መድብለ ጥበብ
🕵️♂️ አንብበን የተማርንባቸውን ፅሁፎች ብዙዎች እንዲማሩበት 'ና የተለያዩ የጥበብ ስራዎች ምናጋራበት ቻናል ነው።@habtewman ፨ንባብ ያልታከለበት ስልጣኔ ግልብ ያደርጋል፨ ✍️ደራሲ በአሉ ግርማ "ያላነበበ ጭንቅላት እና ጨጓራ አንድ ናቸው:: ሁለቱም ባዶ ሲሆኑ አሲድ ያመነጯሉ ✍መጋቢ ሐዲስ እሸቱ share and Join us @habtewman @habtewman
Show more202Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
ጉርሻ🧣
በተቻለህ አቅም ምንም ነገር ስታደርግ በግማሽ ልብ ሆነህ እያመነታህ መሆን የለበትም፤ ስታመነታ ብዙ ነገር ያመልጥሀል፣ ሰዎች ባንተ እርግጠኛ መሆን አይችሉም።
ልበሙሉ ከሆንክ ግን ስህተት እንኳን ብትሰራ በሌላ ልበሙሉ ተግባር ስህተትህን ታስተካክላለህ። የሚያመነታ ሰው ሁለት ቦታ ስለሚረግጥ ከአንዱም ሳይሆን ከመንገድ ይቀራል።
መልካም ቀን ተመኘንላችሁ😍😍
Show all...
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
ዛፍ የደረቀ ቅጠል ከላዩ ላይ ሲወድቅ🍂 አይከፋም ምክንያቱም ሌላ አዲስና ለምለም🌿 ቅጠል እንደሚያወጣ ያውቃል።
በህይወታችሁ ስላጣችሁት ነገር አትዘኑ! ለተሻለው ነገር ቦታ እየለቀቀ ስለሆነ በደስታ😀 ሸኙት።
#ሳስበው የሄደው ነገር እንኳን ሄደ ያስብላል።
አንድ ሰው በ22 አመቱ ተመረቀ ነገር ግን ጥሩ ስራ ሳይሰራ 5 አመት ጠበቀ ። አንድ ሰው በ25 አመቱ ዋና ስራ አስኪያጅ ሆነ ፣ በ50 አመቱ ሞተ ። ሌላው በ50 አመቱ ዋና ስራ አስኪያጅ ሲሆን 90 አመት ኖሯል ። አንድ ሰው እስካሁን ያላገባ ነው ፣ ከትምህርት ቤቱ ጓደኛ የሆነ ሰው ግን አያት ሆኗል ። #ኦባማ በ55 አመቱ ጡረታ ወጣ ትራምፕ በ70 አመቱ ጀመረ ፡፡
በዚህ አለም ላይ ሁሉም ሰው የሚሰራው የጊዜ ክልሉን መሰረት አድርጎ ነው ። በዙሪያህ ያሉ ሰዎች ከፊትህ ያሉ ሊመስሉ ይችላሉ አንዳንዶች ደግሞ ከኋላህ ያሉ ሊመስሉ ይችላሉ ። ሁሉም ግን የራሱን ሩጫ በራሱ ጊዜ እየሮጠ ነው ። እነሱ በራሳቸው የጊዜ ክልል ውስጥ ናቸው ፣ አንተ ደግሞ በራስህ ውስጥ ነህ ። አልዘገየህም አልቀደምክም ፡፡ ባለጊዜ ተጠቀም ፡፡
ምንጭ : ምርጥ ፅሁፎች
"ናፈቅሺኝ"
እንዴት እንደመጣሁ እንዳትጠይቂኝ ለምን
ስለምትናፍቂኝ።
አውቀዋለሁኛ
አንድ የበለደሽ ሰው ናፍቀሺኛል ቢልሽ
ላንቺ ፌዝ ነው ሚመስልሽ።
ግን ናፍቀሺኛል አዎ በድያለሁ በግፍ
ደግሞም ናፍቀሺኛል በእጥፍ።
ማርያምን የምሬን በዝቷል መናፈቄ
የትም እገኛለሁ የትም እስቃለሁ
ግን ያለቅሳቃል ሳቄ።
ብራመድ ባገሩ ብከንፍ እንኳን ብበር
ተከፍቶ አያለሁ ቆለፍኩት ያልኩት በር።
ቀን የከረመችኩት ሌት በምን ከፈትኩት።
በለሊትሽ መጣው አለሜን ስላጣው
ከትናንት የባሰ እንደማጣሽ ሳስብ
በደሌን አየሁት እጥፍ መውደድ ሲስብ።
አንቺዬዋ ውዴ የበደለ ሁሉ አይናፍቅም እንዴ።
ማቀፍ እንኳን ባልችል ምህረት ባለምንም
አትሳቂብኝ እንጂ
ግጥሙን እያነበብኩ ናፈቅሺኝ አሁንም።
ፀሀዮን ከተትኳት አይንሽን ለማየት
ከቤት እየወጣው
የበደለ አይኔን እንዳታይኝ ብዬ
በጨለማ መጣው ።
ደረስኩኝ ከደጅሽ መፍራቴ በነነ
እሰይ አገኘሁሽ ናፍቆቴ ሰው ሆነ።
ስደርስም አልሳምሺኝ
አጃኢብ ሰው መሆን
ሳጠፋ ጊዜ ነው ጭራሽ የናፈቅሺኝ።
አጥፍቻለው አዎ አጥፍቻለው አዎ
መውደዴን ቀብሬ
አትሳቂብኝ እንጂ ልክ ስበድልሽ
ጨመረብኝ ፍቅሬ።
"ናፈቅሺኝ🤔
✍️የኤልያስ ሽታሁን ሼር
@habtewman