ch
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

前往频道在 Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

显示更多
2 931
订阅者
-124 小时
+1487 天
+38530 天
帖子存档
የድል ዜና!! የአ.ፋ.ብ.ን 305ኛ ጎቤ መልኬ ኮር በቀን 24/10/2018 ዓ/ም በማዕከላዊ አርማጭሆ ወረዳ ከራማ ቀበሌ በአገዛዙ ሀይል ላይ ከፍተኛ ም*ት*ን በማሳ*ረፍ በርካታ ቁጥር ያለዉን የጠላ
+1
የድል ዜና!! የአ.ፋ.ብ.ን 305ኛ ጎቤ መልኬ ኮር በቀን 24/10/2018 ዓ/ም በማዕከላዊ አርማጭሆ ወረዳ ከራማ ቀበሌ በአገዛዙ ሀይል ላይ ከፍተኛ ም*ት*ን በማሳ*ረፍ በርካታ ቁጥር ያለዉን የጠላት ሀይል እስከወዲያኛዉ በመሸኘት አንፀባራቂ ድልን ተጎናፅፏል። በታላቁ አርበኛ ዋዋ ጎቤ ስም የተሰየመዉ ግዙፉ ኮር ልክ እንደ ስሙ ትልልቅ ጀብዶችን በመፈፀም በድል ጎዳና ወደፊት እየገሰገሰ ይገኛል። ትልቅ ታሪክም እያስመዘገበ ይገኛል።

የ206ኛ ኮር 14ኛ ክ/ጦር ጀበላ ሙተራ ሻለቃ በደብረ ኤልያስ ወረዳ አበሽም ቀበሌ በመሸገው የጠላት ሰራዊት ላይ ከሌሊቱ 8:00 ሰዓት በፈፀመው ጥቃት ፦ - ወታደራዊ ቦርሳ - የክላሽ ካዝና - የጠ
+3
የ206ኛ ኮር 14ኛ ክ/ጦር ጀበላ ሙተራ ሻለቃ በደብረ ኤልያስ ወረዳ አበሽም ቀበሌ በመሸገው የጠላት ሰራዊት ላይ ከሌሊቱ 8:00 ሰዓት በፈፀመው ጥቃት ፦ - ወታደራዊ ቦርሳ - የክላሽ ካዝና - የጠላትን ወታደራዊ ሚስጢር የያዘ የአመራር 3 ስልክ - የደረት ወታደራዊ ትጥቅ - ጥይት - ወታደራዊ ጫማ እና ቁሳቁሶች ሲማረኩ በርካታ ጠላት ተደምስሷል ከሞት የተረፉት ከባድ ቁስለኛ መሆናቸው ተረጋግጧል። በተከታታይ እረፍት የለሽ ጥቃት በጠላት ላይ የከፈተው የበረኸኛው ጅበላ ሙተራ ሻለቃ የጦር አመራሮችን ጨምሮ በመደምሰስ ተከታታይ አምስተኛ ግዳጅ በብቃት ተወጠዋል። ሰኔ 24/2018 ዓ.ም አዲስ ትውልድ አዲስ አስተሳሰብ አዲስ ተስፋ የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር ህዝብ ግንኘነት

የጀግናው አርበኛ አበባው ሠለሞን 1ኛ ዓመት መታሰቢያ መርሐ-ግብር ​    ሰኔ 24/2018 ዓ.ም ​የጀግናው አርበኛ አበባው ሠለሞን 1ኛ ዓመት መታሰቢያ መርሐ-ግብር በዛሬው ዕለት በደመቀ ሁኔታ ተካሂዷል። በመርሐ-ግብሩ ላይ የጀግናው ሁለገብ የሜዳ ላይ ተጋድሎ፣ የነበረው የላቀ የፖለቲካ ብስለት እና በትግሉ ውስጥ የነበረው የፊት አውራሪነት ሚና በሰፊው ተዘክሯል። ​ ​በዚህ  የሰማዕቱ አርበኛ አበባው ሠለሞን የክብር መታሰቢያ ዕለት ላይ የአፋብን ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ እና የአፄ ዘረያዕቆብ ፩ ኮር አመራሮች የተገኙ ሲሆን የአፄ ይኩኖ አምላክ ክፍለ ጦር ​ የሠራዊት አባላትም በፕሮግራሙ ታድመዋል። ​በመድረኩ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረገው የአፋብን ወታደራዊ ቃል አቀባይ አርበኛ አበበ ሙላቱ፣ ለአርበኛ አበባው ሠለሞን ያለውን ጥልቅ አክብሮትና የትግል አጋርነት በመግለጽ ለተሰበሰበው አመራርና የሠራዊት አባል ብርቱ የትግል መልዕክት አስተላልፏል። ​"ጀግኖቻችን በአካል ቢለዩንም አልሞቱም፤ ሕዝባቸውን ከጭቆና እና ከበደል ነፃ ለማውጣት በሠሩት ታሪክ እና በከፈሉት የክብር መስዋዕትነት ሁሌም በልባችን ሕያው ሆነው ይኖራሉ።" ​አርበኛው አክሎም አሁን ስላለው የትግል ምዕራፍና ታሪካዊ ኃላፊነት ሲያብራራ "እኛ ዛሬ በሕይወት ያለነው አመራሮችና ታጋዮች፣ እነሱ የተሠዉለትን ታላቅና ቅዱስ ዓላማ ከዳር ለማድረስ ቃላችንን የምናድስበት ዕለት ነው። ለአማራ ሕዝብ ሕልውና እና መብት ስንል የማይተካ ነፍሳችንን ለመስጠት ምንጊዜም ዝግጁ መሆን አለብን" በማለት የቁርጠኝነት ጥሪ አቅርቧል። ​የአርበኛ አበባው ሠለሞን ታሪካዊ ሚና ​በዕለቱ እንደተገለጸው፣ አርበኛ አበባው ሠለሞን የጦር ሜዳ አርበኛ ብቻ አልነበረም። ​ሕዝብን በማደራጀት ረገድ ግንባር ቀደም መሪ መሆኑ፣ ​ትግሉን በማጠናከር እና መዋቅሩን በመገንባት ያሳየው ብቃት፣ ​በማስተባበር ረገድ የነበረው የፊት አውራሪነት ሚና የጎላ ነው። ክብር ለትጥቅ ትግሉ ሰማዕታት!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

አፋብን|ቴዎድሮስ ዕዝ 7 ቀን ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ጎዛምን ፈንድቃ ፣በደጋዳሞት ሀሙሲት ኤቨርት፣ ቋሪት ከተማ እና ብር አዳማ ፣ ሞጣ ፣አማኑኤል መቻከል ከተማ ሙገር በተሰራ ኦፕሬሽን ፩ የተደመሰሰ ጠላ
አፋብን|ቴዎድሮስ ዕዝ 7 ቀን ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ጎዛምን ፈንድቃ ፣በደጋዳሞት ሀሙሲት ኤቨርት፣ ቋሪት ከተማ እና ብር አዳማ ፣ ሞጣ ፣አማኑኤል መቻከል ከተማ ሙገር በተሰራ ኦፕሬሽን ፩ የተደመሰሰ ጠላት -76ኛ ክፍለጦር ከነ አመራሯ እና ህክምና ቡድኗ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ተደምስሳ መሀመድ ተሰማ ሩጠው በተረፉት ላይ ሀይል በመጨመር መልሶ ለማደራጀት እየለፋ ይገኛል። - 56ኛ ክፍለጦር አንድ ሬጅመትን ሙሉ በሙሉ ተደምስሷል። - የ25ኛ ክፍለጦረር አንድ ሻለቃ ተደምስሷል። - በርካታ ሚሊሻና አድማ ብተና በመደምሰስ የጠላትን ሀይል ሙሉ በሙሉ እቅዱን ማዛባት ተችሏል። ፪ የተደመሰሰ አመራር - ሁለት ኮረኔል - ሶስት ሻለቃ መሪ - ሁለት የሚሊሻ ጠርናፊ አመራር - በርካታ መቶ አለቃዎች ተደምስሰዋል ፫ የተገኘ ምርኮ - 3 ዲሽቃ - 1ሞርተር ባለ 82mm - 290 ክላሽ - 10 ብሬን - 6 ስናይፐር እና በርካታ ተተኳሽ እና ሎጅስቲክ ወደ ቴዎድሮስ ዕዝ ገቢ ተደርጓል። አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ ፣አዲስ ተስፋ! አፋብን | ቴዎድሮስ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ሰኔ 23/2018ዓ.ም

የአርበኛ አበባው ሰለሞን 1ኛ ዓመት መታሰቢያ:የህልውና ትግል አሻራና የማይጠፋው የነፃነት ታሪክ ሰኔ 24/2018 ዓ.ም የአማራን ህዝብ ህልውና ለማረጋገጥና ጠላትን በትጥቅ ትግል ድል ለማድረግ በተካሄደው መራራ የምድር ላይ ተጋድሎ ውስጥ፣ ስማቸው በወርቅ ቀለም ከሚፃፉ ግንባር ቀደም የጦር መሪዎች መካከል አንደኛው አርበኛ አበባው ሰለሞን ነው። የቀድሞው የሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ከፍተኛ ወታደራዊ አመራር የነበረው አርበኛ አበባው፣ በትጥቅ ትግሉ ታሪክ ውስጥ ታላቅ ስልታዊ አሻራ ጥሎ ያለፈ እውነተኛ የህዝብ አለኝታ ነው። አርበኛ አበባው ሰለሞን በየቀጠናው ተበታትነው የነበሩ ብርጌዶችንና ክፍለጦሮችን በማቀናጀትና በአንድ ወታደራዊ ዕዝ ስር በማሰባሰብ፣ የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝን በፅኑ መሰረት ላይ ካቆሙት ቀዳሚ የጦር ስትራቴጂስቶች አንዱ ነበር። በትጥቅ ትግሉ ውስጥ ወታደራዊ ዲሲፕሊን፣ የወንድማማችነትና የአንድነት መንፈስ እንዲሰፍን በሁሉም የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አውራጃዎችና የጦር ግንባሮች እየተዘዋወረ፣ የህዝቡንና የሰራዊቱን የፖለቲካ-ወታደራዊ ንቃትና ዝግጁነት በማሳደግ ረገድ የማይተካ ሚና ተጫውቷል። በተለይም አማራ ለጋራ ህልውናው በጋራ እንዲቆም ከፍተኛ ጥረት ያደረገው ይህ ጀግና፣ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መርሐቤቴ አውራጃ በራስ አበበ አረጋይ የትውልድ ቀዬ ሞረትና ጅሩ የጀግናው መታሰቢያ በደመቀ ሁኔታ ተከብሮ ውሏል። ከሁሉም በላይ ወጣቱን የህብረተሰብ ክፍል በደፈጣ ውጊያና በትጥቅ ትግል ስልቶች በማደራጀት፣ ለአማራ ህዝብ ነፃነትና ክብር ግንባር ቀደም ተዋጊ ሆኖ እንዲሰለፍ በአካልም ሆነ በስነ-ልቦና (Military Psychology) በማሰልጠን፣ ለነፃነት የሚጋደል ቆራጥና ታጣቂ ትውልድ በመቅረጽ በኩል ግንባር ቀደም መሃንዲስ ነበር። ለቆመለት የትጥቅ ትግል ዓላማና ለተሰለፈለት ህዝብ ህልውና ቀን ከሌሊት በዱር በገደሉ ሳይታክት የደከመው አርበኛ አበባው ሰለሞን፣ አማራን በጦር ሜዳ ድል ለማውጣት በተጓዘበት የእውነተኛ ጉዞ ላይ እጅግ አሳዛኝ ክስተት ገጥሞት፣ ከጀርባው በተተኮሰ የከዳተኞች ጥይት ሰኔ 24/2017 ዓ.ም ውድ ህይወቱን በጦር ሜዳ ሰማዕትነት አሳልፎ ሰጥቷል። ይህንንም ዕለት የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሲያከብር፣ ጀግናው የተሰዋለትን ቅዱስ የትጥቅ ትግል ዓላማና ወታደራዊ ግብ ከእቅዱ ለማድረስ ቃል ኪዳን የማደሻና ክንድ የማጠናከሪያ መንገድ ጭምር በማድረግ ነው። ዛሬ እሱ በሰማዕትነት ያለፈበትን 1ኛ ዓመት ስንዘክር፣ እርሱ የጀመረውን ቅዱስ የነፃነት ተጋድሎ እስከ የመጨረሻው ድል ድረስ ለማስቀጠል ቃላችንን በአንድነትና በጦርነት ወኔ በማደስ ጭምር ነው። "አርበኛ አበባው ሰለሞን፤ ስምህ በታሪክ ማህደር፣ የጀግንነት ስራህ በትውልዱ የትግል ልብ ውስጥ ለዘላለም ይኖራል።" "ክብር ለትጥቅ ትግሉ ሰማዕታት! "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

ወገኖቼ... እስኪ ለአፍታ ቆም በሉና ልባችሁን አድምጡት። ​የታሪክና የክብር ተምሳሌት እንደነበረው እንደ አባታችን እንደ አሳምነው ልብ... ኑ፣ ዛሬ በአንድ ጥላ ስር እንሰብሰብ። ኑ፣ አብረን እንመ
ወገኖቼ... እስኪ ለአፍታ ቆም በሉና ልባችሁን አድምጡት። ​የታሪክና የክብር ተምሳሌት እንደነበረው እንደ አባታችን እንደ አሳምነው ልብ... ኑ፣ ዛሬ በአንድ ጥላ ስር እንሰብሰብ። ኑ፣ አብረን እንመካከር፤ ኑ፣ ክንዳችንን አስተሳስረን አብረን እንስራ፤ ኑና ታሪካችንን አድሰን በአንድነት እናሸንፍ! በየሰንሰለታማ ተራራውና በየበረሃው ስለ ህልውናችን ደማቸውን የሚያፈሱትን፣ ቅስglobal ተጋይ ወንድም እና እህቶቻችንን በጋሻነት እንጠብቃቸው። ​እስኪ ንገሩኝ... በዚህ ጨለማ በዋጠው የጭቆና ዘመን፣ እንደ እኔ ቤቱ ድረስ ግፍ የገባበት፣ ሰላሙን የተነጠቀና የተበደለ ማን አለ? ​ለመሆኑ... እንደ ኢትዮጵያዊ ተወልዶ፣ እንደ አማራ መኖር ወንጀል የሆነባት፣ ማንነት መግደያ በሆነባት በዚህች ምድር ላይ እስከመቼ በዝምታ እንጠቃለን? ይህንን የታሪክ ጠባሳ የምንቀይረው፣ ክብራችንን የምናስመልሰውና ህልውናችንን የምናስከብረው እርስ በርስ ስንተማመንና በአንድ ልብ ለነፃነታችን ስንቆም ብቻ ነው!"

ኢትዮጵያ በቀጣናው ከፍተኛ የገቢ ግብር በመጣል 3ኛ ደረጃ ላይ ተቀመጠች። የብልጽግና አስተዳደር የህዝቡን ኪስ እያደማ ነው። ሰኔ 24/2018 ​በአፍሪካ ቀንድ እየተካሄደ ያለውን መጠነ-ሰፊ የፋይናንስ እና የግብር ማሻሻያ ተከትሎ የወጣ አዲስ ጥናት እንደሚያሳየው ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ ከሚገኙ ሀገራት መካከል በተቀጣሪ ሰራተኞች ደመወዝ ላይ ከፍተኛ ግብር በመጣል ሶስተኛዋ ሀገር መሆንዋ ተገልጿል። ​ይህ በአብይ አህመድ የሚመራው የብልጽግና አስተዳደር፣ ሀገሪቱን ካስገባት መጠነ-ሰፊ የጦርነትና የፖለቲካ ቀውስ ማጥ ለማገገም በሚል የዜጎችን ኑሮ ይበልጥ አጣብቂኝ ውስጥ እየከተተ መሆኑን የሚያሳይ ማረጋገጫ ሆኗል። የኢኮኖሚ ባለሙያዎች እንደሚሉት ከሆነ መንግስት የኢኮኖሚውን ዘርፍ ባዶ አስቀርቶ መደበኛ ተቀጣሪውን ማማረርን ዋና ስራዬ ብሎ ተያይዞታል። ​የቀጣናውን የቅጥር ገቢ ግብር ተመን ያነጻጸረው አዲስ ጥናት እንደሚያሳየው፣ የገቢዎች ሚኒስቴር ከፍተኛውን የግብር ተመን 35 በመቶ አድርሶ እየተገበረ ይገኛል። ይህ መረጃ እንደሚያሳየው የኢትዮጵያ ተቀጣሪዎች ከጎረቤት ሀገራት በበለጠ ለከፍተኛ ምዝበራ መጋለጣቸውን ያመላክታል። ከፍተኛው የገቢ ግብር ተመን ኡጋንዳ በ40% 1ኛ ስትሆን በቅርቡ በዚሁ ሳቢያ ተቃውሞን ያስተናገደችው  ኬንያ 35% ተጨማሪ ልዩ ልዩ ታክሶችን ጨምሮ ሁለተኛ ስትሆን በአብይ አህመድ የጦርነት ፖሊሲ የምትታመሰው ሀገረ ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ በ35% 3ኛ ደረጃን ይዛለች። ታንዛኒያ በ30% 4ኛ፣ ሩዋንዳ በ30% 5ኛ፣ ደቡብ ሱዳን 15% 6ኛተኛን ይዘዋል። ከጦርነት ስቃይ ወደ ኢኮኖሚ ምዝበራ የተሸጋገረው የብልጽግና አስተዳደር ውድቀት በዜጎች ላይ ተጨማሪ የኑሮ ውድነትን ጨምሯል።​ይህ የደረጃ ምደባ የወጣው ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በሐምሌ 2025 ያከናወነችውን አጠቃላይ የግብር ማሻሻያ ተከትሎ ነው። የአብይ አህመድ አገዛዝ ላለፉት ዓመታት በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የከፈታቸውና እያካሄዳቸው ያሉትን የርስ በርስ ጦርነቶች ተከትሎ፣ የሀገሪቱ የኢኮኖሚ መዋቅር ሙሉ በሙሉ እንዲፈራርስና ካዝናዋ ባዶ እንዲቀር አድርጓል። ​አገዛዙ ይህንን በጦርነትና በግጭት ምክንያት የደረሰውን የኢኮኖሚ ክስረት ለመሸፈን፣ "የኢኮኖሚ ሞዴሉን ወደ ነፃ ገበያ የመቀየር ሽግግር" እና "የመሠረተ ልማት ጉድለቶችን ለመሙላት" የሚሉ ማስተባበያዎችን እየደረደረ ይገኛል። የኢትዮጵያን ብር የመግዛት አቅም ማረጋጋት አቅቶት የዋጋ ግሽበቱ ሰማይ በነካበት በአሁኑ ወቅት፣ መንግስት መደበኛ ተቀጣሪዎችን ዋነኛ የገቢ ምንጭ (የገንዘብ ማግኛ) አድርጎ መውሰዱ የህዝቡን ስቃይና መከራ ይበልጥ አክሮታል። ​የምጣኔ ሀብት ባለሙያዎች እንደሚናገሩት ከሆነ፣ የብልጽግና አገዛዝ የግብር እርከኑን የቀረጸበት መንገድ ሆን ተብሎ ዜጎችን ለመበዝበዝ የታለመ ነው። የግብር መዋቅሩ መካከለኛ ደረጃ ላይ ያሉ ስራ አስኪያጆች እና ባለሙያዎች  ገና በቂ ገቢ ማግኘት ሳይጀምሩ፣ በፍጥነት ወደ ከፍተኛው 35 በመቶ የግብር ጣሪያ ውስጥ እንዲገቡ የሚያስገድድ ነው። ይህም በሀገሪቱ ልፋትና ጥረት አድርገው ኑሮአቸውን ለማሻሻል የሚጥሩ ዜጎችን ተስፋ ያስቆረጠ አሰራር ሆኗል። ​ "ይህ በምስራቅ አፍሪካ ሀገራት መካከል ያለው የግብር ፖሊሲ ልዩነት በቀጣናው የሰለጠነ የሰው ኃይል ዝውውር ላይ ከፍተኛ ጫና እየፈጠረ ይገኛል። የኢትዮጵያ የሰለጠነ የሰው ኃይል በአገዛዙ የግብር ጫና እና በኑሮ ውድነት ምክንያት ሀገር እየለቀቀ እንዲሰደድ በር ከፍቷል።" ​የአብይ አህመድ አስተዳደር በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ያመጣው የጦርነት ስቃይ፣ መፈናቀልና መከራ ሳያንስ፣ አሁን ደግሞ በከፍተኛ ታክስና ግብር የዜጎችን ኪስ እያደማ ይገኛል።  ጎረቤቶቹ ታንዛኒያ እና ሩዋንዳ ከፍተኛውን የገቢ ግብር ተመናቸውን በ30 በመቶ ሲወስኑ፣ ደቡብ ሱዳን ደግሞ በ15 በመቶ ዝቅተኛ ታክስ በቀጣናው የመጨረሻውን ደረጃ ይዛለች። ኢትዮጵያ ግን ካለችበት የሰላም እጥረት እና የኢኮኖሚ ቀውስ አንጻር 35 በመቶ ግብር መጣሏ፣ የብልጽግና አስተዳደር ህዝብን ማዕከል ያደረገ ፖሊሲ እንደሌለውና አላማው ስልጣኑን ለማስቀጠል ሲል ዜጎችን ማማረር መሆኑን በግልጽ ያሳያል።

ቀን 24/ 10/2018 ዓም " በፋኖ ክትትል  የተገነባው የትምህርት ህንፃ ርክክብ ተደረገ"      በአማራ ፋኖ ብሔራዊ  ንቅናቄ ጎ/ ጠ/ ግ/ በላይ ዕዝ የራስ ጋይንት ልዩ ተወርዋሪ ክፋለ ጦር  በራስ ጋይንት  ጨጨሆ ቀበሌ 19 አንደኛ ደረጃ (1__8)  ትምህርት ቤት በ 3 R  4 ድርጅት የበጀት ምንጭ  ባለ አንደኛ ፍሎር ያስገነባውን  መማሪያ ህንፃ  በቀን 23/10/2018 ዓም ከአሰሪ ኮሚቴ: ከፋኖ አመራሮችና የትምህርት ቤት ማህበረሰብ በተገኙበት  ርክክብ ተፈፅሟል።    ትምህርት የማናቃቸውን ነገሮች የምናውቅበት  ሂደት ነው።  ከሁለት ዓመታት በላይ የአብይ ስርዓት  አማራን ከሚያጠቃባቸው ዘርፈ ብዙ ሴራዎች  አንዱ ከትምህርት  የተገለለ  የትውልድ  ቅብብሎሽ አቋርጦ የነበረውን  በ2018 ዓም ከከተማ ውጭ ያሉ ትምህርት  ቤቶችን  አስፈላጊወን እገዛና ክትትል በማድረግ  ህፃናቶችና ወጣቶች በትምህርት ገበታ እንዲቆዩ የራስ ጋይንት ልዩ ተወርዋሪ ክፍለ ጦር  ክትትል ሲያደርግ ከቆየባቸው መካከል የጨጨሆ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በመሀንዲስ የጥራት ክትትል የተደረገውን መማሪያ ህንፃ ህብረተሰቡ የራሱ ንብረት አድርጎ  እንክብካቤና ክትትል  እንዲያደርግ በመተማመን በአካል ተረክቧል። የክፍለ ጦሩ ከፍተኛ አመራር የሆኑት አርበኛ ሚኪያስ  ውዱ  ዛሬ እኛ በጦርነት መሀል ቁመን ትምህርት በየትኛውም ስበብ መዘጋት የለበትም የትኛውም ለትምህርት ዕድሜው የደረሰ ሁሉ መማር አለበት  ነገ  የመከራው ምሽት ሲያልፍ የከበረና የደመቀ  የማለዳ ፀሀይ ይወጣል  ትግላችንም በፍፁም እርግጠኝነት  በአሸናፊነት ይጠናቀቃል ሲሉ  በትምህርት ዙሪያ መልዕክታቸውን አሰተላልፈዋል። የአካባቢው ማህበረሰብም ስርዓቱ ቀስበቀስ ወደ ችግር ገሀነም የሚወስደውን መንገድ ስቦ ሲኦል ውስጥ  ሲከተን ወደ ገነት ቦታ እንደሚያስገባን የዋሸን ሁሉ ትምህርት ቤቶችን በከባድ መሳሪያ እና ድሮን  ማፍረሱ እያየን ስለሆነ  ስጋታችን ነው ሲሉ ገልፀዋል።እስከ ዛሬ  በፋኖ በተደረገው ክትትልና ድጋፍ  በተለይ የ6 ኛ እና 8 ኛ ክፍል   ተማሪዎችን ቁማችሁ ማስፈተናችሁን ስናይ ከቀፋፊው እጅ አውጥቶ ከአቃፊው  ፋኖ እና እግዚአብሔር  እጅ  ጥሎናልና እናመሰግናለን ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።   *ድላችን  በተባበረ ክንዳችን   * ራስ ጋይንት ልዩ ተወርዋሪ ክ/ ጦር                     ሻምበል ተስፋ ቃል አቀባይ

የአንድነት ጥሪ...!! የተከበራችሁ የህዝብን ህልዉና በዘላቂነት ለማስከበርና ለማረጋገጥ ታላቅ መስ-ዋ-ዕት እና ዋጋ እየከፈላችሁ የምትገኙ የነፃነት ታጋዮች በሙሉ አሁን የደረስንበትና የምንገኝበት የ
የአንድነት ጥሪ...!! የተከበራችሁ የህዝብን ህልዉና በዘላቂነት ለማስከበርና ለማረጋገጥ ታላቅ መስ-ዋ-ዕት እና ዋጋ እየከፈላችሁ የምትገኙ የነፃነት ታጋዮች በሙሉ አሁን የደረስንበትና የምንገኝበት የትግል ምዕራፍ ከምንጊዜዉም በላይ አንድነታችንን አጥብቆ የሚሻበትና የሚፈልግበት ጊዜ ላይ በመሆኑ ከእኔነት ይልቅ እኛነትን በማስቀደም ለጋራ ዓላማ በጋራ እንድንቆምና እንድንሰለፍ ስል ጓዳዊ ጥሪየን አቀርባለሁ። አንድነት ለድል የሚያበቃን እና ወንዝ የሚያሻግረን ድልድይ ነዉ። አርበኛ አንዳርግ ጫቅሉ

​🟢🟡🔴 የአማራ ልጅ - የነፃነት ቀንዲል! ​ታሪክን የሚያውቅ፣ ለፍትህ የሚቆም አገር ውስጥና በስደት የምትኖሩ ውድ ወገኖቼ፤ ጠላቶች ገጻችንን ቢዘጉትም፣ የእውነትን ድምጽ ግን ሊዘጉት አይችሉም! ከአንበሶቹ የትግል ጓዶቼ ጋር በመሆን ለነፃነታችን የምናደርገውን ጉዞ ይበልጥ አድምቀን ለመቀጠል በአዲስ መድረክ መጥተናል። ​“አይዞህ” ባይነታችሁ ለጥንካሬያችን መሰረት ነውና፣ አሁኑኑ አዲሱን የፌስቡክ ገጻችንን በመከተል ለሀቅ በጋራ አብርን እንስራ ይወዳጁን!! ​👉 የፌስቡክ ገጻችንን እዚህ ይጫኑ፦ https://www.facebook.com/share/1P6KxYkqKP/

ይድረስ ለጋዜጠኛ ሄኖክ ስዩም Henoke Seyuome Hagere ወዳጄ ሄኖክ ሆይ ከዚህ ቀደም በቱሪዝም ዘርፍ ላደረግከው አስተዋፅዖ እና ለአገራችን ቱሪዝም እድገት የነበረህን ቀናኢነት እኔ ብቻ ሳልሆን የዘርፉ ባለሙያዎች ሁሉ ያውቁታል። ላለፉት ዓመታት አብረን በረሃ ለበረሃ፣ ተራራ ለተራራ ተዘዋውረን የኢትዮጵያን ውበት ለዓለም ስናስተዋውቅ የነበረው ጊዜ ትዝታው ገና ትኩስ ነው። ነገር ግን ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ጋር ያደረግከውን ቃለ ምልልስ ስታስተዋውቅ ሳይ ስሜቴ በሀዘን፣ በቁጭትና በግራ መጋባት ተሞልቷል። ወዳጄ ሄኖክ አንተ በየቱሪስት መዳረሻው ስትዞር፤ በጢስ አባይ ፏፏቴ ዳር፣ በስሜን ተራሮች አናት፣ በላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስትያናትና፣ በጣና ሀይቅ ዳርቻ ወዘተ… ከእኛ ጋር አብረው የሳቁ፣ እግራችንነ‍እ አጥበው አልጋ ለቀው ያስተናገዱን ፣ በደስታ ያስተናገዱን የዚያች ምድር ገበሬዎችና ህፃናት ዛሬ የት እንዳሉ ታውቃለህ? እነዚያ እንግዳ ተቀባይ ቤተሰቦች ዛሬ በድሮን እና በመድፍ እንደቅጠል እየረገፉ ቤት አልባ ሆነው ከሞት ጋር ግብግብ ገጥመዋል። የዛሬ ጥቂት አመታት የቱሪስት መዳረሻ ብለን ስናሞካሽባቸው የነበሩ ቦታዎች፣ ዛሬ በጦርነት እሳት እየነደዱ ነው። የቱሪስት አስጎብኝዎች የእለት ጉርስ አጥተው ለስደት ተዳርገዋል። እነዚያ በላሊበላና በስሜን ተራሮች ውበት መሃል ሲቦርቁ የነበሩ ህፃናት ሳቃቸው ዛሬ በለቅሶ ተለውጧል። ይህንን ሁሉ እያየህ፣ ይህ ሁሉ እልቂትና ውድመት ሲፈፀም የጥፋቱ ፊታውራሪ ከሆኑት ሰው ጋር ፊት ለፊት ተቀምጠህ ቃለ ምልልስ ማድረግህ፣ እንደ አንድ የቱሪዝም ጋዜጠኛ ብቻ ሳይሆን እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ህሊናህን አልጠየቀህም? ጠቅላይ ሚኒስትሩን ስለ ቱሪዝም ስትጠይቃቸው ኮይሻና ጎርጎራ ትዝ አሉህ ወይስ በመውደም ላይ ያሉት መገለጫዎቻችን? ነገር ግን ጥያቄው ይህ ነው፡- እኝህ ሰው በየቦታው ቱሪዝምን ለማልማት ፕሮጀክት ሲከፍቱ፣ በሌላ በኩል ደግሞ የቱሪዝም ማዕከል የሆኑትን የአማራ ክልል አካባቢዎች በድሮንና በከባድ መሳሪያ ሲያወድሙ ማየትህ ምን ስሜት ፈጥሮብህ ይሆን? በእርግጥ ከእርሳቸው ጋር ስትቀመጥ እውነተኛውን የቱሪዝም አደጋና የህዝቡን ስቃይ ጠየቅካቸው? ወይስ የተዘጋጀልህን ጥያቄ ብቻ በማንበብ ለሰውየው ገፅታ ግንባታ አገልጋይ ሆንክ? እንደ ቱሪዝም ጋዜጠኛ፣ ቱሪዝም የሚመሰረተው ሰላም ባለበትና የሰው ልጅ ክብር በተጠበቀበት ምድር ላይ እንደሆነ ጠንቅቀህ ታውቃለህ። ህዝቡ እየተፈናቀለ፣ ታሪካዊ ቅርሶች እየወደሙ፣ የባህል መዳረሻዎች በጦርነት እየፈረሱ፤ ስለ ቱሪዝም ማውራት የአሸዋ ላይ ህንፃ ከመገንባት አይለይም። በርካታ የቱሪስት አስጎብኝዎች ተሰደው፣ ቀሪዎቹም ከቱሪስት ጋር ሳይሆን ከጦርነት ጋር እየተዋጉ ባሉበት በዚህ ሰዓት፣ ከቱሪዝም ማህበረሰብ የወጣህ ጋዜጠኛ እንደመሆንህ መጠን፣ ለህሊናህና ለታሪክ የምትሰጠው መልስ ይኖራል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ። በድጋሚ መልካም እድል! ከወዳጅህ ምኒልክ ፋንታሁን (የቀድሞ የቱሪዝም ጋዜጠኛ፣ በአሁኑ ሰዓት ታጋይ) ጀግናው ወንድሜ Menilk Fantahun 🙏🙏🙏

ዓፄ ይኩኖአምላክ ክፍለ ጦር የአመራርና መዋቅር ማሻሻያ ማድረጉን አስታወቀ!!                               ሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ስር የሚንቀሳቀሰው እና የዓፄ ዘርዓያዕቆብ ፩ኛ ኮር አካል የሆነው የዓፄ ይኩኖአምላክ ክፍለ ጦር፣ ለሦስት ቀናት የቆየ የ9 ወራት የሥራ ግምገማና የተሃድሶ መድረክ ማካሄዱን ገለጸ። ክፍለ ጦሩ ይህንን ስልታዊ ግምገማ ተከትሎ፣ የወደፊት ግስጋሴውን ለማፋጠንና አደረጃጀቱን ለማዘመን ያስችለኛል ያለውን አዲስ የአመራር መዋቅር ማሻሻያ ለሕዝብ ይፋ አድርጓል። የኮሩ የሕዝብ ግንኙነት ሪፖርተር በላከው መረጃ መሠረት፣ የተደረገው የአደረጃጀትና የአመራር ማሻሻያ በትግሉ ሂደት ውስጥ ክፍለ ጦሩን ይበልጥ ለማዘመንና በላቀ ዲሲፕሊን ለመምራት ያለመ ነው። በዚህም መሠረት የክፍለ ጦሩ አዲስ መዋቅራዊ ይዘት በሁለት ዋና ዋና ዘርፎች (በሲቪል/ፖለቲካ እና በወታደራዊ) የተከፋፈለ ሲሆን ዝርዝሩ እንደሚከተለው ቀርቧል፦ አወቃቀሩን፦ የሲቪል ፥ የፖለቲካና ወታደራዊ  መዋቅር ዘርፍ አካቷል። ይህ ዘርፍ በዋና ሰብሳቢ የሚመራ ሆኖ በሶስት(3) ንዑሳን የኃላፊነት ክፍሎች የተዋቀረ ነው። ፩. የሕዝብ አስተዳደር ኃላፊነት፦ በአደረጃጀት፣ በሰላምና ደህንነት እንዲሁም በሕግና ስነምግባር (ፍትሕ) ንዑሳን ክፍሎች የተዋቀረ። ፪. የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊነት፦ የሪፖርተር፣ የፋይናንስ እና የግዢ ንዑሳን ክፍሎችን ያካተተ። ፫. የወታደራዊ ዘርፍ መዋቅር ይህ ዘርፍ በዋና ወታደራዊ አዛዥ የሚመራ ሆኖ በሚከተሉት ሦስት ንዑሳን የኃላፊነት ክፍሎች የተዋቀረ ነው። [  ] የኦፕሬሽናል ኃላፊነት (በምክትል የሚመራ)፦ የመረጃና መሐንዲስ፣ የዋና ዘመቻ፣ የምክትል ዘመቻ እና የኦፕሬተር ንዑሳን ክፍሎችን የሚመራ። [  ] .የወታደራዊ አስተዳደር ኃላፊነት፦ የወታደራዊ ሕግ፣ የኦርዲናንስ እና የፐርሰኔል ንዑሳን ክፍሎችን የያዘ። [  ] የሎጀስቲክ ኃላፊነት (በምክትል የሚመራ)፦ የሕክምና እንዲሁም የቀለብና አልባሳት ንዑሳን ክፍሎችን የያዘ ነው። የኮሩ ሪፖርተር መግለጫ ማጠቃለያ  ይህ አዲስ የተዋቀረው የአመራር መዋቅር የተጀመረውን የሕልውና ትግል ወደ ላቀ ምዕራፍ ያሸጋግረዋል፤ በአውደ ውጊያው ላይ የተመዘገቡ ድሎችንም ይበልጥ ያጠናክራል የሚል ሙሉ እምነት አለን ሲል ለዕዙ ሕዝብ ግንኙነት አድርሷል። በዚሁ መሠረት በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ላይ የተመደቡት አመራሮች ቃለ መሐላ ፈጽመው ሥራቸውን በይፋ መጀመራቸውን የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ አረጋግጧል። "ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!" "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!" የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!!