cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ባርኮን CHANNEL

ኤፌ 1:3 " በክርስቶስ በሰማያዊ ስፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ የባረከን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ።"

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
602Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

ሀሳብ ከሸፈተ ሀሳቤ ሸፍቶ ከመንፈስህ ሌላ አስቦ በራሱ ጋጋታ ጩሄት ልቤን በቀንበር ይዞ ሀሳቤ በሌላ ታስሮ ሌላውም አካሌ ተከትሎት በሮ ስጠራ የማልሰማው ሆኜ በሀሳቤ ቋጠሮ የማውጣት ማውረዴ ብዛት ሁለንተናዬን ከቶት በማሠሮ ሀሳብ ከሸፈተ ሌላው ይሆናል ምርኮኛ ያለ አዕምሮ የታቹ አይንቀሳቀስምና ካለሰማይ ውጭ ላለማሰብ ሀሳቤ እኔነቴን ወደ ራሱ ስስብ Earphone ሰክቼ መዝሙር ባዳምጥ መጽሐፍ ገልጬ አይኔን በቃልህ ብጠምድ ሀሳቤ ሸፍቶ እምብ ስለኝ ከህልውና ድንገት ሰርቆ ስያወጣኝ ፀሎቴን ጀመርኩ እንድህ ስል ግዛው ሀሳቤን ፤ ውስጠቴን በቃልህ ውረስ ነብሴ ወታ እንዳትበር ይዘህ በመንፈስህ ውስጠቴን አረስርስ ውስጥ ተቀምጬ ፤ ቃል ውስጥ ተኝቼ አላስብ ውጭ ሀሳቤን አስገዝተህ ለራስህ ውረሰኝ አልውጣ ከእጅህ ሀሳብ ከሸፈቴ ሌላው ምርኮ ነው አብሮ በራር ግዛውና አሳድረኝ ፤ ከጅያለው መሰንበት ከህልውና ከጠረንህ ሙሉ ሀሳቤን ጠቅልዬ በቤትህ ዙርያ ልደር ሀሳብ ከሸፈቴ ሌለላው አደጋ ጣይ ነው ባንደ የምያፈራርስ አዕምሮን ሰርቆ እግሮቼን ከቤትህ አርቆ የማይመልስ አደራህን እንግድህ አንተ ቀድመህ ሀሳቤን ውረስ በቃልህ ጨምቀህ ውስጠቴን በመንፈስህ አረስርስ ሁሌንቴናዬን በቃልህ አድስ ....... በእኔ በወንድማችሁ እንባክ መልካም የክርስቶስ እናም የኛም ልደት ! @Blessedus
Show all...
Ameeeennnn
Show all...
Amen amen
Show all...
" ሕፃን ተወልዶልናልና፥ ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና፤ አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል፤ ስሙም ድንቅ መካር፥ ኃያል አምላክ፥ የዘላለም አባት፥ የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል።" (ትንቢተ ኢሳይያስ 9:6) 🎅 መልካም የክርስቶስ በምድር በአካል መገለጥ መታሰብያ ይሁንላችሁ። 🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄 ⛄️⛄️⛄️⛄️⛄️⛄️⛄️⛄️⛄️ @Blessedus
Show all...
.......ትንቢተ ኢሳይያስ ምዕ. 11 1፤ ከእሴይ ግንድ በትር ይወጣል፥ ከሥሩም ቍጥቋጥ ያፈራል። 2፤ የእግዚአብሔር መንፈስ፥ የጥበብና የማስተዋል መንፈስ፥ የምክርና የኃይል መንፈስ፥ የእውቀትና እግዚአብሔርን የመፍራት መንፈስ ያርፍበታል። 3፤ እግዚአብሔርን በመፍራት ደስታውን ያያል። ዓይኑም እንደምታይ አይፈርድም፥ ጆሮውም እንደምትሰማ አይበይንም፤ 4፤ ነገር ግን ለድሆች በጽድቅ ይፈርዳል፥ ለምድርም የዋሆች በቅንነት ይበይናል፤ በአፉም በትር ምድርን ይመታል፥ በከንፈሩም እስትንፋስ ክፉዎችን ይገድላል። 5፤ የወገቡ መታጠቂያ ጽድቅ፥ የጎኑም መቀነት ታማኝነት ይሆናል። 6፤ ተኵላ ከበግ ጠቦት ጋር ይቀመጣል፥ ነብርም ከፍየል ጠቦት ጋር ይተኛል፤ ጥጃና የአንበሳ ደቦል ፍሪዳም በአንድነት ያርፋሉ፤ ታናሽም ልጅ ይመራቸዋል። 7፤ ላምና ድብ አብረው ይሰማራሉ፥ ግልገሎቻቸውም በአንድነት ያርፋሉ፤ አንበሳም እንደ በሬ ገለባ ይበላል። 8 የሚጠባውም ሕፃን በእባብ ጕድጓድ ላይ ይጫወታል፥ ጡት የጣለውም ሕፃን በእፉኝት ቤት ላይ እጁን ይጭናል። 9 በተቀደሰው ተራራዬ ሁሉ ላይ አይጐዱም አያጠፉምም፤ ውኃ ባሕርን እንደሚከድን ምድር እግዚአብሔርን በማወቅ ትሞላለችና። 10 በዚያም ቀን እንዲህ ይሆናል፤ ለአሕዛብ ምልክት ሊሆን የቆመውን የእሴይን ሥር አሕዛብ ይፈልጉታል፤ ማረፊያውም የተከበረ ይሆናል። @Blessedus @Blessedus
Show all...
" Yea, and all that will live godly in Christ Jesus .........." (2 Timothy 3: 12) " For bodily exercise profiteth little: but godliness is profitable unto all things, having promise of the life that now is, and of that which is to come." (1 Timothy 4: 8) Be godly.......... " ነገር ግን ለዚህ ዓለም ከሚመችና የአሮጊቶችን ሴቶች ጨዋታ ከሚመስለው ተረት ራቅ። እግዚአብሔርን ለመምሰል ግን ራስህን አስለምድ።" (1ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 4:7) " ሰውነትን ለሥጋዊ ነገር ማስለመድ ለጥቂት ይጠቅማልና፤ እግዚአብሔርን መምሰል ግን የአሁንና የሚመጣው ሕይወት ተስፋ ስላለው፥ ለነገር ሁሉ ይጠቅማል።" (1ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 4:8) እግዚአብሔርን ለመምሰል እራሳችሁን አስለምዱ ! ልምከራችሁ:- ሰዎች ስሰድቧችሁ -ጉንጫችሁን አቅልታችሁ 😊 ፈገግ 😁 ብላችሁ እለፉ። ሞኞች ሳትሆኑ ልክ እንደ እግዚአብሔር ገረ ለመሆን ተበረታቱ። godly ሁኑ.......! አለም ሞኝንና ገርን ለይቶ አያውቀውም ግን እናንተ ገር በመሆናችሁ ባለ አክልል ናችሁ። ከመጸለይና ከመጾም ያለፈ ነው ቅባት ለዚህም አካላችሁን በየወኻት አዘጋጁ።👍 ማንም ላይ እጃችሁ አይነሳ ለመምታት ማለቴ ነው ፤ ለመጸለይ ከሆነ ይቻላል። እጃችሁን ሰው ላይ ሳይሆን ለሰውና ፤ እግዚአብሔርን ለማምለክ ስትሉ ብቻ ዘርጉ።🤚 ክብራችሁን አትፈልጉ ፤ ስያዋርዷችሁ ውስጣቹ አይድማ በሳቅ ተፍለቅለቁ። -ለሰው ስታደርጉ ክብር ደሞዛችሁ ሳይሆን ቀርቶ ውርደትን ስያከናንቧችሁ ፤ አትዋረዱላቸው ፤ ይልቁን ደስታችሁ እጥፍ ይሁን። አየሱሰ ገር ነበር ፤ ሞኝ አልነበረም። ልክ እንደ እየሱስ ለመሆን እራሳችሁን አስለምዱ ፤ ይሄ ካልሆነ ስትቀቡ ተናካሽ ውሻ ይመስል ህዝባችሁን በደም ታጨማልቃላችሁ። 💪ፈርጠም ያለ ጡንቻችሁ ፤ ቸርነትን ማድረግ ይሁን። . .. . . . . . ብርሃነ ልደቱ 😊 የቸርነት ትምህርት የጀመረበት ! Be godly* @Blessedus
Show all...
Be Devout Person ያለመረበሽ አናም ያለመሬበሽ በእርጋታ ፤ በጸሎትና በቃል ቆዩ ከዛ አርፍ Pastors, Prophets, Evangelists, Teachers, Apostels ብቻ ሳትሆኑ የመንግስቱ ውበትና ወራሽ ትሆናላችሁ። @Blessedus
Show all...
መንፈሳዊውን አለም በሀይል ለመገናኘት ሌላ ምትሀት የለም ፤ ስለቱ ጥማት ነው። ብዙ ስትጠሙ ብዙ ትጠጣላችሁ ፤ በትንሽ አትረኩም ፤ ተመጣጣኝ የህይወት ውሃ ወንዝ ያሻቿል። " ከበዓሉም በታላቁ በኋለኛው ቀን ኢየሱስ ቆሞ። ማንም የተጠማ ቢኖር ወደ እኔ ይምጣና ይጠጣ።" (የዮሐንስ ወንጌል 7:37) እንድትቀበሉ ጥማት ይለቀቅባችሁ .....!! @Blessedus
Show all...
ጠለቅ ያለ የመንፈሳዊው አለም ርሃብ ይመጣባቿል
Show all...
ኢየሱስ
Show all...