ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
前往频道在 Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
显示更多2 945
订阅者
+1624 小时
+127 天
+37730 天
帖子存档
በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ስር የሚገኙ ሁለት ክፍለ ጦሮች ለውሕደት የጋራ ምክክር ማድረጋቸውን አስታወቁ
ሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ መመስረቱን ተከትሎ፣ ቀደም ሲል በተለያዩ ጎራዎች ተሰልፈው የነበሩ የሁለት የተለያዩ ክፍለ ጦር አመራሮች እና አባላት በአካል ተገናኝተው ወቅታዊ የጋራ ምክክር ማድረጋቸውን አስታውቀዋል።
ዕዙ በሰጠው መግለጫ መሠረት፣ የአማራ ፋኖ አንድነት ውጤት የሆነው የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ከተመሰረተ ወዲህ፣ በቀጠናው የሚገኙ የፋኖ ሰራዊት አባላትን በማናበብ በገዥው አካል የጦር ኃይሎች ላይ በርካታ አመርቂ ድሎችን በቅንጅት መቀናጀት ይታወቃል።
ከተከናወኑት ተጨባጭ የጋራ ዘመቻዎች በተጓዳኝ፣ ቀደም ሲል በሸዋ በነበሩ ሁለት ዕዞች ስር በተለያየ ጎራ ተሰልፈው የነበሩት፡ የአፄ አምደ ጽዮን ኮር 7ለ70 ክፍለ ጦር እና የአፄ ዘርዓያዕቆብ ፩ኛ ኮር 7ለ70 ክፍለ ጦር አባላት፣ አመራሮች እንዲሁም በስራቸው የሚገኙ ሻለቆች በአካል ለምክክር ግንኙነት አድርገዋል።
በኤፍራታና ግድም ወረዳ በተካሄደው በዚህ የምክክር መድረክ ላይ የሁለቱ ክፍለ ጦር ከፍተኛ አመራሮች፣ የናሁ ሰናይ ሻለቃ፣ የስበር ሻለቃ፣ የሲኖ ሻለቃ አመራሮች ና የደምላሽ ሻለቃ ኮማንድ አመራሮች እና የሰራዊት አባላት ተገናኝተው መክረዋል።
ተመሳሳይ ስም የነበራቸው እነዚህ ሁለት ነባር ክፍለ ጦሮች በአካል መገናኘታቸው ና መመካከራቸው በሰራዊቱና በአመራሮቹ እንዲሁም በሕዝቡ ዘንድ ደስታን ና ከፍተኛ መነሳሳትን የፈጠረ መሆኑ ተገለፀ። ይህ የጋራ ውይይት ለቀጣዩ የትግል ጉዞ እና በጠላት ላይ ለሚወሰዱ እርምጃዎች ይበልጥ ጥንካሬና አንድነትን የሰጠ መሆኑን አስታውቀዋል።
➾በተያያዘ ዜና፡ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መርሐቤቴ አውራጃ፣ መርሐቤቴ ወረዳ አገሪት ቁምአንባ ቀበሌ፣ ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቀኑ 9:00 ሰዓት ላይ በግብርና ስራ ላይ ተሰማርተው የነበሩት አቶ እንጎቻ ክብርቱ የተባሉ አርሶ አደር በአገዛዙ ታጣቂዎች ተከበው መገደላቸው ተረጋግጧል።
ከአካባቢው በደረሱን ምንጮች እንደሚያመለክቱት፣ ሟቹ ቀደም ሲል በትግል ላይ እያለ መስዋዕትነት የከፈለው የአርበኛ ጎረምሳው ክብርቱ ወንድም በመሆናቸው ምክንያት ያነጣጠረ የበቀል እርምጃ ተወስዶባቸዋል።
ከዚህም በተጨማሪ በአካባቢው በሚገኙ የፋኖ አባላት ቤተሰቦች ላይ፣ ለከተማው ቅርብ በሆኑ የእርሻ ቦታዎቻቸው ላይ ወጥተው እንዳያርሱ እገዳ እንደተጣለባቸው ሰምተናል።
ይህን ተከትሎ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የአፄ ዘረያዕቆብ ኮር የናደው ክፍለጦር አባላት በሰጡት ገለፃ፣ ድርጊቱን ለማስቆም ከባድ አፀፋዊ እርምጃ እንደሚወስዱ አስታውቀዋል።
ይሕንን ተከትሎ ቁርጠኝነታቸውን የገለጹት የክፍለጦሩ አባላት፣ የአገዛዙ የፍርሀት እርምጃዎች የህዝቡንና የሰራዊቱን የትግል ጉዞ እንደማያቆሙት ይልቁንም እዲጠነክር አድርገውታል ሲሉ አክለው ገልጸዋል።
ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
+3
የብልፅግና ካምፕ በተከታታይ ባዶ ራቁቱን ቀርቷል!!
=======================
.....ዛሬ ሰኔ 10/2018 ዓ.ም
ከደብረ ወርቅ ከተማ ከድተው ከእነ ሙሉ ትጥቃቸው 201ኛ ኮር 74ኛ ክ/ጦርን የተቀላቀሉ አድማ ብተና ፦
1.ዘለቀ.... ፀሀዬ
2.ሞላ.....ዋለ
3.በላቸው ...አባተ ሲሆኑ በዛሬው እለት የተቀላቀሉት አንድም አባል የመዋጋት ስነ ልቦና የሌለው መሆኑን የገለፁ ሲሆን በቀጣይ ሁሉም አባል ለመውጣት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል የመጡትን አባላት በክ/ጦሩ አመራሮች ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
< በተደራጀ መንገድ ያለአንድ ጥይት ጩኸት የጠላትን ካምፕ እየፈራረሰ ነው ^
የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
የ64ኛ ክ/ጦር ቃኝ እና መሃንዲስ በሰሩት የደፈጣ ኦፕሬሽን 6 የአገዛዙ ሰራዊት አባላት ሲወገዱ 2ቱ ቁስለኛ ሆነዋል!!
64ኛ ክ/ጦር ሰኔ 10/2018 ዓ.ም
የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ቃኝ እና መሃንዲስ ሰኔ 09/2018 ዓ.ም በእነማይ ወረዳ ሁለት አንባ ዲቢሳ ቀበሌ በተጣለ ደፈጣ ስድስት የአገዛዙ ሰራዊት አባላት እስከ ወዳኛው ሲወገዱ ሁለቱ ቁሰለኛ ሆነዋል ከእነዚህም ውስጥ #ተክለ አብ አባቡ አይተን የተባሉ የአገዛዙ ሰራዊት አባል ቢቸና የመጀመሪያ ደረጃ ሆስቢታል የገባ ቢሆንም ወዲያውኑ መሞቱ ተረጋግጦል። ከዚህ ጋር በተየያዘ ሰኔ 10/2018 ዓ.ም በማህበረ ብርሃን ቅዱስ ገብሬኤል ቤተክርስትያን በጅምላ ተቀብረዋል።
በሁለት አንባ ዲቢሳ ቀበሌ በተጣለ ደፈጣ ከፍተኛ ኪሳራ ያስተናገደው የአገዛዙ ሰራዊት አባላት የንፁሃንን ሀብት ንብረት ዘረፎል አውድሟል። ከእነዚህም ውስጥ:-
1ኛ.መ/ር ሰው ዓለም የኔሰው ሙሉ የቤት ዕቃ
2ኛ.የሽዋስ መግስቱ የልብስ መስፊያ መኪና እና የኤሌክትሮኒክስ ሱቅ ሙሉ በሙሉ ሲዘረፍ
3ኛ.ሞጋ ስታየሁ እና
4ኛ.ሐብቴ አያሌዉ በዱላ ከጥቅም ውጭ የሆኑ
6ኛ.ዳቆን ባን ታምላክ ዉዱ በአፈሙዝ የተመታ
7ኛ.የቻለዉ ሞሴ የቀንድ ከብት በአገዛዙ ጥይት የተገደሉ ሲሆን አገዛዙ በፋኖ ከፍተኛ ብትር ሲገጥመው ንፁሃንን በመረሸን እና በመዝረፍ ለአማራ ህዝብ አረመኔ መሆኑን አረጋግጦል።
አዲስ ትውልድ! አዲስተሳሰብ! አዲስ ተስፋ!!
ሰኔ 10/2018 ዓ.ም
አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት
ስብሰባው በጭቅጭቅም ቢሆን ተጠናቋል
👉በትናንተናው እለት እኔን ጨምሮ በምድር ሀይል
ሲካሄድ የዋለው የጄነራል መኮንኖች ስብሰባ በአብዛኛው ባለመግባባት መግባባት ተጠናቋል ቃለ ጉባኤ አያያዝ ኮለኔሉን በጣም አድንቄያለሁ😁😁
😁የስብሰባው አጀንዳዎች የሚከተሉት ናቸው
1,የህወሀት የጦርነት ዝግጅትና ኦባሳንጆ ትግራይ የሄደበትን የፕሪቶሪያ ውል በተመለከተ ማብራሪያ መስጠት
2,የፋኖ ሀይሎች የውጊያ ስልት አስቸጋሪነትና የሀይል ሚዛንን በተመለከተ
3,ጦርነቱ መጀመሩ አይቀሬ በመሆኑ ውጊያውን የሚመራ ኮማንድ ፖስት ማቋቋም
✍️የመጀመሪያው አጀንዳ ላይ የብርሀኑ ጁላ ማብራሪያ
👉ህወሀት በሙሉ አቅሙ ለውጊያ እየተዘጋጀ እንደሆነና የትግራይ ወጣት 90% በሚባል ደረጃ ወታደራዊ ማሰልጠኛ መግባቱን ገልፆ አሸባሪው ህወሀት ሰፊ አውደ ግምባር የሚሸፍን ውጊያ እንደሚከፍት ገልጿል
🤔 በጣም የገረመኝ አፌን ይዤ ስከታተለው የነበረው የፕሪቶሪያ ውልን በተመለከተ ሲሆን ኦባሳንጆ ለህወሀት አመራሮች ከአብይ አህመድ ይዞት የሄደው አጀንዳ የፕሪቶርያ ውልን እንደገና ማስቀጠል እንዳለባቸውና የፕሪቶሪያ ውል አካል የሆኑት ወልቃይትና ራያን ያለምንም ውጊያ እናስረክባችሁ የሚል ነበር በዚህ ሁኔታም ብርሀኑ ጁላ ከህወሀት አመራሮች የተሰጣቸውን ምላሽ ሲያብራራ
🙉 አብሪተኛውና ፅንፈኛው ህወሀት ያቀረብንለትን የድርድር ሀሳብ እምቢ አሻፈረኝ በማለት አሁን የምንደራደረው የፕሪቶሪያ ውልን ማደስ ሳይሆን ከሁሉም ሀይሎች ጋር በመሆን የሽግግር መንግስት ማቋቋም ነው በዚህ ሁኔታ በማንኛውም ሀገር መነጋገር እንችላለን የሚል የንቀት መልስ ሰጥተውናል ብሏል 😁😁👏👏👏👏👏👏👏👏 ኧረ አጨብጭብ ጎበዝ
👉እኔም የስብሰባው ተሳታፊ ስለነበርኩ ሀሳብ ልሰጥ እጄን ሳወጣ ሻለቃ ሙላት እጄን አፈፍ አድርጎ አንተ እኮ ፋኖ ነህ አላለነኝም😁😁😁😁
😎ለማንኛውም ፋኖ ውስጥ ሆነህ ወልቃይት ምናምን እያልክ የምታላዝን ጅል መሳይ ፖለቲከኛ እረፍ ወልቃይትም ሆነ ራያ አዲስአበባም ሆነ መተከልና ደራ አሁን በብልፅግና እጅ ነው ''ጥቅማችንን 5 ሳንቲም አሳልፈን አንሰጥም የሰውም አንነካ'' የአርበኛ ዘመነ ካሴ🤴 ይህ ንግግር ብቻውን መፅሀፍ ነው::
✍️ሀለተኛው አጀንዳ የተለመደው ፅንፈኛው ፋኖ ነው
👉ጀነራሉ የፋኖ ውጊያ በታሪክ እስካሁን ከተደረጉ ውጊያዎች አስቸጋሪና ውስብስብ መሆኑን ገልፆ መከላከያ ከፍተኛ የሀይል ሚዛኑን ያጣበት ጉሬላ ውጊያ አይሉት መደበኛ ውጊያ አይሉት በአለም ላይ የሌለ የውጊያ ስልት ይከተላሉ ብሏል 👏👏👏👏👏👏አጨብጭቡ እንጂ ጎበዝ ፋኖ ምትሀት ነው ስላችሁ
👉ከዚህ ባለፈ ስለፋኖ ከቤቱ በርከት ያለ ሀሳብ ቢነሳም ጠቅለል ሲል መደበኛ ውጊያ ከመጀመሩ በፊት የፋኖን ሀይል ለማዳከም በሚል ከዛሬ ከሰኔ 10 ጀምሮ እስከ ሀምሌ 10 ተከታታይ የማያቋርጥ ኦፕሬሽን በማታና በቀን እንደሚጀምር አቅጣጫ ተቀምጧል በዚህ ወሳኝ ኦፕሬሽን መደረግ ያለባቸው ብሎ የዘረዘራቸው
✍️ በሌሊት በመንቀሳቀስ የአፈናና የከበባ ስራ መስራት
✍️የድሮን ጥቃት በተከታታይ በመፈፀም የመዋጋት ሞራላቸውን ዝቅ ማድረግ የሚልና
✍️ከፍተኛ የሆነ የምርኮና የእጅ መስጠት ፕሮፖጋንዳ አሁን ካሉት የሚዲያ ሀይሎች ላይ ተጨማሪ በማሰማራት ከፍተኛ የሆነ በጀት በመመደብ ተግባራዊ ማድረግ ይህንን በዋነኝነት የመከላከያ ኢንዶክትሪኔሽንና በበላይነት ብርጋዲየር ጄነራል ጌትነት አዳነ ከነ ዳንኤል ክብርት ጋር ሆኖ በበላይነት እንዲመራ ትዕዛዝ ተሰጥቶታል
❤ስለዚህ በብልፅግና በኩል ማረክን ይህንን ያህል ፋኖ እጅ ሰጠ የሚል ተከታታይ የውሸት ዜና ስለምትሰሙ እንዳትደናገሩ ፋኖ በማንኛውም ሰአትና ቦታ ዝግጁ ሁን!!!!!!
✍️ 3ኛው አጀንዳ መደበኛ ውጊያ መጀመሩ ስለማይቀር ውጊያውን በበላይነት የሚመራ ኮማንድ ፖስት ማቋቋም ሲሆን በጠቅላይ ሚኒስቴሩና ወታደራዊ ካውንስሉ በኩል ተቋቁሞ ይነገራችኋል ተብሏል::
😎 በዚህ አጋጣሚ ለፋኖ መረጃ የሚሰጥ አለ በሚል ከአጀንዳ በወጣ ሀሳብ ለ30 ደቂቃ ያህል ከባድ መነቋቆር ነበር እኔና ሻለቃ ሙላት በስብሰባው መሳተፋችን ታውቋል በመካከላቸውም አደገኛ መጠራጠር ተፈጥሯል 🤔🤔 ጉዳዬ አደለም ከፈለክ መጠዛጠዝ ትችላለህ
መውጫ:- አሁን ከምን ጊዜውም በላይ የምንጠነቀቅበት መጨረስ ያለብንን ነገር ጨርሰን አንዳንድ ፍላጎታችንን ትተን ለመጨረሻውና ለአይቀሬው የዋንጫ 🏆🥇ፍልሚያ ዝግጁ መሆን አለብን በስብሰባቸው ላይ ግድ ሆኖ እንጂ የሽንፈት ስሜት 100% ታይቶባቸዋል እመብርሀንን ብልፅግና ፈርሷል ስላችሁ
እንደተለመደው ለሁሉም ይደርስ ዘንድ ሼር አድርጉት
ሰዴ ወረዳ የ16 ቀበሌ ሊቀመንበር ሰላምና ደህንነት እና የህግ ኮሚቴዎች ጋር ውይይት ተካሔደ
"""""""""“""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""" """"""
ሰኔ 09/2018 ዓ.ም
አፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 54ኛ ክ/ጦር
ምስራቅ ጎጃም የሰዴ ወረዳ በቅርብ ቀን ከአምባገነኑ የብልፅግና ስርዓት በአማራ የቁርጥ ቀን ልጅ የሆነዉ አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ እና 206ኛ ኮር ጥምረት ድልን ተጎናፅፎበት ነፃ መዉጣቱ ተከትሎ የሰዴ ወረዳ ጊዜያዊ መንግስት የወረዳውን 100% ህዝብ በማስተዳደር አደረጃጀቶችን በማፅናት የጠላት ራስ ምታት ተባብሶባቸዋል።ሆኖም የሰዴ ወረዳ ጊዜያዊ መንግስት አስተዳር መልካም አስተዳደር ሰዴ ወረዳ የ16 ቀበሌ ሊቀመንበር ሰላምና ደህንነት እና የህግ አካላቶች በዛሬዉ እለት፦
1.የድርጅታችን አወንታዊ ቁመና የደረሰበትን ደረጃ በማሳወቅ
2.ጓዳዊ ዝምድናን ተግባብቶ ስራን ከመስራት አአኳያ
3.የታጠቀዉን ሀይል ንቃተ ህሌና ከማስረጥና ከማደራጀት አኳያ
4.ህዝባችን በድርጅታችን ላይ ያለዉ አቅም ምን ይመስላል
4.1 መልካም አስተዳደር
4.2 በፍትህ አሰጣጥ
4.3 ሀብት አሰባሰብና አየያዝ
4.4 ህዝብ አስተዳደርና አየያዝ እና በመሳሰሉት አጀንዳዎች ዉይይት እና ምክክር በማድረግ፣ ወንድማማችነትን በማፅናት፣ በአንድነት የፍቅር ገመድ በመተሳሰር፣ ወታደራዊ አቅምን በጋራ በማጎልበት፣ በህዝባዊ አስተዳደር ዘንድ መልካም ግንኙነት በመፍጠር ማህበረሰባዊ ጥያቄዎችን በመፍታት እና ሌሎችንም የአማራ ልጆች ቆጥረዉ ያስረከቧቸዉን የህልዉና ጥያቄዎች በመፍታት ይገኛል።
ስብሰባው ቀጣይነት እንዲኖረዉ በማሳሰብ ትግላችን ወደ አንድነት መምጣት ድልን እንደሚያመጣ ጠላት ወደ ሽንፈት ወገን ደግሞ ወደ ድል ማማ መሆኑን አመስግነዉ የመድረኩ ታዳሚዎች ገልፀዋል። የአማራ የትጥቅ ትግል እድገት ወደ በአንድነት ብስራትና አንድ ወጥ ድርጅትን ከወለደ ጀምሮ የአደረጃጀት ማሻሻያ የጊዜያዊ መንግስት አስፈላጊነት ከአገዛዙ ትይዩና የተሻለ የአስተዳደር ስራዎች ተጀምረዋል።
አዲስ ትውልድ፣አዲስ ተስፋ፣ አደስ አስተሳሰብ
አፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 54ኛ ክ/ጦር የሰዴ ወረዳ ጊዚያዊ መንግስት ሚዲያና ግንኙነት
''የድምፃዊ ሰማኸኝ በለው ስርዓተ ቀብር ተፈፀመ!''
ድምፃዊ ሰማኸኝ በለው ከአባቱ አቶ በለው ሹምየ እና ከእናቱ ወ/ሮ እናትነሽ ቢልልኝ መስከረም 17 ቀን 1960 ዓ.ም. የአባይ እና የጣና መፍለቂያ በሆነችው ውቧ ባህር ዳር ከተማ ተወለደ።
ያደገውም ቀበሌ 03 (አባ ፋሲሎ ትምህርት ቤት አካባቢ) በተባለው ሰፈር ነው። ገና ከልጅነቱ ጀምሮ ለድምፅና ለሙዚቃ ልዩ ተፈጥሯዊ ተሰጥኦ የነበረው ሲሆን፣ በማራኪ ድምፁና በደግነቱ ይታወቅ ነበር።
የመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በሰርፀ ድንግል፣ በአባ ፋሲሎ እና በጣና ሃይቅ ትምህርት ቤቶች አጠናቋል። ገና በ14 ዓመቱ በባህር ዳር ሕጻናት ኪነት ቡድን ውስጥ በመሳተፍ የረጅም ዘመን የጥበብ ጉዞውን ጀምሯል።
እሱ ድምፃዊ ብቻ ሳይሆን የግጥም፣ የዜማና የቲያትር ደራሲ፣ እንዲሁም የባህል ሙዚቃን ከዘመናዊ ስልት ጋር በማዋሃድ የኢትዮጵያን አርሶ አደር ህይወት በመድረክ ላይ ከፍ ያደረገ የጥበብ ጀግና ነበር።
የሰማኸኝ የኪነ-ጥበብ ጅማሮ በ1978 ዓ.ም. የጎጃሙን ዝነኛ “ግሼ አባይ” የኪነት ቡድንን ሲቀላቀል ይበልጥ ደመቀ።
በግሼ አባይ ከነይሁኔ በላይ እና ሀብቱ ንጋቱ ጋር በመሆን ለአራት አስርት ዓመታት በሕዝብ ልብ ውስጥ የኖረውን “አንቱየዋ” የተሰኘውን አስደናቂ ሙዚቃዊ ድራማ አቅርቧል።
በ1982 ዓ.ም. ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ከታንጎ እና ኤሌክትራ ሙዚቃ ቤቶች ጋር በመሥራት የመጀመሪያ አልበሙን አሳተመ። “ያዢኝ አላበድሁም” የተሰኘው ሥራውም ከፍተኛ ዝናን አጎናጽፎታል።
ከሶስና፣ አይቤክስ እና ሸዋ ጌጥ የምሽት ክለቦች ቆይታው በኋላ፣ በ1990 ዓ.ም በካዛንችስ የራሱን የባህል ምሽት ቤት በመክፈት የጥበብ ሥራው ይበልጥ እንዲጎመራ አድርጓል። በትያትሩ ዘርፍም “የባላገር ፍቅር” በተሰኘው ተውኔት ብቃቱን አስመስክሯል።
ሰሜ በኪነ-ጥበብ ጉዞው ካከናወናቸው ትልልቅ ድሎች አንዱ “ባላገር” የሚለውን ቃል ከኋላቀርነት ትርጉም አውጥቶ የኩራት መገለጫ ማድረጉ ነው።
መድረክ ላይ ሲወጣ የአርሶ አደር አልባሳትን በመልበስ፣ “ባላገር ነኝ” ብሎ በመዘመር የገጠሩን ማኅበረሰብ ክብር አሳይቷል። ለዚህም ነው “ሰሜ ባላገሩ” ተብሎ የተሰየመው።
የትውልድ ከተማውን ያወደሰበት “ውቧ ባህር ዳር (ዲስካው)”፣ የልጅነትንና የበዓላትን ትዝታ የቀሰቀሰበት “ደቦት እንስራ”፣ እንዲሁም በፈጣን ውዝዋዜ የታጀበው “ዘገኛ” የማይረሱ ሥራዎቹ ናቸው።
በተጨማሪም “ኧረ ምኑን ሰጠሽ”፣ “ማነሽ ማነሽ” እና “ዝናቡ” የተሰኙት ዘፈኖቹ ተወዳጅነትን አትርፈዋል። መድረክ ላይ በማይጠፋው ደማቅ ፈገግታው እና ያለ ድምፅ ማጉያ (Mic) መድረክን የመቆጣጠር ተፈጥሯዊ ብቃቱ ወደር አልነበረውም።
ሰማኸኝ ለሕግና ለፍትሕ ከፍተኛ ክብር የነበረው ሰው ነው። በ1991 ዓ.ም. በደረሰ የመኪና አደጋ ተጠርጥሮ የ4 ዓመት እስር ሲፈረድበት፣ አሜሪካ በሥራ ላይ ቢሆንም...
ሥራውን አቋርጦ በመምጣት ቦሌ አውሮፕላን ጣቢያ ላይ እጁን ለፖሊስ በመስጠት ለሕግ ተገዥነትን በተግባር አስተምሯል።
“ሦስት ነገር እወዳለሁ፤ ሀገሬን፣ ትዳሬን እና ሥራዬን” የሚለው ሰማኸኝ፣ በ1982 ዓ.ም. ከወ/ሮ ገበያነሽ አባተ ጋር ትዳር መስርቶ 4 ወንድ ልጆችን በማፍራት አሳድጓል። 4 የልጅ ልጆችንም ለማየት ታድሏል።
በማኅበራዊ ሕይወቱም ለታመመ ደራሽ፣ አረጋውያንን አቃፊ እና ታማኝ ጓደኛ እንደነበር ወዳጆቹ ይመሠክራሉ።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ውፍረቱን ለመቀነስ የተለያዩ የሕክምና ዘዴዎችን ሲከታተል የቆየው ሰማኸኝ፣ ሰኞ ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጠዋት የድካም ስሜት ተሰምቶት በልጆቹ አማካኝነት ወደ ሆስፒታል ሲወሰድ በድንገት ሕይወቱ አልፏል።
ከመሞቱ ጥቂት ቀደም ብሎም ለጀግናው ንጉሥ አፄ ቴዎድሮስ ማስታወሻ የሚሆን ዜማ ለሕዝብ አድርሶ ነበር። ስርዓተ ቀብሩ ዛሬ ማክሰኞ ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ.ም በቦሌ ቡልቡላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ተፈጽሟል።
በባህርዳር ከተማ ቤተሰቦቹ መላ የባህርዳር ከተማ ህዝብም የቀጠሮ ለቅሶ ለሰሜ ባላገሩ ለማድረግ ቀጠሮ መያዙን ግዮን ማለዳ ያገኘው መረጃ ያመለክታል ።
ለባለቤቱ፣ ለልጆቹ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹ እና ለመላው የጥበብ አፍቃሪ ስም መጽናናትን እንመኛለን ። ነብሱን ይማርልን #RIP
የአማራ ልጅ ስራ ላይ ነው አዲስና ወቅታዊ የትግሉን እንቅስቃሴ ከዚህ በተሻለ ቀጥታውን ከግንባር ሁነን እየሰራን እንገኛለን ይወዳጁን!!
በምስራቅ ጎጃም ደባይ ጠላት ግን ወረዳ በቁይ ከተማ የመሸገው የአገዛዙ ሰራዊት በአደረገው የእርስ በርስ ውጊያ ዋና ሳጅን ደሳለኝ ህይወቱን ሲያጣ ሁለት ሚኒሻዎች ከባድ ቁስለኛ ሁነዋል።
ሰኔ 9/ 2018 ዓ.ም
===================================
በምስራቅ ጎጃም ደባይ ጠላት ግን ወረዳ ቁይ ከተማ የመሸገው የአገዛዙ ሰራዊት በሁለት ተከፍሎ በአደረገው የእርስ በዕርስ ውጊያ ዋና ሳጅን ደሳለኝ የተባለው ፖሊስ ህይወቱን ሲያጣ ሁለት ሚኒሻዎች ከባድ ቁስለኛ ሁነው ደብረ ማርቆስ ሆስፒታል ለህክምና ተልከዋል።
ከመከላከያ ሰራዊት አባላት በተቃራኒው ጎራ ለይተው የተሰለፉ የሚኒሻ እና ፖሊስ አባላት ትናት ምሽት በመከላከያ ሰራዊት በተከፈተባቸው ተኩስ ግጭቱ የተቀሰቀሰ ሲሆን በቁይ ከተማ ለሰዓታት የወሰደ ውጊያ እርስ በእርስ አድርገዋል።
የፖሊስ እና የሚኒሻ አዛዦች በተሳተፉበት የምሽቱ ውጊያ ሁለት የመከላከያ አባላት እንዲሁ ህይወታቸውን አጠዋል ። ውጥረቱ እስከ አሁን አልበረደም።
አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ ! አዲስ ተስፋ!
የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መርሐቤቴ አውራጃ ሞረትና ጅሩ ወረዳ የአባት አርበኞች አደረጃጀት ተጠናከረ
ሰኔ 09 ቀን 2018 ዓ.ም
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መርሐቤቴ አውራጃ ሞረትና ጅሩ ወረዳ፣ በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ዓፄ አምደጽዮን ኮር ስር የሚንቀሳቀሰው የራስ አበበ አረጋይ ክፍለ ጦር ህዝብን የማንቃትና በክላስተር የማደራጀት ስራውን አጠናክሮ መቀጠሉን አስታወቀ።
ክፍለ ጦሩ በቀጠናው ከህዝብ ጋር በቅርበት እየሰራ እንደሚገኝ የገለጸ ሲሆን፣ የአካባቢው ማህበረሰብም የተደራጀ የፋኖ ኃይልን በደጀንነት በመደገፍ ወደፊት መገስገስ የመጨረሻ ምርጫው መሆኑን ማረጋገጡ ተገልጿል። በዚህም መሰረት በአካባቢው ነዋሪዎች ተነሳሽነት የተመሰረተው አዲስ አደረጃጀት "አብዲናጎ ክላስተር አርበኛ ኢንጅነር ናሁሰናይ ብርጌድ" በሚል ስያሜ መቋቋሙ ታውቋል።
የአካባቢው ነዋሪዎች እንደገለጹት፣ ይህ አደረጃጀት የተፈጠረው በቀጠናው የህዝብን ሰላም፣ ደህንነትና ፍትህ በአስተማማኝ ሁኔታ ለማስፈን ካለው አስፈላጊነት በመነሳት ነው። ነዋሪዎቹ አክለውም፣ በንጹሃን ላይ እየደረሰ ያለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዲሁም በትምህርት ቤቶችና በጤና ተቋማት ላይ እየተፈጸመ ያለው ውድመት ሊገታ የሚችለው በተቀናጀ የህዝብ ተሳትፎ መሆኑን አስገንዝበዋል።
የክፍለ ጦሩ አመራሮች በበኩላቸው፣ የህዝቡን ሰላምና ደህንነት የሚያስጠብቅ ጠንካራ ደጀን እየፈጠሩ ጉዟቸውን ወደፊት እንደሚያደርጉ ገልጸዋል። ማህበረሰቡም የተጀመረውን አደረጃጀት ይዞ የአካባቢውን ሰላም እንዲጠብቅ ጥሪ አቅርበዋል።
ይህ በይህ እንዳለ የቀድሞው የአፄ አምደ ጽዮን ኮር ምክትል ጦር አዛዥ የነበረው የሃምሳ አለቃ ፀሐዬ ወልዴ የ80 ቀን የዝክረ ሰማዕታት መታሰቢያ ዕለት በክብር ታስቦ ውሏል።
በዚሁ መርሃ ግብር ላይ የትግል ጓዶቹ፣ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች፣ የአፄ አምደ ፅዮን ኮር እና የአፄ ዘርዓያዕቆብ ፩ኛ ኮር የፋኖ ሰራዊት አባላት እንዲሁም የጀግናው ቤተሰቦች ተገኝተዋል።
የዕለቱ ተሳታፊዎች የጀግናውን ዓላማ ከግብ ለማድረስ ቃል ኪዳናቸውን ያደሱ ሲሆን፣ የአማራ ሕዝብ የህልውና ትግል መስዋዕትነት የነገው ነፃነት ዋስትና መሆኑን የሚገልጹ መልዕክቶች ተላልፈዋል።
ምንጭ፦ የኮሩ ሚዲያና ኮማኒኬሽን ክፍል (ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ.ም)።
'' ክብር ለትግሉ ሰማዕታት''
"ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!"
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
የኦህዴድ/ብልፅግና ሥልጣን ጠባቂ ኃይል 11ኛ ዕዝ 104ኛ ኮር 9ኛ ክ/ጦር አባላት የሆኑ 5 ወታደሮች ከነሙሉ ትጥቃቸው ምኒልክ ዕዝን ተቀላቀሉ!
የግፈኛው ሥርዓት የሥልጣን ጠባቂና ብቸኛ መከታ የሆነው ኃይል በመፍረስ ላይ የሚገኝ ሲሆን ወታደሮች የአፋብን ወሎ ቤተ_አማራ ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር 47ኛ ክ/ጦር #አትሮንስ_ሻለቃን እየተቀላቀሉ ይገኛል።
የእስረኞች ዕዝ ተብሎ የሚጠራው 11ኛ ዕዝ 104ኛ ኮር 9ኛ ክፍለ ጦር ስምና ታሪክ ብቻ ሆና ለመቅረት አፋፍ ላይ ደርሳለች፤ ማታ ታይተው ጧት የውሃ ሽታ የሚሆኑት የክፍለ ጦሯ አባላት የትየለሌ ሆነዋል። በመዓልትና በሌሊት በተገኜው አጋጣሚ ሁሉ የአገዛዙን የመዋቅር ሰንሰለት በጣጥሰው እየወጡ ነው።
በዛሬው እለት የወገን ኃይልን የተቀላቀሉ አባላት ስም ዝርዝር:-
1. መሠረታዊ ወታደር ከድር ጀማል.......የክ/ጦሩ ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ ( ወ/ጊዮርጊስ) አጃቢ
2.መሠረታዊ ወታደር በዳሳ ሀሚዳ
3. 10 አለቃ ጌታ ውለታው
4.መሠረታዊ ወታደር ይታገሱ ታዬ
5.መሠረታዊ ወታደር ይመር ጉዴታ
➥4 ጥቁር ክላሽና 1 ባለሁለት እግር ኮሪያ ሰራሽ ክላሽ
➥555 የክላሽ ተተኳሽ
➥3 የእጅ ቦንብ
➥5 የደረት ትጥቅ
➥11 የክላሽ ካዝና
ከእፉኝት ልጆች ካንፕና መዋቅር ኮብልለው የመጡ ወታደሮችን 105ኛ ኮር ም/ዘመቻ ኃላፊው አርበኛ ጎሹ ታረቀና የአትሮንስ ሻለቃ አመራሮች በታላቅ ክብር ተቀብለዋቸዋል።
በውጊያ ላይ ከሞትና ምርኮ የተረፈው ኃይል በሁሉም ቀጠናዎች እየፈረሰ በመሆኑ የሚይዘው የሚጨብጠው ያጣው የኦህዴድ/ብልፅግና ወንጀለኛ ቡድን ከፍተኛ ድባቴና የተስፋ መቁረጥ አሮንቋ ውስጥ መዘፈቁ ታውቋል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን መምሪያ
ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ.ም
በአራቱም ማዕዘን ከጀግኖች ጋር ሆኖ የሚዲያችን #አድሚን ሆኖ መስራት የሚፈልግ የአማራ ልጅ ፋኖ በውስጥ አውሩን በአንድነት የሚያምን ማንኛውንም የአማራ ታጋይ የሚያከብር
+3
ያለ አንድ ጥይት ጩኸት የአብይ ሰራዊት መፈራረሱን ቀጥሏል የፓራ ኮማንዶ አባላቱ ፋኖን ተቀላቅለዋል።
►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►
.....ሰኔ 09/2018 ዓ.ም
በዛሬው እለት ከመርጦለማርያም ከተማ ከድተው 201ኛ ኮር 74ኛ ክ/ጦርን የተቀላቀሉ ፓራ ኮማንዶወች
1.ገበያው ሞላ.....ኮሪያ መሳሪያ
2.ተስፋው አንሙት....ኮሪያ ሸ
3.እንድሪስ ሙሉጌታ....ኮሪያ እና 2 የብሬን መውጊያ ይዘው የወጡ ሲሆን በክፍለ ጦር አመራሮች አቀባበል የተደረገላቸው።
መተኪያ የሌለው ህይወታችን መስዋት አናድርግም መጀመሪያም የትጥቅ ችግር ስለነበረብን ነው ፍላጎታችን አሳክተን ወደ ወንድሞቻችንን ተመልሰናል።
የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
