cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Etsegenet Haileloul Eshaherget

Advertising posts
256
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

"ደስ የሚል ቤተሰብ አለው። ብዙ ስኬቶች አስመዝግቧል። የሚገርሙ ስራዎች ይሰራ ነበር። ብዙ እቅድ ነበረው። ነገር ግን በሚያሳዝን ሁኔታ እራሱን አጥፍቶ ተገኘ። " የሚል ፅሁፍ አነበብኩ ፤ ግን አልደነገጥኩም፤ አልተገረምኩም አላዘንኩምም። የሰው ልጅ ሲጨንቀውና ግራ ሲገባው ለጓደኞቹ ደውሎ፣ ለቤተሰብ አሳውቆ፣ የሀይማኖት ሰዎችን አማክሮ፤ ወደ ሀኪም ሄዶ እና የስነልቦና ሀኪም አማክሮ መፍትሄ ሲያጣ። ሰዎችን እንደማናገር የሚከብድ ነገር ባይኖርም "ተጨናንቄያለሁ እርዱኝ" ማለት ቢከብድም ግን ለብቻ ሲሆን በብቸኝነት ሲሆን የበለጠ ከባድ ነው ብሎ "የሰው ያለ ፤ ያቅም ያለ" እያለ ቸል ከተባለ የህይወት ትርጉሙ የታለ?። አሜሪካ ራስ የማጥፋት ሀሳብ ያላቸውና የጨነቃቸው ሰዎች የሚደውሉበት 24 ሰአት የሚሰራ ነፃ የስልክ መስመር 988 አለ። ሁሉም ሀገር ላይ እንደዚህ አይነት አገልግሎት ቢኖር ጥሩ ነበር። ቢያንስ የሰው ልጅ ከመሞቱ በፊት መናገር የሚፈልገውን ነገር በሙሉ ተናግሮ ይሞታል። ምንም አይነት የኢኮኖሚ ደረጃ ላይ ብንሆን፣ ምንም አይነት ቤተሰብ ቢኖረን፣ ምንም አይነት ስራ ላይ ብንሰማራ አእምሮ ደህና ካልሆነ ሁሉም ነገር እያለን ምንም እንደሌለን ነን። አእምሮአችን ህይወት ትርጉም አልባ እንደሆነ እየነገረን እንዴት እንኖራለን?። በከባድ ሁኔታ ውስጥ ሆነን ነገሮች መልካም እንደሚሆኑ ተስፋ ማድረግ ሲያቅተን፣ ሁልጊዜም ተስፋ ካጣን፣ የስነ ልቦና ህክምና ውስጥ ተስፋ ካላገኘን፣ በቤተሰብና በጓደኛ እገዛ ተስፋ የለሾች ስንሆን፤ በእምነት ውስጥ ያለን ተስፋ ሲከሽፍ እና በጊዜ ላይ ያለን ተስፋ እንደጉም ሲተን ምን እናድርግ?። እገዛ ፈልገን ከመጠየቅ ወደኋላ ሳንል፤ አቤት የሚል ስናጣ፣ ሳይረፍድ ቶሎ እገዛ ለማግኘት የጣርነው ሁሉ በዜሮ ሲባዛ፤ ብዙ የሸሸግናቸው የአእምሮ ጤና ጉዳዮች ብቅ ብቅ ሲሉብን፤ ከህፃንነታችን ጀምሮ የስነ ልቦና ጠባሳ የተዉብን ጥቃቶች ደርሶ ቁስላቸው ሲያገረሽብን፤ ለብቻችን ለመቋቋም ሞክረንም ሲከብደን፤ እገዛና ድጋፍን ከፈጣሪም ከፍጡርም ጠይቀን ዝም ስንባል.... ለራሳችን ብለን እንዳንጠነክር በራሳችን ላይ ያደረብን መሪር ጥላቻ አልፈቅድ ሲለን፤ ለምንወዳቸው ሰዎች ስንል የመኖር ፍላጎት እንዳናመርት የምንገፋው በእነሱ ሲሆን፤ በደዌ ተመተን ካልተኛን በስተቀር የልብ ስብራታችን እና የመንፈስ መታወካችን ከህመም እንደማይቆጠር ሲገባን፤ በቁም ሞተን ስንታይ ምንም ያልመሰለው ማህበረሰብ ነፍሳችን ከስጋችን የተለየች ግዜ አልቅሶ አፈር እንደሚያለብሰን ስናውቅ ታዲያ ምን እናድርግ?????! እራሳችን ላይ እርምጃ ከመውሰድ ውጪ እኮ ሌላ ምን መፍትሄ አለ?! እራስን ማጥፋት አይደለም መሸነፍ.......... እንደውም ይሄን አለም ማሸነፍ ነው።
Show all...
Photo unavailable
በስተመጨረሻም እንዲህ ሆነ ......... አላደርግም ብዬ የማስበውን ክፉ ነገር ሁሉ ሳደርግ፤ አልወድቅበትም ካልኩበት ጥግጋት ሁሉ ስወድቅ፤ ብርቱ ነኝ ብዬ ባልኩበት ነገር ሁሉ ስደክም ተገኘሁ። ራሴን ታግዬ ማሸነፍ አልቻልኩም። ልቤ ውስጥ ያለው ጨለማ ደጅ ካለው ጨለማ እየበለጠ ሄዷል። አንተ ፊት እንባ ይቀድመኛል። መናገር አልችልም።
Show all...
Photo unavailable
My heart is now in so much pain. My tears are falling like pouring rain. I can no longer sleep a full night. I can no longer fight. We are no longer together. What happened to forever? No one can save me from the dark's might. This time there will be no light. I'm not going to fight. There's no reason to. When I did fight, it was for you. I know I never did show how I felt. Just believe me, every time I saw you, my heart would melt. Just know... I loved you then, I love you still. I promise I always will. I don't know why we had to say our goodbyes... but I'll love you till the day I die. My heart is broken, but I still have hope. One day we might get back together. Maybe next time will be forever.
Show all...
Photo unavailable
መንገድ የጀመረ የሸፈተ ልብን በተማፅኖ ምልጃ ላያስቀሩት ነገር ህመሙ ቢከብድም ምን አማራጭ አለ ከመሸኘት በቀር?! ያ'ንተም ልብ እንዲያ ነው የሸፈተ ተጓዥ መንገድ የጀመረ ብኩን ስደተኛ እኔም እንደዛ ነኝ ህመሙ ያቃተኝ አማራጭ አጥቼ ልብህን የሸኘው ቀሪ በሽተኛ፡፡ መንገድህ ህመሜ መሸፈትህ ፀፀት የህሊና ቁስል ህመሜ ድህነትህ ስብራቴ ተስፋ ላንተ መልካም እድል፡፡ በበዛው ፍቅሬ ላይ በአንድ የታጠረው የምርጫዬ ግድብ ለነጠፈው ፍቅርህ እልፍ አማራጭ ሆኖ የፍላጎትህ ግብ ይኸው ባንተ ቀዬ የገባዎት ሰማይ የማጠልቅ ጀንበር ፀሀይን አትሞ በኔ ቀዬ ላይ ግን እንደመሸ ቀረ ላይነጋ ጨልሞ!
Show all...
Photo unavailable
የደከመ እግሬን መንገድ ገትቼ እንደማሳርፈው፤ ለደከመች ነፍሴም ፋታ መስጠት ብችል ብዬ እመኛለሁ።
Show all...
Photo unavailable
አምላኬ የምጥለው የለኝ፡ የማነሳው የለኝ ፡ጓዳዬን ታውቃለህ፤ ለምን ከዚህ በላይ፡ ስሰቃይ እያየህ ፡ዝ'ም ትለኛለህ??
Show all...
Photo unavailable
ወደ እኔ ያመጣህ መንገድ፣ መልሶ ከእኔ ከወሰደህ፤ እንግዲህ ምን አደርጋለሁ? እሺ ደህና ሁን፤ መልካሙን ሁሉ እመኝልሃለሁ።
Show all...
Photo unavailable
ሕይወቴ በቃል እንደሚሸመደድ ሀረግ ስለሆነብህ፤ በአንድ ጀምበር አውቀኸኝ ስለጨረስህ፤ ስለነገዬ ከገመትከው አንዱም ስላልተሳሳትህ፤ በዚህም ተሰላችተህ ስለተውከኝ፤ አርቀህም ስለገፋኸኝ፥ ገፍተህም ስለሰበርከኝ..... ይቅርታ። አንድአንድ ቀን እኔም ከእንቅልፌ ስነሳ እኔን ሆኜ በመንቃቴ እሰለቻለሁ። አንተስ ባይተዋር ነህና ፈታኸኝ። አታገኘኝም ብለህ አንዱ ዳርቻ ሕይወትህን ቀጠልህ - እሰይ እንኳንም አበጀህ። ድሮም ሰው ሌላ ሰውን እንጂ እራሱን አይተውም። እኔ ግን ከዚህ ተነስቼ የት ድረስ ብሮጥ እራሴን አመልጠው ይሆን?
Show all...
Photo unavailable
አያችሁኝ አይደል ካፈር ተማስዬ፤ በጉጬ ሲራመድ አያባሬ እንባዬ፤ በቁዘማ ሲያልፍ በሀዘን ጊዜዬ። ወድጄዋለሁኝ  ይሄንን ስቃየን፤ ከሰው ተለይቼ የብቻ ውሎዬን፣ የብቻ ኑሮዬን፣ የብቻ ህይወቴን፣ የብቻ ማንባቴን፣ የብቻ ለቅሶዬን፣ ወድጄዋለሁኝ፤ እንዳትቀሰቅሱኝ አለሁ አንዳትሉኝ፤ ምንም አትጠይቁኝ ስሜንም አትጥሩኝ፤ ምነው ቄስ ቢጠራኝ ብገባ ካፈሩ! ዳግም ባልሰማቸው ወፎች ሲዘምሩ፤ አቤት ባልላቸው ወዳጆች ሲጣሩ፤ መቼም ላይከፈት በተዘጋ በሩ።
Show all...
Photo unavailable
ደከመኝ አምላኬ... ለረጋጭ ተመልካች ምስኪን ልቤን ማስጣት፤ በነፍሴ ቴአትር ላይ ህልም ላየሁበት ተስፋ ከፍሎ መውጣት፤ ሰለቸኝ ጌታዬ... ላልኖርኩበት ዘመን እድሜዬን መገፍገፍ፤ ያዘመመን እውነት በእውቀት መደገፍ፤ በቃኝ! ወይ ከህይወት ፃፈኝ ወይ ከህይወት አውጣኝ! ገፍታሪ ሸልመህ መውደቂያ አታሳጣኝ!!
Show all...