cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Addise_Media_Network™(AMN)❤️

ይህ ታማኝ የሁሉም ኢትየጵያን መረጃ ነዉ። በዚህ ሚዲያ ስለኢትዮጵያ ህዝብ አንድነት፣ ሰላምና ደህንነት፣ ልማትና ዲሞክራሲ፣ ታሪካዊ፣ ባህላዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ይወሩበታል። አስተያየት ወይም ጥቆማ ካለ አድርሱን™ ለአስተያየትዎ በስልክ ቁጥር 0960819654 0968374238 ስለምትከታተሉንእናመሠግናለን። https://t.me/Absenya_News

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
172Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

🔝ጎንደር! "ጎንደር"ማለት "ጉንደ ሀገር" ከሚለው የግዕዝ ቃል የተገኘ ሲሆን ትርጓሜውም "የሃገር ግንድ፣ የሀገር መሰረት፣ ርዕሰ ሃገር ወይም የሀገር ራስ ማለት ነው። ይኼውም ኖህ ከጥፋት ውሐ በኋላ የተቀመጠበት በእንተላ ፣በአይዋርካ፣ በሽሌ፣ በአይከል፣ በኩል አድርጎ ጎንደር ላይ ብዙ ዘመን ፈጣሪውን እያመሰገነ እየቀደሰ የኖረባትና የተቀበረባት ቦታ በመሇኗ የሃገር መጀመሪያ ዋና ግንድ ተባለች። እንዲያውም በ950 ዓ.ዓ ኖህ ሲሞት መቃብሩ ላይ ምንጭ ፈልቆ በርካታ ሰዎችን ይፈውስ ነበር። ከዚያም ለኖህ መታሠቢያ ይሆን ዘንድ አምላክ በቤተመንግስት አሳቦ የኖህ የመቃብር ሐውልት እንዲታነጽ ፈቀደ። ይህም በኋለኛው ዘመን በንጉሥ ፋሲለደስ የታነጸው የፋሲል ግንብ ነው። ዐፄ ፋሲለደስም በ1629 ዓ.ም በመሀንዲስ አባ ገብረክርስቶስ መሪነት የእደ ጥበብ ባለሙያዎችን በማሰባሰብ ከኖህ መቃብር ላይ የቤተመንግሥቱን ታላቅ መሰረት ጥለውታል። ግንባታውም በ7 አመት ውስጥ ተጠናቀቀ። ከዚህ በኋላ ዐፄ ፋሲል በቀሐ ወንዝ አጠገብ "ማንኪት" የሚባለውን ህንጻ በ17ሺህ ካሬ ሜትር ስፋት ባለው ግቢ መሀል ላይ 50 ሜትር በ25 ሜትር ስፋትና 2 ሜትር ጥልቀት ያለው የባህረ ጥምቀት ገንዳ አስገነቡ፡፡ ከቀሃ ወንዝ በተቆፈረ ቦይ ውሐ ተጠልፎ እንዲገባ አደረጉ። ከዛን ጊዜ ጀምሮ ገንዳው ለጥምቀት በዓል መጠመቂያነት የሚያገለግል ሲሆን፣ ዐፄ ፋሲል ባሰሩት ጥንታዊ ህንፃ ደግሞ የታቦታቱ ማደሪያ ሆኖ ያገለግላል። መዋኛ ገንዳው በባእሉ ሰሞን የባንዲራ መቀነት ይታጠቃል፡፡ ጎንደር የመንግሥት ከተማ ከሆነችበት እስከ ጎንደር ዘመን ማክተሚያ ፈፃሜ መንግሥት አፄ ተክለ ጊዮርጊስ ድረስ 18 ነገሥታት የነገሱ ሲሆን እነዚህም አብዛኛዎቹ አብያተ ክርስቲያናትን አሠርተዋል፡፡ 44 የሚባሉት አብያተ ክርስቲያናት ጎንደር የመንግሥት ከተማ ከመሆኗ አስቀድሞ የተተከሉበትን ጨምሮ እስከ ፈፃሜ መንግሥት ተክለ ጊዮርጊስ ድረስ የተተከሉትን ብቻ ሲሆን ቁጥራቸውም 44 ነው፡፡ ከዚያ ወዲህ ከዘመነ መሣፍንት እስከ አሁን የተተከሉ በርካታ አብያተ ክርስቲያናት ቢኖሩም ከ44ቱ የሚቆጠሩ አይደሉም፡፡ በአጠቃላይ አርባአራቱ ታቦታተ በጎንደር ዘመን በጎንደር ከተማና አካባቢው የሚገኙና የነበሩ 44 አብያተ ክርስቲያናት ጥቅል ስም ነው፡፡ ይህም ማለት አሁን ባለው የጎንደር ከተማ ክልል እና ዙሪያውን በሚገኙ አዋሳኝ የገጠር ቀበሌዎች ለምሳሌ፣ ጠዳ፣ ፈንጠር፣ ብላጅግ፣ ደፈጫ እና በመሳሰሉት ቦታዎች የሚገኙ አጠቃላይ የአድባራት ቁጥር ነው፡፡ #የአርባ_አራቱ_ታቦታት_ስም_ዝርዝር፦ 1-አዘዞ ተ/ሃይማኖት 2-ፊት አቦ 3-ፊት ሚካኤል 4-አደባባይ ኢየሱስ 5-ግምጃ ቤት ማርያም 6-እልፍኝ ጊዮርጊስ 7-መ/መ/መድኃኔዓለም 8-አቡን ቤት ገብርኤል 9-ፋሲለደስ 10-አባ እንጦንስ 11-ጠዳ እግዚአብሔር አብ 12-አርባዕቱ እንስሳ 13-ቀሐ ኢየሱስ 14-አበራ ጊዮርጊስ 15-አደባባይ ተ/ሃይማኖት 16-ደብረ ብርሃን ሥላሴ 17-ዳረገንዳ ኤዎስጣቴዎስ 18-አጣጣሚ ሚካኤል 19-ጐንደር ሩፋኤል- 20-ደፈጫ ኪዳነ ምህረት 21-ቅ.ዮሐንስ መጥምቅ 22-ጐንደር ልደታ ማርያም 23-ሠለስቱ ምዕት 24-ጎንደር በአታ ለማርያም 25-ወ/ነጐድጓድ ዮሐንስ 26-ጐንደር ቂርቆስ 27-ጐንደር ሐዋርያት(ጴጥሮስ ወጳውሎስ ) 28-ፈንጠር ልደታ 29-ሰሖር ማርያም 30-ወራንገብ ጊዮርጊስ 31-ምንዝሮ ተ/ሃይማኖት 32-ደ/ፀሐይ ቊስቋም 33-ደ/ምጥማቅ ማርያም 34-አባ ሳሙኤል 35-ጐንደሮች ማርያም 36-ጐንደሮች ጊዮርጊስ 37-አባ ጃሌ ተ/ሃይማኖት 38-ዐቢየ እግዚእ.ኪ/ምህረት 39-ብላጅግ ሚካኤል 40-አሮጌ ልደታ 41-ጫጭቁና ማርያም 42-ጋና ዮሐንስ 43-አይራ ሚካኤል 44-ዳሞት ጊዮርጊስ ( ታደለ ጥበቡ )
Show all...
👋ሰላም Mequannent ይህ ከታች የላክንልዎ የእርሶ መለያ ቁጥር ነው ይህን ለ 25 ሰዎች በመላክ እና Start እንዲሉ በመጋበዝ የ 500 ብር የሞባይል ካርድ ተሸላሚ ይሁኑ። 👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/AwashBankRefferalBot?start=r0072691435 💞 መልካም እድል 💞 💎Awash Bank💎
Show all...
Awash Bank

🌟በዚህ Bot 25 ሰዉ ወደ ቦቱ በመጋበዝ የ500 ብር ከፈለጋችሁ ሞባይል ካርድ ካልፈለጋችሁ ደግሞ በባንካችን ተሸላሚ መሆን ይችላሉ። 💞መልካም እድል💞 💎Awash Bank💎

#DebreTaborUniversity የደብረ ታቦር ዩንቨርሲቲ ተመራቂ ያልሆኑ ሁሉም ተማሪዎች የመግቢያ ቀን ጥር 3 እና 4 ተብሏል❗️ ፨ጥሪው አንደኛ ዓመት ተማሪዎችንም ይጨምራል!!! #2012 ሁለተኛ ሴሚስተር ላይ አፓረንት የወጣቹህ ተማሪዎችን ጥሪው አይመለከትም ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት 🔽 @amharictutorialclass ጥቆማ/ቅሬታ/ጥያቄ ለማቅረብ ⤵️ @amharictutorialclassbot
Show all...
"ጥቃት ሲፈጸምብን የተዋጋነው መሬት ፍለጋ ሳይሆን የተቀማነውን ማንነት ለማስመለስ ነው" አቶ አገኘሁ ተሻገር የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አገኘሁ ተሻገር የአማራ ብዙኀን መገናኛ ድርጅት ሠራተኞች ህግ በማስከበር ሂደቱ መረጃ በትክክልና በታማዓኒነት ለኢትዮጵያ ሕዝብ መረጃ አድርሰዋል ብለዋል። ጦርነቱ የፍትህና የመገፋት ጦርነት ነበር፤ ተገፍተንም ስለነበር ድል አድርገናል። አሁን ዓላማ አለን በርካታ ሥራአጥ ወጣት አለን፣ የልማት ሥራ እንሰራለን። ጦርነቱ ለችግር ደራሽነቱን፣ ጀግንነቱንም ያሳየበት ነው፣ ጋዜጠኞች መረጃ በትክክል በማድረስ ሚናቸውንም ተወጥተዋል ብለዋል፡፡ ርዕሰ መስተዳደሩም በሁሉም ግምባሮች ለዘገቡ የአማራ ብዙሃን መገናኛ ድርጅትና የአማራ ፖሊስ ኮሚሽን ጋዜጠኞች ሽልማት አበርክተዋል፡፡ [አብመድ]
Show all...
የህወሓት አመራሮች የሚገኙበትን ለጠቆመ 10 ሚልዮን ብር ሽልማት ማዘጋጁትን የመከላከያ ሠራዊት አስታወቀ ! ሌተናል ጀነራል አስራት ዴኔሮ ዛሬ እንደተናገሩት የህወሓት አመራሮችን በአጭር ጊዜ በቁጥጥር ስር ለማዋል የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ ሽልማቱ መዘጋጀቱን አስታውቀዋል። በዚህም የመከላከያ ሠራዊት የህወሓት አመራሮች ያሉበትን ቦታ ለጠቆመ የ10 ሚሊዮን ብር ሽልማት እንደሚሰጥ አመልክተዋል፡፡ #etv @tikvahethiopiaBOT
Show all...
እርግጠኛ ነኝ መቸም ከዚህ በሇላ የወልቃይት - ጠገዴ-ዳንሻ-ጠለምት-ሁመራ የራያ አለማጣ አማራዎችን ወደ ትግራይ ይካለሉ እሚል አይኖርም ካላም እሱ ሰው ሳይሆን ሰይጣን ነው። ይህ የእኔው አስተያየት ነው። ''''መኳንንት ጋሻው አስናቀ''''
Show all...