☦ኦርቶዶክስ:የዘላለም:ቤቴ☦
☦️እመን:እንጂ፡አትፍራ ምስጉነው:በክፉዎች:ምክር:ያልሄደ:በዋዘኞችም:ወንበር:ያልተቀመጠ። ኦርቶዶክስ:የዘላለም:ቤቴ:በመንፈሳዊ:ሕይወታችን:እንድንበረታ:የሚያግዙ:ትምህርቶች፣መዝሙሮች፣ጸሎቶች:እንዲሁም:የተለያዩ:መንፈሳዊ:ጉባኤዎች:ሲዘጋጁ:የሚነገርበትና:የሚለቀቅበት:መንፈሳዊ:channel:ነው። @orthodox30 @orthodox30 @orthodox30
Show more297Subscribers
No data24 hours
-27 days
No data30 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
†
[ ተዋሕዶ ፍጽምት የቅዱሳን ሃይማኖት ]
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
[ አንድ አካል አንድ ባሕርይ ነው እንጂ ! ]
--------------------------------------------------
" ከሦስቱ አካላት አንዱ አካል ከሰማይ መውረዱን ፤ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ነፍስና ሥጋን ነሥቶ ሰው መሆኑን ፤ እግዚአብሔር ቃል መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእርሷ ተወልዶ መገለጡን ፤ በተዋሕዶ ሰው የሆነ አምላክ ሆኖ በሰዎች መካከል መመላለሱን አምናለሁ፡፡
አንዱ አምላክ ነው ፥ አንዱ ዕሩቅ ብእሲ ነው አልልም፡፡ እግዚአብሔር ቃል ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከነሣው ሥጋው ጋር አንድ አካል አንድ ባሕርይ ነው እንጂ !
ከእግዚአብሔር የተወለደው ከድንግል የተወለደው ይኸው አንዱ ነው ። አንድ ሲሆንም ይታመማል ፤ አይታመምም፡፡ በሥጋው ይታመማል ፤ ሕማማችንንም ገንዘብ ያደርጋል ፤ በመለኮቱ ሕማማችንን ያርቃል፡፡ በሞቱም ሞታችንን ያጠፋል ፤ ለእኛ ለአገልጋዮቹ ድኅነትን የሰጠን እርሱ ነው፡፡ ለአመኑበትም ትንሣኤን ገለጠላቸው፡፡ የዘለዓለም ሕይወትን በጌትነቱ በሚያወርሳት በመንግሥተ ሰማያት ትሰጥ ዘንድ ያላት ተድላ ነፍስንም ሰጣቸው፡፡"
[ አቡሊዲስ ]
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፤ ወለወላዲቱ ድንግል ፤ ወለመስቀሉ ክቡር። አሜን።
† † †
💖 🕊 💖
Repost from ማህበረ ጻድቃን ዘኢትዮጵያ️/️mahiber tsadkan
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
ታላቅ የንግስ ጉዞ
መጋቢት 4_5 ምድረ ከብድ እና ዝቋላ አቦ መጋቢት 8_12 ግሸን ማርያም
ዘወትር እሁድ
ፃድቃኔ ማርያም ዋጋ =700
ኩክየለሽ ማርያም =550
ሰሚነሽ ኪዳነምህረት =550
ዘብር ቅ/ገብርኤል 2 ቀን ዋጋ =1200
ትኬት ባንክ 14665803 absina
1000515659351 cbe
አዘጋጅ :- ማህበረ ጻድቃን
+251973171717
+251954939595
+251923552424
🙏መድሀኒያለም ይባርካቹ ነገ መድሀኒያለም ነው ይቅርታ ፍቅር ሰላም ሁሉም የታየበት አዳም እና ሄዋን የዳኑበት እኛ ያዳም ልጆች ነፃ የወጣንበት 🙏🙏🙏🙏መልካም በአል። 27
Repost from ሰብሕዎ ለአምላክነ
"መጻጉዕ" ማለት ምን ማለት ነው?Anonymous voting
- አልጋ
- መዳን
- በሽተኛ
- መጠመቅ
"ሁል ጊዜ የምትጾም ከሆነ በትዕቢት ራስህን ወደ ላይ አታውጣ፣ ከዚህ የተነሣ ራስህን ከፍ አድርገህ የምትመለከት ከሆነ ግን ሥጋ ብትበላ ይሻላል፡፡ ለአንድ ሰው ራሱን በትዕቢት ከመንፋትና ራሱን ከማክበር ሥጋ ቢበላ ይሻለዋልና፡፡” ብለው አባ ኤስድሮስ የትሕትናን ጥቅም አብራርተዋል፡፡
"ፍሬ የያዘ ዛፍ (ቅርንጫፍ) ዝቅ ይላል" ይላሉ አበው፡፡ አንድ አባት "ካልበደለና ጻድቅ ነኝ ከሚል ሰው ይልቅ የበደለና ኃጢአተኛነቱን የሚያምን ሰው ይሻለኛል" ብሎ ስለ ትሕትና ገልጿል፡፡
ጾማችንን የትሕትና ያድርግልን!
ዲ/ን ሕሊና በለጠ ዘኆኅተ ብርሃን
ኦርቶዶክስ የዘላለም ቤቴ ።።።
"ሁል ጊዜ የምትጾም ከሆነ በትዕቢት ራስህን ወደ ላይ አታውጣ፣ ከዚህ የተነሣ ራስህን ከፍ አድርገህ የምትመለከት ከሆነ ግን ሥጋ ብትበላ ይሻላል፡፡ ለአንድ ሰው ራሱን በትዕቢት ከመንፋትና ራሱን ከማክበር ሥጋ ቢበላ ይሻለዋልና፡፡” ብለው አባ ኤስድሮስ የትሕትናን ጥቅም አብራርተዋል፡፡
"ፍሬ የያዘ ዛፍ (ቅርንጫፍ) ዝቅ ይላል" ይላሉ አበው፡፡ አንድ አባት "ካልበደለና ጻድቅ ነኝ ከሚል ሰው ይልቅ የበደለና ኃጢአተኛነቱን የሚያምን ሰው ይሻለኛል" ብሎ ስለ ትሕትና ገልጿል፡፡
ጾማችንን የትሕትና ያድርግልን!
ዲ/ን ሕሊና በለጠ ዘኆኅተ ብርሃን