግብሩ 51,523 ተማሪዎችና 1,800 መምህራን ትምህርቱን ለመስጠት ምዝገባ ማካሄዳቸውን ገልፀው በመርሀ ግብሩ የሚሳተፉ የመንግስት እና የግል ተማሪዎች በተገለፀው ቀን በተመረጡ 63 ክላስተር ማዕከላት በመገኘት ትምህርቱን እንዲከታተሉና ስራው በጥብቅ ዲሲፕሊን እንዲመራ አቅጣጫ አስቀምጠዋል::
Repost from Addis Ababa Education Bureau
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ጥላዬ ዘውዴ ሰነዱን ባቀረቡበት ወቅት ተማሪዎችና መምህራን ትምህርቱን ሲያጠናቅቁ የእውቅና ሰርተፍኬት እንደሚሰጣቸው የገለፁ ሲሆን ተማሪዎች በዋናነት ለሀገር አቀፍ ፈተና ዝግጁ እንዲሆኑ የሚያደርግ መሆኑን ገልፀዋል::
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc
Repost from Addis Ababa Education Bureau
+9
የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ትራንስፎርም ለማድረግ የተገዙ ግብአቶች ለተቋማቱ ተሰራጩ።
(ሰኔ 2/2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ "የትምህርት ግብዓት ለትምህርት ቤቶች ውጤታማ ትራንስፎርሜሽን!" በሚል መሪ ቃል 137 የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ትራንስፎርም ለማድረግ የሚያስችሉ የተለያዩ ግብአቶችን በመግዛት ለተቋማቱ አሰራጨ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊና የዘርፉ አስተባባሪ አቶ ጥላዬ ዘውዴ በመርሀግብሩ ባስተላለፉት መልዕክት ትምህርት ቢሮ በከተማ አስተዳደሩ የሚገኙ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ትራንስፎርም ለማድረግ ባከናወናቸው የተለያዩ ተግባራት እስካሁን 115 ያህሉ ትራንስፎርም ማድረጋቸውን በተቋማቱ በተካሄደ ምዘና መረጋገጡን አስታውሰው ትምህርት ቤቶቹ ግብአት ማሟላታቸው በጫወታ የማስተማር ስነ ዘዴን ተግባራዊ አድርገው ሞዴል እንዲሆኑ የሚያስችል መሆኑን አስገንዝበዋል።
ምክትል ቢሮ ኃላፊው አያይዘውም የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ህጻናቱ ለቀጣይ የትምህርት ዘመናቸው መሰረት የሚይዙበት እንደመሆኑ በዛሬው እለት ግብአት የተሰራጨላቸው ተቋማት ግብአቶቹን ለሚፈለገው አላማ በማዋል ተማሪዎችን ተጠቃሚ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።
Repost from Addis Ababa Education Bureau
+8
ቢሮው የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ወደ ከፍተኛ ደረጃ ትራንስፎርም ለማድረግ እየሰራ መሆኑ ተገለፀ ::
(ግንቦት 30/2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ዘርፈ ብዙና ቀዳማይ ልጅነት ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ትራንስፎርም ለማድረግ በሚያስችል ስታንዳርድ ላይ ስልጠና ሰጥቷል ::
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ጥላዬ ዘውዴ ሀገርን በመገንባት ጉዞ የትምህርት ስራ ዋንኛው መሆኑን ገልፀው የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ለተማሪዎች ምቹ ማድረግ ተማሪዎች በቀጣይ ሕይወታቸው ምቹ ሁኔታን የመፍጠር ስነልቦና እንዲያዳብሩ ያግዛል ብለዋል ::
በከተማ አስተዳደሩ ከ 240 በላይ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መኖራቸውን ያስታወሱት አቶ ጥላዬ ትምህርት ቤቶቹን ምቹ ለማድረግ ከትምህርት ቤት ርእሳነ መምህራንና ከሚመለከታቸው ጋር በመሆን የሀገርን መሰረት በማነፅ ረገድ የመምህራን ድርሻ ትልቅ በመሆኑ ከስልጠናው የማጨበጠውን እውቀት በተግባር ላይ ማዋል ከመምህራን ይጠበቃል ሲሉ ተናግረዋል :: አያይዘውም በ 4ኛ ሩብ ዓመት ምዘና ይህንን ስልጠና የወሰዱ ትምህርት ቤቶች ወደ ከፍተኛ ደረጃ ትራንስፎርም እንዲሆኑ ይጠበቃል ብለዋል ::
የዘርፈ ብዙና ቀዳማይ ልጅነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ በላይነሽ የሻው በበኩላቸው የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በጨዋታ የማስተማር ስነዘዴን በመተግበር ከሥጋት ነፃ እና ምቹ የመማሪያ አካባቢና ክፍሎች እንዲሁም አስፈላጊ ግብአቶች ማሟላት መሰረታዊና ግድ መሆኑን አስታውሰው በትምህርት ቤቶች ትራንስፎርሜሽን ምዘና መሰረት መካከለኛ ደረጃ ላይ ያሉትን ወደ ከፍተኛ ደረጃ
ክቡራትና ክቡራን የተማሪዎቻችን ወላጆች እና አሳዳጊዎች፤
ባለንበት በዚህ ፈጣን ዘመን፣ አብዛኞቻችን ወላጆች የልጆቻችንን ስኬት የምንለካው በትምህርት ውጤታቸው፣ በሚያስመዘግቡት የክፍል ደረጃ እና ወደፊት በሚሰማሩበት የሥራ መስክ ላይ ብቻ ሆኗል። ልጆቻችን ምርጥ ትምህርት ቤት እንዲገቡ፣ በሳይንስና በሂሳብ አንደኛ እንዲሆኑ ቀንና ሌሊት እንለፋለን፣ እንደክማለን፣ ትልቅ ዋጋ እንከፍላለን። ይሄ በጣም የሚደነቅ የወላጅነት ፍቅር ነው። ነገር ግን፣ አንድ ትልቅ እውነት እንዘንጋ፦ ትልቁና እውነተኛው የህይወት ትምህርት ቤት የሚጀምረው ከክፍል ውጭ፣ በእናንተና በልጆቻችሁ ቤት ውስጥ ነው።
"ቤት — የመጀመሪያውና ዘላለማዊው የህይወት ላብራቶሪ ነው።"
በትምህርት ቤት ጥሩ ውጤት ያመጣ ልጅ ነገ ዶክተር፣ ኢንጂነር ወይም ታዋቂ ሳይንቲስት ሊሆን ይችላል። ነገር ግን ያ የተማረው ሰው መልካም ባል፣ ታማኝ ጓደኛ፣ አዛኝ ጎረቤት እና ሀገር ወዳድ ዜጋ የሚሆነው ከክፍል ውስጥ የሚያገኘው ትምህርት ብቻ ሳይሆን፣ ከእናንተ ከወላጆቹ በሚያገኘው ‘የማይታይ የቤት ውስጥ ሥርዓተ-ትምህርት’ (Hidden Curriculum) አማካኝነትም ጭምር ነው!
ይህ ማለት ምን ማለት መሰላችሁ? እኛ በትምህርት ቤት ዕውቀትን እንሰጣለን፣ እናንተ ግን በቤት ውስጥ ልብንና ባህሪን ትቀርጻላችሁ። እያንዳንዱ ወላጅ ከትምህርት ቤት ግድግዳዎች ባሻገር ለልጁ ሊያስተምራቸው የሚገቡ 10 ዋና ዋና የህይወት መርሆዎች አሉ። እነዚህን መርሆዎች ዛሬ አብረን እንያቸው፡-
1. ውድቀትን የመቋቋም አቅምና ጥንካሬ
በትምህርት ቤት መውደቅ ማለት ዝቅተኛ ውጤት ማምጣት ሊሆን ይችላል፤ በህይወት ውስጥ ግን መውደቅ የማይቀር ጉዞ ነው። ለልጆቻችን ስህተት መስራት የውድቀት ማብቂያ ሳይሆን የመማሪያ መንገድ መሆኑን ማስተማር አለብን። ስለሆነም:-
• አንድ ነገር ሲከብዳቸውና ሲሳሳቱ ወዲያውኑ ጣልቃ ገብተን ከመስራት ይልቅ፣ ራሳቸው ደጋግመው እንዲሞክሩ እናበረታታቸው።
• ህይወት ሁልጊዜ አልጋ በአልጋ እንዳልሆነችና በገጠመኞቻቸው ሁሉ ጥንካሬን እንዲያዳብሩ ማስተማር፣ የነገን ጠንካራ ማንነት የመገንቢያ ቁልፍ ነው።
2. ስሜትን መረዳትና ርህራሄ (Empathy)
ከፍተኛ የአካዳሚክ ዕውቀት ኖሮት የሰዎችን ስሜት የማይረዳ እና የማይራራ ትውልድ ለዓለም የሚጨምረው እሴት የለም። ስለሆነም:-
• ልጆቻችን ሰዎችን በዘራቸው፣ በገቢያቸው ወይም በማህበራዊ ደረጃቸው ሳይሆን በሰብአዊነታቸው ብቻ እንዲያከብሩ በተግባር እናሳያቸው።
• የራሳቸውን ስሜት በነጻነት እንዲገልጹ፣ የሌሎችንም ስሜት በጥንቃቄ እንዲያዳምጡ ስናደርጋቸው ማህበራዊ ግንኙነታቸው የተሳካ ይሆናል።
3. ራስን መምራትና ለድርጊታቸው ኃላፊነት መውሰድ
ትምህርት ቤት ደወልና የጊዜ ሰሌዳ አለው፤ እውነተኛው ህይወት ግን የራስን መንገድ በራስ መምራትን ይጠይቃል። እናም:-
• ልጆች ለሰሩት ስህተት ሌሎችን ወይም ሁኔታዎችን ከመውቀስ ወጥተው፣ የራሳቸውን ኃላፊነት እንዲወስዱ ማስተማር አለብን።
• ከቴክኖሎጂ ሱስ ወጥተው፣ ለጨዋታ፣ ለጥናትና ለቤተሰብ ያላቸውን ጊዜ በስርዓት እንዲያደራጁ መርዳት የወደፊት ህይወታቸውን የተቃና ያደርገዋል።
4. የዲጂታል ዓለም ግንዛቤ እና ሚዛናዊነት
በአሁኑ ዘመን ልጆቻችን ከእውነተኛው ዓለም ይልቅ በስክሪን ላይ የሚያሳልፉት ጊዜ እየበለጠ መጥቷል። የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ በልጆቻችን ስነ-ልቦና ላይ ትልቅ ጥላ እየጣለ ይገኛል። ስለሆነም:-
• በኢንተርኔት ላይ የሚታዩ ነገሮች ሁሉ እውነት እንዳልሆኑ፣ አብዛኛው ነገር የተቀነባበረ መሆኑን ማስተማር አለብን። የሚመለከቱትን ነገር በጭፍን ከመቀበል ይልቅ በምክንያታዊነት እንዲመረምሩ እናግዛቸው።
• ስልኮችን ዘግቶ በአካል የመገናኘትን፣ አብሮ የመጫወትን እና ከተፈጥሮ ጋር የመገናኘትን ውበት በቤታችን ውስጥ በተግባር እናሳያቸው። ቴክኖሎጂ ሰዎችን ማገናኛ እንጂ ቤተሰብን ማራቂያ መሆን የለበትም።
5. ጠያቂና መርማሪ አእምሮን ማሳደግ
ትምህርት ቤት ብዙ ጊዜ መደበኛ የሆኑ ጥያቄዎችንና መልሶቻቸውን በቃል መያዝ ላይ ያተኩራል። ህይወት ግን ከተዘጋጁ መልሶች ውጭ ናት። ስለዚህ:-
• ልጆች በቤት ውስጥ "ለምን?" ብለው እንዲጠይቁ እናበረታታቸው። የፈለጉትን ጥያቄ በነጻነት የሚጠይቁ ልጆች በነገው ህይወታቸው አዲስ ነገር ፈጣሪና ችግር ፈቺ (Innovators) እንጂ የሌሎችን ሃሳብ ብቻ የሚከተሉ ተላላኪዎች አይሆኑም።
• በትምህርት ቤት ማስታወሻዎች ብቻ ሳይገደቡ በቤት ውስጥ የንባብ ልምድ እንዲያዳብሩ መጻሕፍትን ማቅረብ የወላጅ ትልቅ ስጦታ ነው።
6. ጤናማ ማንነት እና ራስን መቀበል
በአሁኑ ጊዜ ወጣቶች በውጫዊ ገጽታ፣ በፋሽን ወይም በሌሎች ሰዎች "የሐሰት ስኬት" ራሳቸውን በመለካት ለጭንቀትና ለስነ-ልቦና ቀውስ እየተጋለጡ ነው። ስለሆነም:-
• የልጆቻችን ዋጋና ክብር የሚለካው ባላቸው ቁስ ወይም ሰዎች ስለነሱ በሚናገሩት ነገር ሳይሆን በውስጥ ማንነታቸውና በሰብአዊ እሴታቸው መሆኑን ደጋግመን ልንነግራቸው ይገባል።
• አእምሮን ከክፉ ሐሳቦች መጠበቅና አካልን መንከባከብ የራስን ህይወት የመውደድ መገለጫ መሆኑን ከልጅነት ጀምሮ እናስርጽባቸው።
7. የትዕግስት ጥበብ እና ፍላጎትን ማዘግየት
በአሁኑ የቴክኖሎጂ ዘመን ሁሉም ነገር "ፈጣን" ሆኗል። ምግብ፣ መረጃ፣ መልእክት ሁሉም በአንድ ክሊክ ይደርሳል። ይህ "ፈጣን እርካታ" (Instant Gratification) ልጆች በህይወት ውስጥ ትዕግስትን እንዲያጡና ጥረትና ጊዜን የሚጠይቁ ነገሮች ላይ በቀላሉ ተስፋ እንዲቆርጡ እያደረጋቸው ነው። ስለሆነም:-
• እውነተኛ ስኬት፣ ጥልቅ እውቀት እና ጠንካራ ህይወት ጊዜና ትዕግስትን እንደሚጠይቁ ለልጆቻችን ማስረዳት አለብን። አንድን ነገር በፈለጉበት ቅጽበት ወዲያውኑ ከማግኘት ይልቅ፣ ጠብቀውና ለፍተው ሲያገኙት የሚኖረውን ደስታ እንዲለማመዱ ማድረግ ያስፈልጋል።
9. የማህበረሰብ ተቆርቋሪነት እና የማገልገል ባህል
ራስ ወዳድነት በነገሰበት በዚህ ዘመን፣ ልጆች ስለ ራሳቸው ምቾት ብቻ እያሰቡ እንዳያድጉ ማድረግ የወላጅ ትልቅ ኃላፊነት ነው። ስለሆነም:-
• ልጆቻችን ከተደላደለ ህይወታቸው ወጣ ብለው የተቸገሩትን እንዲያዩ፣ አቅመ-ደካሞችን እንዲረዱ እና በበጎ ፈቃድ ስራዎች ላይ እንዲሳተፉ እናድርግ።
• እውነተኛ ደስታ ከማግኘት ይልቅ በመስጠት ውስጥ እንደሚገኝ በተግባር ሲማሩ፣ በዓለም ላይ በጎ ተፅዕኖ መፍጠር የሚችሉ እውነተኛ መሪዎች ይሆናሉ።
📌 #የማጠቃለያ_መልእክት
የተከበራችሁ ወላጆች፤
ወላጅነት ማለት ልጆችን መመገብ፣ ማልበስና ጥሩ ትምህርት ቤት መላክ ብቻ አይደለም። ወላጅነት ማለት ለአለም የሚጠቅም፣ በስነ-ምግባር የታነጸ፣ ራሱንና ማህበረሰቡን የሚለውጥ "ሙሉ ሰው" መቅረፅ ነው።
አንድ ነገር ሁልጊዜ እናስታውስ፡ ልጆቻችን ከቃላቶቻችን ይልቅ ድርጊቶቻችንን ያያሉ። እነሱ የእኛን ንግግር ሳይሆን የእኛን ህይወ
Repost from Addis Ababa Education Bureau
+6
በከተማ አስተዳደሩ ለትምህርት ተቋማት ተከታታይነት ያለው ድጋፍና ክትትል መደረጉ የመማር ማስተማር ስራው ስኬታማ እንዲሆን እያበረከተው ያለው ድርሻ ትልቅ መሆኑ ተገለጸ፡፡
(ግንቦት 13/2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አጠቃላይ ትምህርት ሱፐርቪዥን ዳይሬክቶሬት በትምህርት ተቋማት ላይ ተከታታይነት ያለው ድጋፍና ክትትልን በማጠናከር የትምህርት ተቋማት የሚሰጡትን ትምህርት ውጤታማነት ለማረጋገጥ እንዲቻል በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ገልጻል::
የአዲስ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊና የሱፐርቪዥን ዘርፍ አስተባባሪ አቶ ጥላዬ ዘውዴ የሱፐርቪዥን መዋቅሩ በመማር ማስተማር ስራ ውስጥ ውጤታማነትን ለማረጋገጥ እየሰራቸዉ የሚገኙ ስራዎች ተጨባጭ ውጤት እያስዘገቡ እንደሚገኙ ገልጸው ፤ ለዚህ መጎልበት የባለሙያዎች አስተዋፅኦና አቅም ብሎም ድጋፍ ትልቅ ድርሻ ይጫወታል ብለዋል፡፡
አያይዘውም የድጋፍና ክትትል ስራዎች ሲከናወኑ አላማዉን በአግባቡ በመረዳት በቢሮው የተቀየሱ ስትራቴጂዎች ያመጡትን ለውጥ የሚያሳይ መረጃ መኖሩን ማረጋገጥ ብሎም በቀጣይ በሚደረጉ ከተማ አቀፍና ሀገር አቀፍ ፈተናዎች በውጤታማነት እንዲጠናቀቁ የመሪነት ሚናን መወጣት ይገባል ብለዋል፡፡
