ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
前往频道在 Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
显示更多2 923
订阅者
+3224 小时
+3727 天
+36630 天
帖子存档
አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ 305ኛ ጎቤ መልኬ ኮር 76ኛ ክፋለ ጦር ለወራት ሲያሰለጥናቸዉ የቆዩትን የአማራ የቁርጥ ቀን ልጆቹን በደማቁ አስመርቋል!!
ነሐሴ 16/12/2018 ዓ.ም
የአማራን ሕዝብ ሕልውና የማስከበር ትግል ለማጠናከር ለተከታታይ ወራት የተሰጠውን ወታደራዊ ስልጠና ሲከታተሉ የቆዩ ሰልጣኞች በዛሬው ዕለት በድምቀት ተመርቀዋል።
በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የአፋብን ምክትል ኃብት አፈላላጊ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ በለጠ አዱኛ፣ የ305ኛ ጎቤ መልኬ ኮር ዋና ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ ኤሊያስ ድንቁ፣አርበኛ ጌታቸዉ የሽወንድም የ305ኛ ኮር አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ፣ አርበኛ ናቃቸዉ ጌትነት የ305ኛ ኮር ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ ፣ አርበኛ አበባዉ አማረ የ305ኛ ኮር ም/ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ ፣አርበኛ ተስፋየ ማስረሻ 305ኛ ኮር 76ኛ ክፋለ ጦር ዋና አዛዥ ፣ እንዲሁም ሌሎች የዕዝ፣ የኮር እና የክፍለ ጦር ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
ተመራቂዎቹ ላለፉት 3 ተከታታይ ወራት ያጋጠሟቸውን ሁለገብ ችግሮችና ፈተናዎች በጽናት በመጋፈጥ የጀመሩትን ጠንካራ ወታደራዊና ስልታዊ ስልጠና በስኬት አጠናቀዋል። ሰልጣኞቹ በሥነ-ሥርዓቱ ላይ ባሳዩት ዝግጁነት ለአማራ ሕዝብ ህልውናና መብት መከበር በሚደረገው ትግል ውስጥ እራሳቸውን ሙሉ በሙሉ በማዘጋጀት ግንባር ቀደም ሚናቸውን ለመወጣት ቃል ገብተዋል።
የእዝ እና የኮር አመራሮቹ በበኩላቸው ይህ ፕሮግራም ከጎንደር አንድነት ማግስት መሆኑ ልዩ ልዩ ስሜት የሚሰጥ መሆኑ እንዳለ ሆኖ ሰልጣኞች ያሳዩትን ጽናትና ቁርጠኝነት አድንቀው፣ የተገኘው ወታደራዊ ክህሎት ለትግሉ አዲስ ጉልበትና ጥንካሬ እንደሚሆን እምነታቸውን ገልጸዋል ሲል መረጃውን ያደረሰን የኮሩ ህዝብ ግንኙነት ነው።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ !
አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ ሜጀር ጀኔራል ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር ነበልባሉ 23ኛ ክፍለ ጦር በጠላት ላይ ከፍተኛ ኪሳራ አድረሰ።
ነሐሴ 16/2018 ዓ.ም
የአገዛዙ ኃይል ነሐሴ 15/2018 ዓ.ም በሜጀር ጀኔራል ውባተ አባተ ፩ ኛ ኮር ሁሉም ክፍለ ጦሮች ቀጣና እንቅስቃሴ ለማድረግ ሞክሮ በርካታ ኃይሉን እንዲያጣ አስገድዶታል ።
በመሆኑም ሜጀር ጀኔራል ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር ነበልባሉ 23ኛ ክፍለ ጦር በተሳተፈባቸው አውደ ውጊያዎች ከፍተኛ ምት ያረፈበት ጠላት በዛሬው ዕለት ነሐሴ 16/2018 ዓ.ም ቁስለኛውን እና አስከሬኑን ለመውሰድ ከወረታ ከተማ አንድ ሲኖ ትራክ መኪና እና አንድ አንቡላንስ ይዞ ወደ መነጉዘር እንቀስቃሴ ቢያደርግም የክፍለ ጦሩ ተወርዋሪ ሻለቃ የደፈጣ ጥቃት በመክፈት ከፍተኛ ምት አሳርፈውበት ሙትና እና ከከባድ እስከ ቀላል ቁስለኛውን ታቅፎ ባለበት እንዲቆም ተገዷል።
በሌላኛው አውደ ውጊያ ሀገረሰላም እና የማሪያም እሳር በሰፈረባቸው የጠላት ቀጣና እንዳይንቀሳቀስ በመግታት የእርስ በእርስ ትስስር ሙሉ በሙሉ እንዲቋረጥ በማድረግ የጠላት ዕዝና ሰንሰለትን ማሽመድመድ ተችሏል።
በትናትናው ዕለት ሜጀር ጀኔራል ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር ነበልባሉ 23ኛ ክፍለ ጦር ከጧቱ 12:00 ሰዓት እስከ 1:00 ሰዓት በዘለቀው አውደ ውጊያ ከአባ ኪሮስ እስከ መነጉዘ የክፍለ ጦሩ ቃኝና መሐንዲስ፣ 3ኛ ሻለቃ እና የክፍለ ጦር ስታፍ ሸኸቲ ተራራ ፣ አባኪሮስ ፣ ቀሰር ተራራ ፣ እንድርያስ ተራራ ፣ ባንዲገዝ ፣ጮሪት እና መነጉዘር ላይ ድል ሲቀዳጅ በርካታ ኃይሉ ከጥቅም ውጭ ሆኗል።በሌላኛው አውደ ውጊያ ደግም 2ኛ ሻለቃ ዓለም በር ከተማ በመግባት ከፍተኛ ትንቅንቅ በማድረግ በጠላት ኃይል ላይ ድል መቀዳጀት መቻሉን አስታውሶ መረጃውን ያደረሰን የክፍለ ጦሩ ህዝብ ግነኙነት ነው።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
🚨 ሰበር ዜና - ስቦ ማስከዳት! 🚨
በአማኑኤል ከተማ መሽጎ ከነበረው የብልፅግና ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት ውስጥ አንድ ሻምበል አመራርና አባላት ትጥቃቸውን ይዘው ፋኖን ተቀላቀሉ። ከ6ኛ ዕዝ 10ኛ ክ/ጦር 2ኛ ሬጅመንት 1ኛ ሻምበል በመውጣት፣ የአማራን ህዝብ ህልውና ለማስከበር ቆርጦ የተነሳውን የአፋብን|ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ 109ኛ ኮር 99ኛ ክ/ጦር ኢንጅነር ክበር ተመስገን ሻለቃን ተቀላቅለዋል፦
✅ ሃምሳ አለቃ መለሰ፦ ከወር በፊት ሻለቃ መሪ የነበር አሁን በአማራነቱ ሻምበል መሪ የተደረገ 1 ስናይፐር፣ 1 ጥቁር ክላሽ እና 1 የመገናኛ አይኮም ሬዲዮ
✅ ምክትል አስር አለቃ ቶሎሳ አቦ፦ የጋንታ መሪ 1 ጥቁር ክላሽ
✅ አብርሃም ጋሻው፦ 1 ጥቁር ክላሽ
✅ መኳንት ምስጌ፦ 1 ጥቁር ክላሽ በመያዝ ከብልፅግናው ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት በመውጣት ፋኖን ተቀላቅለዋል።
የድል ጉዞው ይቀጥላል!
ድል ለአፋብን! 💪🦅
አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!
📅 ነሐሴ 16/2018 ዓ.ም
#BreakingNews #Ethiopia #Fano #Amhara #ሰበርዜና #ጎጃም #አማኑኤል #ነፃነት
የአማራ እናት ምን ያህል የተባረከች ነች! ሊቅ ነው፤ ፖለቲካ ይችላል። ዉጊያን ከጥበብ ጋር እንዴት እና እንዴት ማድረግ እንዳለበት ጠንቅቆ ያውቃል። ምሁር ነው፣ ጀግናም ነው። አብይ አህመድ እና መሰሎቹን እንደ ህፃናት 'ዳዲ' ያስሂዳል።
የአማራ ልጅ ፋኖ አርበኛም ነው፣ ጠበቃም ጭምር እንጂ ምኑ ተነግሮ ያልቃል! ብዙዎቹ ይፈሩታል፤ ደግሞም ፍራቻቸውን አይተው ይተቹታል። የሴራ ፖለቲካ እንዴት እና እንዴት እንደሆነ ጠንቅቆ ያውቃል።
የአማራ ልጅ ፋኖ ከጀግናው በላይ ዘለቀ ሰፈር የተወለደ፣ የአብይ አህመድ የክኒን መድኃኒት፣ የአፋብን ህዝብ ግኑኝነት ዋና መምሪአርበኛ አስርስ ማረ! #Dave #Amhara
ሁሌም አዲስ መርጃዎችን ለማግኘት የፊስቡክ አካውንታችን ይወዳጁን!! https://www.facebook.com/share/1cTMCWWYSh/
የጅግናው የአርበኛ ዝናው በቀለ አዲሱ ፒጁን ይወዳጁት!! https://www.facebook.com/share/1DjX3RQc7X/
የጅግናው የአርበኛ ዝናው በቀለ አዲሱ ፒጁን ይወዳጁት!! https://www.facebook.com/share/1DjX3RQc7X/
ሁሌም አዲስ መርጃዎችን ለማግኘት የፊስቡክ አካውንታችን ይወዳጁን!! https://www.facebook.com/share/1cTMCWWYSh/
የአንሻ ሰይድ 4ኛ ዕዝ በጠላት ላይ ድል ተቀዳጀ!!!
የዘረ ፈጁ አገዛዝ ሰራዊት እና ገዳ ኮማዶ ፣ኤርፔሎላ፣የጃልሞሳ ሸኔ አንሻ ሰይድ 4ኛ ዕዝ ሲፋለም መዋሉና በዚህም አውደ ውጊያ ሞገደኛው የአንሻ ሰይድ ዕዝ ሰራዊት ከፍተኛ ወታደራዊ ብልጫ በመውሰድ የወራሪውን ሰራዊት ሲያራግፉት ውለዋል።
ዘሬ ከጠዋቱ 11:00ሰዓት መነሻውን ከአንገር ጉትን በማድረግ ወደ ማርያም ሰፈር ለመግባት የቋመጠው ይህ ገዳይ ሃይል ቀድሞ ቦታዎችን በአራት ክፍለጦሮች በመያዝ ጠዋት የጀመረው አውደውጊያ እስከ ምሸት 11:00ሰዓት የቆየው ተጋድሎ ደቢቦ እምትባል አከባቢ ጀምሮ እስከ ወሎ ሰፈር ድርስ
አይቀጡ ቅጣት ሲቀጣ ወደኋላ በመመለስ በከባባድ መሳርያዎች ሽፋን አስክሬኑንና ቁስለኛውን በፓትሮል ወደ አንገር ጉትን በማመላለስ ቀሪው ሃይል ወደኋላ በመውጣትና ተጨማሪ ሃይል በመስገባት አዶዴ ከተማ ሙሉ በሙሉ ቤቶችን በማቃጠልና ስለታማ መሳርያ የታጠቀ የቄሮ ቡድን ቤት ለቤት እየዞረ መሸሽ ያልቻሉትን ነፍሰጡር እናቶችን ፣አቅመ ደካሞችን በአሰቃቂ ሁኔታ እየገደለ ይገኛል።
ይህ በእድህ በሆሩ ጉዱሩ ዞን አቤ ደጎሮ ወረዳ በታፈረ አለሙ ሳተናው ክ/ጦር እና ጌጤ ግርማ መብረቅ ክ/ጦር
በተደረጉ ልዩ ኦፕሬሺን ቱሉጋና ከተማን በቁጥጥር ስር ማዋል ተችሏል።
በዚህም ተጋድሎዎች የተገኙ ምሩኮዎች
👉ከ50 በላይ ይህ ገዳይ ሃይል
የተደመሰሰ
👉36ጥቁር ክላሺ
👉12 የኮማዶ ጥርጥር ክላሺ
👉አራት መገናኛ ሬድዮ
👉እና ተተኳሾችን ገቢ ማድረግ ችለናል።
ግፍ የወለደን:ግፈኞችን የምቀጣ የአንሻ
ሰይድ ወድሞች ነን‼️
አፋብን አንሻ ሰይድ 4ኛ ዕዝ ህ/ግንኙነት መምሪያ
ነሐሴ 15/2018ዓም
የአፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ በመንዝና ግሸ አውራጃ በክምርድንጋይ ክላስተር ሰፊ ህዝባዊ ውይይት ሲያካሂድ፤ ሚኒልክ ክ/ጦር በባንዳ ላይ እርምጃ ወስዷል!
ነሃሴ 15/2018 ዓ.ም
በክምርድንጋይ ክላስተር በተካሔደው ህዝባዊ መድረክ የአፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ ፣ የኮር ፣ የአፄ ምኒልክ ክፍለ ጦር እና የክላስተር አመራሮች በተገኙበት ወቅታዊ የትግሉን ቁመና በተመለከተ ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ሰፊ ውይይት ሲካሔድ በወቅታዊ ፖለቲካዊ እና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ ለህዝቡ ማስረዳትና ትግሉ ያለውን ሕዝባዊነት ማጠናከርን ያለመ ውይይት ተካሂዷል።
በውይይቱ ወቅትም የዕዙ ከፍተኛ አመራሮች እንደገለፁት የብልጽግና ስርዐት የውድቀት ጫፍ ላይ እንደሚገኝ ገልፀዋል። ለዚህ ደግሞ ህዝባችን ስርአቱን እምቢኝ ከማለት ባለፈ በሁሉም መንገድ ድርጅታችን አፋብንን መደገፍ መቻሉና አደረጃጀት በማጠናከር በተደራጀ መንገድ መታገል መቻሉ አንዱ አቅም ነው ብለዋል።
በመድረኩም ህዝባዊ አስተዳደሩ በምን መንገድ ህዝቡን እየመራ እንደሚገኝ፣የፍትህ አሰጣጥ ሂደቶች እና አሰራሮች በሰፊው ተዳሰዋል። ህዝቡም ትግሉ የራሱ መሆኑንና ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ህዝባዊ አስተዳደሩም ይበልጥ እንዲጠናከርና አደረጃጀቱ እየሰፋ እንዲሄድ በመድረኩ ተሳታፊዎች ተጠይቋል።
ይህ በኢንዲህ እንዳለ የአፄ ምኒልክ ክፍለጦር 1ኛ ሻለቃ ቃኝወች በትላንትናው ዕለት ዘመሮ ከተማ ድረስ ዘልቀው በመግባት አራጋው ተፈራ የተባለውን ቀንደኛ የሚኒሻ አመራር ላይ እርምጃ መውሰዱን ክፍለ ጦሩ ገልጿል።
አቶ አራጋው ተፈራ በተደጋጋሚ ሕዝብን በማጉላላትና መሠል በሆኑ ፀረ ሕዝብ ድርጊቱ ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ ቢሠጠውም ከጥፋት ድርጊቱ አልመለስ በማለቱ ወታደራዊ እርምጃ ተወስዶበታል ሲል ኮሩ በመረጃው ገልጿል።
" ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ የህዝብ ግንኙነት መምሪያ
የአብይ አህመድ ስርዓት የመጨረሻ ሸንፈቱ የፊስቡክ ፒጅ በመዝጋት ነው። ወድ አማራዊያም አዲሱ የፊስቡክ ፒጃችን ይወዳጁን!!
https://www.facebook.com/share/1Df23VVTrd/
አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ ሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር በጣላት ላይ ከፍተኛ ኪሳራ ያደረ አውደ ውጊያ አደረገ❗
ነሐሴ 15/2018 ዓ.ም
አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ የሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ 1ኛ ኮር አሃድ የሆኑት:-
➛ሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ተወርዋሪ ክ/ጦር ጉና ክፍለ ጦር (መቅደላ ብርጌድ፣አንዳቤት ብርጌድ፣ጉና ክፍለ ጦር ቃኝና መሐንዲስ ፣የሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር ቃኝና መሐንዲስ ) በተሳተፉበት የማህደረ ማርያም አውደ ውጊያ ( መተረይ፣ ናዳ፣ ዳዋ፣ ማሕደረ ማርያም፣ እማ ወተት ጊዎርጊስ እና ዳዋ መድኃኒዓለም ላይ ከንጋት ) ከንጋት 11:30 የተጀመረው አውደ ውጊያ እስከ ቀኑ 08:00 ሰዓት የቀጠለ ሲሆን ውጊያ የተደረገባቸው ቦታዎችም በጠላት ላይ ከፍተኛ የሆነ ኪሳራ የደረሰ ሲሆን ቁጥሩ ያልታወቀ ሙትና ቁስለኛውን ይዞ ሄዷል።
➛ጉና ክፍለ ጦር/ገብረ መስቀል ብርጌድ ሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ተወርዋሪ ክ/ጦር ከደብረ ታቦር ወርቄን-ገና መጫወቻ፣ ከጋሳኝ በደንጊል አስኩማ- ገና መምቻን አድርጎ ወደ ማሕደረ ማርያም ለማቅናት ቢሞክርም የጉና ክፍለ ጦር አካል የሆነው ገብረ መስቀል ብርጌድ ከጠዋቱ 01:00 ሰዓት ላይ የመጣውን መከላከያ ባለበት እንዲቆም በማድረግ የሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ተወርዋሪ ክፍለ ጦር ከጀርባ በወርቄን በኩል ከበባ በማድረግና በመቁረጥ የገባው ኃይል ቁስቋም፣ ሺሞፈና፣ ሰንሳ ውኋ፣ ጣልሚዱ ሚካኤል፣ ስርስራውና ገና መጫወቻ እንዲመታ በማድረግ ወደ ጋሳኝ እንዲወጣ ተገዷል ።ቁጥሩ ያልታወቀ የጠላት ኃይልም ሙትና ቁስለኛ ሆኗል።
➛ነበልባሉ 23ኛ ክፍለ ጦር ከአባ ኪሮስ እስከ መነጉዘ የክፍለ ጦርዘሩ ቃኝና መሐንዲስ፣ 3ኛ ሻለቃ እና የክፍለ ጦር ስታፍ ሸኸቲ ተራራ ፣ አባኪሮስ ፣ ቀሰር ተራራ ፣ እንድርያስ ተራራ ፣ ባንዲገዝ ፣ጮሪት እና መነጉዘር ላይ ድል ተቀዳጅቷል። በሌላኛው አውደ ውጊያ ግንባር ዓለም በር ከተማ የነበልባሉ 23ኛ ክፍለ ጦር አካል የሆነችው 2ኛ ሻለቃ ዓለም በር ከተማ ከረፋዱ ጀምሮ እስከ ቀኑ 08:00 የቆዬ ውጊያ አድርጋለች።
➛ ጣና ገላውዴዎስ ክፍለ ጦር አፈርዋናት ብርጌድ ከአምበሳሜና አርብ ገበያ ተነስቶ ወደ ግንዳ ጠመምና ማሕደረ ማርያም ለመድረስ ዙ-23 እና መሰል የቡድን መሳሪያዎችን ይዞ ሲከንፍ ገላውዴዎስ ላይ አፈርዋናት ብርጌድ በደፈጣ ተመቷል። አምበሶ ብርጌድና ጣና ብርጌድ የጠላት ኃይል ከዋንዛዬና ከጉራምባ መካከል ከምትገኘው ''ተኬ በር'' ከተባለች ቦታ ላይ ሁለቱ ብርጌዶች በጥምረት ባደረጉት አውደ ውጊያ ጠላትን ማምበርከክ ችለዋል።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
