ch
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

前往频道在 Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

显示更多
2 937
订阅者
-324 小时
+3667 天
+38130 天
帖子存档
የሰባት ለሰባ (7 ለ 70) ታሪካዊ ጀብዱ፦ ከጋዲሎ ሜዳ ተአምር እስከ ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የሰባት ለሰባ ክፍለ ጦር! ​"ኸረ እናንተ ሰዎች ሆዳችሁ አይባባ፣ ይዋጋ የለም ወይ ሰባት እና ሰባ!" ታሪካዊው ድባብ የተቀረጸው በታላቅ የሀገር ህልውና እና የልብ ትርታ ላይ ነው... ዘመኑ ነሐሴ 17 ቀን 1857 ዓ.ም። የሸዋ ጠቅላይ ግዛት፣ በኤፍራታና ግድም ወረዳ፣ በኤፌሶን ከተማ አቅራቢያ የምትገኘው ጋዲሎ ሜዳ በጸጥታ ተውጣለች። ነገር ግን ያ ጸጥታ ከባድ ማዕበል የተሸከመ ነበር። ​የወደፊቱ የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት፣ ብልሁና አርቆ አሳቢው እምዬ ምኒልክ ከባድና አስቸጋሪ ከነበረው የመቅደላ የዓፄ ቴዎድሮስ ግዞት አምልጠው፣ የዘር ማንነታቸውና የክብር መሰረታቸው ወደሆነችው ወደ መሀል ሸዋ በመገስገስ ላይ ነበሩ። ንጉሡ ወደ ሀገራቸው ሲመለሱ በታላቅ ተስፋና ናፍቆት ነበር። ​ነገር ግን በወቅቱ በአፄ ቴዎድሮስ ተሹመው ሸዋን ያስተዳድሩ የነበሩት እንደራሴው አቶ በዛбህ፣ የምኒልክን መምጣት ሲሰሙ ወንበራቸው ተናወጠ፤ ስልጣናቸው በብርቱ ጨለማ ተዋጠ። የምኒልክን ጉዞ በደም ለማደናቀፍና ዳግም ወደ ዙፋን እንዳይመለሱ ለማድረግ ቆረጡ። በመሆኑም በወቅቱ በዘመናዊ መሣሪያ በሚገባ የታጠቀ፣ የሰለጠነና ቁጥሩ ሰባ (70) የሚደርስ ከባድ የጦር ሰራዊት አስከትለው፣ መንገዱን ለመዝጋት ወደ ጋዲሎ ሜዳ አቀኑ። ​አቶ በዛብህ ጦራቸውን ይዘው፣ ጋሻና ጦራቸውን እያብረቀረቁ ጋዲሎ ሜዳ ላይ ሲሰፈሩ የተመለከተች አንዲት ስሟ በታሪክ ያልተጠቀሰች የአካባቢው ጀግና እንስት፣ ነገሩ የደም መፋሰስ ሊሆን መሆኑን ተረዳች። መጪው ንጉሥ የእምዬ ምኒልክ ማንነትና የጌታቸው ልጅ መሆን ያሳሰባት ይህች ታሪክ የማይረሳት ሴት፣ ለአቶ በዛብህ ጦርና ለህዝቡ ትልቅ የቅኔ ማስጠንቀቂያና ወቀሳ የምታዘልል ድንቅ ስንኝ እንዲህ ስትል አወረደችው፦ ​"ማነው ብላችሁ ነው ጋሻው መወልወሉ፣ ማነው ብላችሁ ነው ጦራችሁ መሾሉ፤ ማነው ብላችሁ ነው ካራችሁ መሳሉ፣ የጌታችሁ ልጅ ነው ኧረ በስማም በሉ!" ​ይህ ስንኝ በጋዲሎ ሜዳ ላይ አስተጋባ። የመጣው ሌላ ሳይሆን ህጋዊው የሀገር መሪና የጌታቸው ልጅ መሆኑን የምታስታውስ፣ ህሊናን የሚቀሰቅስ ጥሪ ነበረ። ከዛም ​ከእምዬ ምኒልክ ጋር ከስደት አብረው የመጡት፣ ህይወታቸውን ለንጉሡ የገበሩ ታማኝና ቆራጥ የግል ጠባቂዎች በቁጥር ሰባት (7) ብቻ ነበሩ! አቶ በዛብህ በቁጥር እጅግ መብለጣቸውንና ንጉሡ ምንም መከላከያ የሌላቸው መስሏቸው ታላቅ ንቀት ተሰማቸው። ነጋሪት እየጎሰሙ፣ ፈረስ እየጋለቡና እየፎከሩ በጋዲሎ ሜዳ ላይ ንጉሡን ከበቡ። በታላቅ ትዕቢትም እንዲህ አሉ። ​"አንተን አድብኜህ አንተን አጭሼኅ ሥላሴ ያዉቃል፣ አይጥ ከድመት መች ተርፎ ያዉቃል።" ​እነ አቶ በዛብህ 7ቱን ጀግኖች እንደ "አይጥ"፣ ራሳቸውን ደግሞ እንደ "ድመት" በመቁጠር ንጉሡን እጅ እንዲሰጡ አስጠነቀቁ። ነገር ግን እነዚያ ሰባት አንበሶች በፍርሃት ፊት አልሰጡም፤ ልባቸው አልደነገጠም! ለአንድ እውነትና ለሀገር ክብር የቆመ ሰው በቁጥር እንደማይበገግር ያውቁ ነበር። ​ይህን የሁለቱን ወገን ፍጹም የማይመጣጠን የኃይል አሰላለፍ የተመለከተችው ያቺ የአካባቢው ሴት፣ በሰባቱ ጀግኖች ልባዊ ቆራጥነትና በሰባው ጦር ግርማ መሀል ሊፈጠር ያለውን ተአምር በዓይኗ ስታይ፦ ​ "ኸረ እናንተ ሰዎች ሆዳችሁ አይባባ፣ ይዋጋ የለም ወይ ሰባት እና ሰባ!" ስትል ታሪካዊውን ስንኝ ለዓለም አበሰረች። የጋዲሎ ሜዳ ተአምር እና የባንዳው ውድቀት ​ነሐሴ 17 ቀን የጋዲሎ ሜዳ መሬት በፈረሶች ኰቴና በሰይፍ ጩኸት ተናወጠች! ፍልሚያው ተጀመረ። ሰባቱ (7) የምኒልክ የቁርጥ ቀን ልጆች፣ ሰባውን (70) በደንብ የታጠቀ ጦር መሀል ለመሀል ሰንጥቀው በመግባት ማንም አይቶት የማያውቅ አስገራሚ የጦር ስልትና የጀግንነት ጥበብ ማሳየት ጀመሩ። ​የጦርነቱ ፍጻሜ ግን ታሪክን ለዘላለም የቀየረ ሆነ! በቁጥር አነሱ የተባሉት ሰባቱ ጀግኖች የሰባውን ጦር አምሳያ የሌለው አይቀጡ ቅጣት ቀጥተው፣ በትናንትናው ትዕቢተኛ ላይ ታላቅ ድልን ተቀዳጁ! እምዬ ምኒልክን በታላቅ ክብርና ወኔ አነገሡ። እንደራሴው አቶ በዛብህ የ7ቱን ጀግኖች ክንድ መቋቋም አቅቷቸው፣ በድንጋጤና በሽንፈት ወደ አፍቃራ ቆላ ኰበለሉ። ​የበዛብህን ክህደትና አሳፋሪ ሽንፈት የሰሙ የአካባቢው ነዋሪዎችም በትዕቢተኛው መሪ ላይ እንዲህ እያሉ ገጠሙበት፦ ​"አንተም ጨካኝ ነበርክ ጨካኝ አዘዘብህ፣ እንደ ገና ዳቦ እሳት ነደደብህ!" ​የታሪክ ቀጣይነት ዛሬ የአፋብኝ ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ "ሰባት ለሰባ" ክፍለ ጦር! ​ይህ መረጃ ከኤፍራታና ግድም ወረዳ በተለያዩ ጽሕፈት ቤት በኩራት ተመዝግቦ የሚገኝ የታሪክ አሻራ ነው። ድሉ ከተበሰረ በኋላ እምዬ ምኒልክ በበርግቢ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን አድረው ወደ ታሪካዊቷ መናገሻቸው አንኮበር ተጓዙ። ጋዲሎ ሜዳም ይህንን ታላቅ ተአምር በንጉሷና በ7ቱ አንበሶች ስም አክብራ ትኖራለች። ​ታዲያ ይህ ከ160 ዓመታት በፊት በጋዲሎ ሜዳ ላይ የተጻፈው የወርቅ ታሪክ ዛሬም አልሞተም! ያ የ7ቱ ጀግኖች የጽናትና የአንበሳነት መንፈስ፣ ያ ጥቂት ሆኖ የብዙዎችን ግፍና ክንድ የመስበር ተአምራዊ ወኔ፣ ዛሬ በታሪካዊቷ የሸዋ ምድር ላይ በደመቅ ሁኔታ ህያው ሆኗል።​የአሁኑ ዘመን የሀገርና የማንነት መከታ የሆኑት የሸዋ ጠቅላይ ግዛት የአሳምነው ዕዝ "ሰባት ለሰባ" ክፍለ ጦር ጀግኖች፣ ስያሜያቸውን ቀጥታ ከዚህ ታሪካዊ የጋዲሎ ሜዳ ድል በመነሳት ኩራታቸውና መለያቸው አድርገውታል። ​ያኔ በታሪክ አጋጣሚ 7ቱ ጀግኖች የ70ውን ትዕቢተኛ ክንድ እንደሰበሩት ሁሉ፣ ዛሬም ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሰባት ለሰባ ክፍለ ጦር ያንን የትናንትናውን የጀግንነት አደራ እና የጽናት መንፈስ በመሰነቅ የማንነታቸውንና የሀገራቸውን ክብር ለማስጠበቅ በተጠንቀቅ የቆሙ የቁርጥ ቀን የነጻነት ፋኖዎች ናቸው። ​ምክንያቱም ታሪክ ይደገማል፤ ድልና ነጻነት ደግሞ የሚገኘው በቁጥር መብዛት ሳይሆን፣ እንደ ትናንቶቹ ሰባቱ ጀግኖች ሁሉ በልብ ቆራጥነትና በጽናት ነውና! በመጨረሻም ለአማራ ህዝብ ብላችሁ መስዋዕትነት የተቀበላችሁ የአማራ የቁርጥ ቀን ልጆች ነፍሳችሁ በአፀደ ገነት እንዲያስቀምጠው መልካምነቴን እየተመኘሁ ዛሬ ላይ ሰባት ለሰባን ክፍለ ጦሩን ብታዩ ብዬ ተመኘሁ #Dawit #Amhara

አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት  ይፋትና ጥሙጋ አውራጃ አንፆኪያ ገምዛ ወረዳ የኩሬ የጎደል ቀበሌ ህዝብ ጋር ሰፊ ህዝባዊ ውይይት ተደረገ። የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት  አሳምነው ዕዝ መሐመድ ቢሆነኝ ኮር አስቴጎማ ተራራ ክፍለጦር ነፃ ካወጣቸው ቀበሌዎች አንዷ የሆነችው በኩሬ የጎደል ቀበሌ አገዛዙ ከሚገኝበት የወረዳ ከተማ በስድስት ኪሎ ሜትርእርቀት ላይ የምትገኝ ቀበሌ ሲሆን በቀን 05/11/2018 ዓ/ም በኩሬ የጎደል ቀበሌ አቧር ከተማ ከቀበሌውህዝብ ጋር ሰፊ ህዝባዊ ውይይት ተደረጓል። ህዝቡ ሴት ወንድ ሳይል በነቂስ ወጥቶ ስብሰባውን የተሳተፈ ሲሆን መድረኩን የመሩት የአፋብን ወታደራዊ ቃል አቀባይ አበበ ሙላቱ እና ሌሎችም የዕዝ ፥የኮር እና የክፍለ ጦር አመራሮች ተገኝተዋል። ለመወያያ የተመረጡ አጀንዳዎች የትግላችን ገፊ ምክንያቶች፥ ትግላችን ያለበት ደረጃ ፥ልማትና ትግል እድሁም ህዝባዊ አደረጃጀትን ማጠናከር የሚሉ ናቸው። ለማህበረሰባቸን የትግሉ ገፊ ምክንያቶች የተዘነጉ ባይሆንም ብልፅግና በየጊዜዉ ከሚሰራው ደባ አንፃር ለማህበረሰቡ አፅንኦት እየሰጡ ንቃተ ህሊናውን ማሳደግ ተገቢ መሆኑ ታምኖበት ነው በአጀንዳነት የቀረበው በማለት የአፋብን ወታደራዊ ቃል አቀባይ አርበኛ አበበ ሙላቱ አስረድተዋል። የትግሉ ገፊ ምክንያቶች እና ትግላችን የደረሰበትን የእድገት ደረጃ ለተሰብሳቢው ማህበረሰብ በስፋት ያብራሩት የአፋብን ወታደራዊ ቃል አቀባይ አርበኛ አበበ ሙላት በህዝቦች ላይ የተደቀነው የህልውና አደጋ አሳሳቢ ደረጃ ላይ በመድረሱ አማራጭ ወደለለው የትጥቅ ትግል ገብተናል ሲሉ ተናግረዋል።ቃል አቀባዩ አክለውም ይህ አሸባሪ የብልጽግና መንግስት ከስልጣን እስካልተወገደ ድረስ የአማራ ህዝቡ እደ ህዝብ ከምድረ ገፅ መጥፋቱ የማይቀር ነው በማለት የስርዓቱን አስከፊነት ምን ያክል ጨካኝ እደሆነ አስረድተዋል። አርበኛ አበበ ሙላት እዳሉት የአማራ ህዝቡ በደረሰበት የህልውና አደጋ በተበታተነ መልኩ ትግል ቡንጀምርም የሴርኞችን ሴራ በጣጥሶ ዛሬ ላይ እውነተኛ አታጋይ የሆነውን ድርጀት የአማራን ቤት አፋብንን መመስረት ችለናል ብለዋል። ይህ ድርጅት ብዙ ሙህራንንና የሰለጠነ ወታደራዊ አዛዦችን የያዘ ስለሆነ በአጭር ጊዜ ውስጥ በቀጠናው ተፅእኖ ፈጣሪ ድርጅት ለመሆን በቅቷል። ያሉት አርበኛ አበበ ሙላት አክለውም የድርጅት አሸባሪውንና ፀረ አማራ የሆነውን የብልፅግና መንግስት ከስልጣኑ እሲኪወገድ ድረስ አምርሮ ይታገላል ደግሞም ያስወግደዋል ብለዋል። የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የፍትህ መምሪያ ሃላፊ አርበኛ ፈለቀ ሙላቱ በትግል ላይ ሆነን ህዝባችን በፍትህ እጦት እዳይቸገር የፍትህ መዋቅሩን አስተካክለን የፍትህ አገልግሎት እየሰጠን እንገኛለን በማለት ገልፀዋል። ስብሰባ የተሰበሰበውን ህዝብ በማዝናናት እና ስነልቦናውን በመገንባት ከፍ በማድረግ ከፍተኛውን ድርሻ ደግሞ የተወጣው የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ወታደራዊ ባህል ቡድን አባል አርበኛ ንዋይ በቀረርቶና በፉካሮ ስብሰባውን አድምቆታል። በስብሰባው የታደሙት ሃሳብ ሰጪዎች በቀረበላቸው ሃሳቦች መደሰታቸውን ገልፀው ለቀጣይ ከድርጅታችን ከአፋብን ጎን ሆነው እደሚታገሉ አረጋግጠዋል። ይህ በእንዲህ አንዳለ አንዳንድ አሉብን የሚሏቸውንም ጥያቄዎች ለመድረክ መሪዎች ለማቅረብ ችለዋል።በቀረቡት ጥያቄዎች ላይከመድረክ ተገቢ የሆነ መልስ ከተሰጠ በኋላ የማጠቃለያ ንግግር በአፋብን ወታደራዊ ቃል አቀባይ አበበ ሙላት ተደርጎ የእለቱን ስብሰባ ተጠናቋል። ክብር ለትግሉ ስማአታት ህልውናችን በተባባረ ክንዳችን አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት ሃምሌ 6/2018 ዓ/ምግብ

በአፋብን በላይ ዘለቀ ዕዝ መይሳው ካሳ ኮር ስር አድዋ ክፍለ ጦር 3ኛ ዓመት የምስረታ በዓልን አከበረ ። ግዝፉ አድዋ ክፍለ ጦር 3ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን፡ የአፋብን ስልጠና መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ኮማንዶ ሳሙኤል ባለዕድል፣የመይሳው ካሳ ኮር አመራሮች፣የክፍለ ጦሩ አመራሮችና የብርጌድ አመራሮች በተገኙበት ሃምሌ 5/2018 ዓ/ም በደማቅ ሁኔታ አክብሯል። በውስን የሰው ሃይልና በትንሽ ወንድሞች የተጀመረው የትጥቅ ትግል ሰራዊት በማሰልጠንና በማስታጠቅ፣ብቁ መሪ በማፍራት እንዲሁም መሰል ተግባሮችን በማከናወን ረገድ ከክፍለ ጦር አልፎ እሰከ ድርጅት መድረስ ተችሏል። ይህ አመርቂ ውጤት የተገኘውም በከባድና ውስብስብ ውጣውረድ፣በብዙ መስዋትነትና በበርካታ መዋዕለ ንዋይ ሲሆን የክፍለ ጦሩ አሁናዊ ሁኔታ በጠነከረ ፖለቲካዊና ወታደራዊ ቁመና ላይ እንዳለ በማመላከት ክፍለ ጦሩ በድርጅታዊ አሰራርና በመርህ የሚያምን እንዲሁም የትግሉን መነሻና መዳረሻ ጠንቅቆ የሚያውቅ መሆኑን በፕሮግራሙ ላይ በሰፊው ቀርቧል። በተጨማሪም ክፍለ ጦሩ መንግስታዊ መዋቅርን በመዘርጋት በቀጠናው ያለውን ማህብረሰብ በማወያየትና እንዲሁም የፍትህ ስርዓቱን በማዘመንና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመፍታት ረገድ ወደር የሌለው አስተዋፅኦ ማበርከቱ ተገልጿል። ይህ በእንዲህ እንዳለ፡ በሦስት ዓመት ውስጥ በቀጠናው ካለው ከአገዛዙ ሰራዊት ጋር 40 ጊዜ በላይ አውደ ውጊያ በማድረግ ቁጥሩ ከልክ ያለፈ የጠላት ኃይል እንደተደመሠሠና እንደተማረከም በሰፊው ማብራራት ተችሏል። በሌላ በኩል የፕሮግራሙ ተጋባዥ እንግዳ ከሆኑት መካከል የአፋብን ስልጠና መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ኮማንዶ ሳሙኤል ባለዕድል፣የመይሳው ካሳ ኮር ፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አርበኛ በላይሁን ይትባረክ፣የክፍለ ጦሩ ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ ተመስገን ወለላው፣የክፍለ ጦሩ ፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አርበኛ ተስፋ ጌታሁን፣የክፍለ ጦሩ ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ጌጤ ደሳኝና የክፍለ ጦሩ ፅ/ቤት ሀኃላፊ አርበኛ ጌታቸው ማንደፍሮ የሦሰተኛ ዓመት የምስረታ ባዕሉን አስመልክቶ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክትና ወቅቱን የዋጀ የፖለቲካና የፖለቲካ አሰላለፍ ለሠራዊቱ በሰፊው አብራርተዋል። ምንጭ፦በአፋብን በላይ ዘለቀ ዕዝ መይሳው ኮር የአድዋ ክፍለ ጦር ህዝብ ግንኙነት ክፍል!

በአማራ የህልውና ትግል ሂደት ውስጥ ለማንነታቸው ውድ ህይወታቸውን በመገበር ለአማራ ህልውና መረጋገጥ ሰማዕት የሆኑ አርበኞችን ለመዘከር የድያስፖራው ማህበረሰብ ባዘጋጀው መድረክ ላይ አርበኛ ብሩክ ስለሺ የአፋብን ውጭ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ተጋብዞ ያስተላለፈው መልዕክት።

አፋብን ሸ/ጠ/ግ/አ/ዕ ከሰም ፪ኛ ኮር ኃይለማርያም ክ/ጦር እና አክሊሉ ኃብተወልድ ክ/ጦር በሚገኙበት ቀጠና በስምንት አቅጣጫ ወረራ ላማድረግ የሞከረው የአገዛዙ ቅጥረኛ ሰራዊት፤ በንፁሃን ዜጎች ላይ የግድያና ዘረፈ ድርጊቶችን ፈፀመ ። ሃምሌ 05/2018 ዓ.ም፡  ሸ/ጠ/ግ/ አሳምነው ዕዝ ከሰም ፪ኛ ኮር በኃይለ ማርያም ማሞ ክፍለ ጦር እና በአክሊሉ ኃብተ ወልድ ክፍለጦር ላይ  በስምንት አቅጣጫ ወረራ ለመፈፀም የሞከረው የብልፅግናው ሰራዊት አሰቃቂ የሆነ የዘረፋና የግድያ ድርጊቶችን እንደፈፀመ ተገልጿል ። የአገዛዙ ሰራዊት ድርጊቱን የፈፀመባቸው አከባቢዎች፤ በቅዲሥ-ጌዬ ቀበሌ፣ ዛላ-ዘንባባ ቀበሌ፣ ውሃ ሜዳ ቀበሌ፣ በኮረማሽ ሸረር 3 አምባ እና የለጥ ታቦት ዋሻ፤ እንዲሁም በአክሊሉ ኃብተ ወልድ ክፍለ ጦር በቁልቋል አይብ አምባ ቀበሌ፣ አምፋር ጨመሪ ቀበሌ፣ በጎ ጥጥ አምባ ቀበሌዎች ወረራ ለማድረግ የሞከረው የብልፅግናው ሰራዊት፤ የፋኖ ክንድን መቋቋም ሲሳነው፤ በከፍተኛ ሁኔታ የህዝብ የጋራ መገልገያ የሆኑ ት/ቤቶችን እና  ጤና ኬላዎችና የግብርና ቢሮችን ዘርፎ ሲያወድም በማህበረሰቡ መኖሪያ ቤቶችና የቤት እንሰሳ በዘረፋና በማውደም በንፁሃን ዜጎች ላይም ያነጣጠር ግድያ መፈፀሙ ታውቋል ። ▪ የተዘረፉ የንፁሃን ዜጎች ንብረቶችና ግድያዎች ፦ ➢ ውሃ ሜዳ ቀበሌ የሁለት (2) ግለስብ፡ አራት (4) በሬዎችና የአንድ ግለሰብ ከ10 በላይ የእህል ማደበሪያ ተዘርፏል ። ➢ በሸረር 3 አምባ ቀበሌ የቀበሌውን ት/ት ቤት ሙሉ ለሙሉ ሲያወድም፤ እንደ ኮምፒውተርና የሶላር ሲስተም እቃዎች የመሳሰሉት ሲዘረፍ፤ ቀሪውን ቢሮችን በመሰባበር የተለያዩ ሰነዶች ወድመዋል ። ➢ ሁንያለው ጌታቸው የተባለ ግለሰብ ሲገደል፤ ምንጯ ሀይሉ የተባለች ባለግሮሰሪ ሙሉ በሙሉ እቃዎቿን በመሰባበርና ቀሪውን ንብረቶች ተዘርፈው ወድመዋል ። ➢ በቁልቋል አይብ አምባ ቀበሌ፤ አንድ (1) ንፁሃን አርሶ አደር በመኖሪያ ቤቱ አቅራቢያ ሆን ተብሎ በማነጣጠር ተገድሏል ። ይህ የጥፋት ተልዕኮ ያነገበው ሰራዊት በዞኑ ዋና አስተዳዳሪ በአቶ መካሻ አለማየሁ እና በወረዳው አሥተዳዳሪና አመራሮች፤ አቶ አባይ ግዛው እና ተገኝ አሠፋ አዛዥነት በሰራዊቱን ሆን ተብሎ ንፁሃን ዜጎች እንዲገደሉ እና ዘረፋ እንዲፈፀም አድርገዋል ። ምንጭ-አፋብን ሸ/ጠ/ግ/ አሳምነው ዕዝ ከሰም ፪ኛ ኮር ሚዲያና ኮምኒኬሽን ክፍል ሀላፊ     ክብር ለትግሉ ሰማዕታት ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን ሸዋ ጠ/ግ/አ/ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ሀምሌ 06/2018 ዓ.ም

የማንነት ሰንደቅ የሚኒልክ ትንፋሽ፦ አርበኛው እንጅነር ደሳለኝ ሲያስብ ሽዋ ፅናት!! ​የዳግማዊ አፄ ሚኒልክ መናገሻ፣ የሀገር ሉዓላዊነትና የጀግንነት እምብርት የሆነችው ታሪካዊቷ የሸዋ ምድር፤ ዛሬም እንደ ትላንቱ የነፃነት ቀንበጦችና የቁርጥ ቀን ልጆች መፍለቂያ መሆኗን በተግባር እያስመሰከረች ትገኛለች። ታሪክና ሰንበር አድረገው በሳሏት፣ ፅናትና ክብር በታደለችው የሸዋ መንዝ እምብርት ውስጥ፣ የአማራን ሕዝብ ታሪካዊ ክብርና የማንነት ህልውና ለማስጠበቅ የተነሳው የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምየው ዕዝ ዋና ሰብሳቢ አርበኛ ደሳለኝ፤ የዚህ ዘመን የፋኖ እምቢተኝነት ሕያው ማህተም ሆኗል። ​ዛሬ በዱር በገደሉ፣ በጋራና በሸለቆው የሚሰማው የፋኖ የነፃነት ክንድ እና የምድር አንበሶች ተጋድሎ፤ የእነ አርበኛ እንጅነር ደሳለኝ ሲያስብ ሽዋ የመርህ ፅናትና የስትራቴጂ ውጤት ነው። እናም ​እውነታው ግን ግልጽ ነው ለጊዜያዊ ሥልጣን ፍርፋሪና ለከርሳቸው ጥቅማጥቅም ሲሉ የሕዝባቸውን ሰላምና ክብር አሳልፈው የሰጡ፣ የጥፋትን አጀንዳ ተሸክመው የሚኳትኑ “ጥቁር ሆድ አደሮች” ይህንን አርበኛና እርሱ የሚመራውን የአማራ ልጅ ፋኖ እጅጉን አብዝተው ይጠሉታል።የፋኖ አይበገሬነቱን ያሳየው ይህ የአማራ ልጅ ጀግና በአማራ ህዝብ ላይ ክህደት፣ ባንዳነትና ሆድ አደርነት የፈፀሙትን የብልፅግና አሽከሮች የብአዴን ቅጠረኞች በየቀኑ የእግር እሳት ሆኖባቸዋልና! ​ነገር ግን ለማንነታቸውና ለታሪካቸው የሚቆረቆሩ እውነተኛ የአማራ ልጆች፣ የፋኖን የነፃነት ክንድና የአርበኛ ደሳለኝን አመራር አብዝተው በሚሳሱላቸው፣ በፍቅርና በኩራት በሞሉ ዓይኖቻቸው ይመለከቱታል። በደማቸውና በህይወታቸውም ይደግፉታል። ምክንያቱም ይህ ንቅናቄ የአማራ የቁርጥ ቀን ደራሽ፣ የሚኒልክ የታሪክ ትንፋሽና ከምንም ዓይነት ምድራዊ ሥልጣንና ማዕረግ ይልቅ “አማርነትን፣ ነፃነትንና የሕዝብን ክብር” ያስቀደመ የቁርጥ ቀን ታጋይ ኃይል ስለሆነ። ​ለጥላቶቹና ለባንዳዎች የሚገርመውና የሚያስደነግጠው እውነታ ግን ይህ ነው፤ አርበኛ ደሳለኝንና እርሱ የሚመራውን የፋኖን ስም አፍ አውጥቶ መሳደብና መዳፈር ቀርቶ፣ በሃሳብ እንኳ ነክቶ ማማት የማይታሰብ መሆኑ ነው። ​የፋኖ ፅናትና የአርበኛው መሪ ጥበብ የሸዋ ምድር ዛሬም እንዳልመከነች ሕያው ምስክር ነው። የዚህ ትልቁ ማረጋገጫ ደግሞ ጠላቶቹ ሊያጠፉትና ሊያሸብሩት ቢመኙም አርበኛ እንጅነር ደሳለኝ ሲያስብ ሽዋ ዛሬም በሕይወትና በጤና በመስዋዕትነት ሜዳው ላይ በጽናት መቆሙ ነው! ዛሬም በዕድሜውና በጉልበቱ ሳይበገር የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝን ከፊት ሆኖ በመምራት ላይ ይገኛል። ​በቅርቡ በጦር ግንባሮች በተመዘገበው አስደናቂ የጀግንነት ውሎ፣ የአርበኛ ደሳለኝ ሲያስብ ሽዋ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ መሪዎችና የአሳምነው አናብስት ፋኖ በጠላት ምሽግ ላይ እንደ መብረቅ ተከስተው፣ የክህደትን ኃይል የነቀሉበትና ታሪክ ያደነቀው ወታደራዊ ድል አስመዝግበዋል። አርበኛ እንጅነር ደሳለኝ ሲያስብ ሽዋ በቁርጥ ቀን ልጆቹ ጋር በመሆን፣ ወደ ሽዋ ምድር የዘመተውንና ንፁሃንን የሚጨፈጭፈውን የአብይ አህመድን ወራሪና አራዊት ሰራዊት እግር በእግር እየተከታተለ ድባቅ እየመታው ይገኛል። በነዛ አስፈሪ ጋራዎች ላይ የተሰማው የፋኖ ቀረርቶና ፉከራ፣ የጠላትን አጥር ሰብሮ የገባው አንበሳዊ ተወርዋሪነት፣ የሸዋን ምድር ወደማይደፈር የነፃነት አምባነት ቀይሮታል። ​ይህ የጦር ሜዳ ጀግንነት፣ የጠመንጃቸው ኃይልና የፅናት ማዕበል የማንነታችን ሰንደቅ ዓላማ በጀግኖቻችን ትከሻ ላይ ከፍ ብሎ ለዘላለም እንደሚወለብል ማረጋገጫ ነው። የፋኖ ጀግንነትና የአርበኛው ደሳለኝ ገድል የትውልዳችን የነፃነት አዋጅ ነው ታሪክ በደማቅ ቀለም እየፃፈ፣ ጠላት በሽብር የሚረበሽበት፣ ወዳጅ በኩራት አንገቱን የሚያቀናበት የዘመናችን እውነተኛው የድል ታሪክ እየሰራ ይገኛል። የአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ዋና ሰብሳቢ አርበኛ እንጅነር ደሳለኝ ሲያስብ ሽዋ ፈጣሪ እንዲጠብቅህ እመኛለሁ። #Dave #Amhara

የፓራ ኮማንዶ አባላቱ ፋኖን ተቀላቀሉ ➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺ .......ሐምሌ 6/2018 ዓ.ም ወደ ትግራይ ክልል ግዳጅ መጓዝ አለባቹህ መባሉን ተከትሎ በሁሉም አቅጣጫ ከጠላት ጋር ወግነው የነበ
+5
የፓራ ኮማንዶ አባላቱ ፋኖን ተቀላቀሉ ➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺ .......ሐምሌ 6/2018 ዓ.ም ወደ ትግራይ ክልል ግዳጅ መጓዝ አለባቹህ መባሉን ተከትሎ በሁሉም አቅጣጫ ከጠላት ጋር ወግነው የነበሩ የአማራ ልጆች ፓራ ኮማንዶወች ከግንደወይን እና ከጠልማ በመውጣት 201ኛ ኮር 74ኛ ክ/ጦርን ከተቀላቀሉት መካከል፦ 1.ታሪኩ አለምሻ ...ፓራኮማንዶ ከግንደ ወይን 2.አብርሐም ልጃለም...ፓራኮማንዶ ከጠልማ 3.ዳግም በላይ..ሚሊሻ..ከግንደወይን ሲሆን ሁሉም የአማራ ልጆች ይኸን አጋጣሚ በመጠቀም ወደ ወንድሞቻቹህ እንድትመለሱ በማለት ጥሪያችን እናስተላልፋለን። የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት

በየጎሳ ቀበሌ የሁለት ሰዎችን ህይወት በአሰቃ ሁኔታ የገደለው ሚሊሻ በ64ኛ ክ/ጦር ሰርጎ ገብ/ቀኘ ቢቸና ከተማ ተገደለ!! 64ኛ ክ/ጦር ሀሞሌ 06/2018 ዓ.ም ~ በቴዎድሮስ ዕዝ ከሚገኙ ክ/ጦሮች በሰርጎ ገብ ስራ ሁሌም የሚታወቀው አይበገሬው 64ኛ ክ/ጦር በተለያዩ ሴራዎች ተተብትቦ የተለያዩ ወታደራዊ ግዳጆችን እንዳይሰራ ቢደረግም ከቅርብ ቀን ወዲህ ክ/ጦሩ ከውጭና ከውስጥ ገብተው የነበሩ እጆችን በመቁረጥ በወታደራዊ ግዳጆች ወደ ቀድሞው ገናና ስሙ በመመለስ ድል እያደረገ ይገኛል። #ሚሊሻ አበጄ ጌትነት ይባላል በእናርጅ እናውጋ ወረዳ የጎሳ ቀበሌ ተወላጅ ሲሆን በየጎሳ ቀበሌ በትዳር ላይ የነበሩ ባልና ሚስትን ሰውነታቸውን በቢለዋ በመቆራረጥ በአሰቃቂ ሁኔታ በመግደል ቢቸና ከተማ የሚገኘውን አገዛዝ ቅጥረኛ የሚሊሻ ሰራዊት ተቀላቅሎ ቆይቷል። ይህ ግለሰብ የሁለት ሰዎችን ህይወት በአሰቃቂ ሁኔታ በመግደል በቢቸና ከተማ ለአገዛዙ ስርዓት በባንዳነት ቅጥረኛ በመሆን ሲያገለግል የቆየ ቢሆንም በ64ኛ ክፍለ ጦር የውስጥ ሰርጎ ገብ/የቀኜ አባላት ከፍተኛ ክትትል አማካኝነት ሀምሌ 05/2018 ዓ.ም ቢቸና ከተማ እስከ ወዳኛው ተወግዶል።   በክ/ጦሩ ቀጠና እነማይ እና ሸበል በረንታ ወረዳ ወንጀል በመስራት በሰረው ወንጀል ላለመጠየቅ ከጠላት ጋር በማበር የህዝባችንን ስቃይና መከራ ለማራዘም የሚሞክር ግለሰብ ይሁን ቡድን ከክ/ጦሩ ከባድ እርምጃ እንደማያመልጥ እናሳውቃለን። አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!!                  ሀምሌ 06/2018 ዓ.ም ፋኖ Yibeltal Getie Mitiku አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት

እኔ የታሪክ እረገማን ያረፈብኝ፣ አማራ ሆኜ በመፈጠሬ ብቻ የሞት ፍርድ የተፈረደብኝ፣ ስቃይ እንደ ጥላ የሚከተለኝ የአማራ ልጅ ነኝ። እውነት ለመናገር... እኔ ላይ ያልደረሰ፣ ስጋዬን ያልቀደደና ህሊናዬን ያላደማ የበደል ጽዋ የለም። ​የአጣዬ አመድ፣ በወለጋ ምድር የፈሰሰውና መሬቱን ያጠገበው የንጹሃን ወገኖቼ ደም፣ የወልቃይት፣ የደራ እና የራያ እናቶች ሰቆቃ... እያንዳንዱ ዋይታ ዛሬም በጆሮዬ ላይ ያቃጭላል። የሰው ልጅ ክብር ተገፎ፣ ልክ እንደ ከብት በገጀራ እና በባዶ ጥይት ሲታረድ ማየት ምንኛ ልብን ያደማል? ​የዚህ ሁሉ መቅሰፍት መነሻ የብልፅግናው ስርዓት ብቻ አይደለም። ይልቁንም ልባችንን ክፉኛ የሰበረውና ነፍሳችንን ያቆሰለው የራሳችን ወገን የሆኑት፣ ለሆዳቸው ያደሩትና በአስመሳይነት የተከናነቡት "የሆዳም አማራ" መሪዎች የፈጸሙብን የጀርባ ክህደት ነው። ​ይህ እኛን ከምድር ገፅ ለማጥፋት የታለመው ስውር ጦርነት ዛሬ የተጀመረ እንዳይመስላችሁ። ከብዙ ዓመታት በፊት በክፋት ታቅዶ፣ በረቀቀ መንገድ ሲሰላ የኖረ እንጂ። እንደ ዘመኑ ጨካኝ ዱቅልጣኖስ የሆነው ሽመልስ አብዲሳ የኦሮሚያን ሙሉ በጀት በመመደብ የአማራን ሚሊሻ እና ልዩ ኃይልን ደሞዝ በመክፈል እንደ አንበሳ የሚተማመኑ ጀግኖቻችንን ጋር እርስ በእርስ እንዲዋጉ ያደረገበት ተንኮል መግለጫ የሌለው የታሪክ ጠባሳችን ነው። ​የተከበራችሁ ወገኖቼ፣ አሁን ላይ በውስጤ የታመቀውን ስቃይ ሁሉ አውጥቼ ለመናገር ቃላት ያጥሩኛል። ውስጤን እንደ እሳት የሚበላኝ፣ ቀንና ሌሊት የሚያንገበግበኝ የአማራ ልጅ ሰቆቃ እኔን ብቻ ነው መሰል የሚያመኝ? ለምንስ ዓለም ጆሮዋን ደፈነች? እንድንል አድርጎናል። ​በመጨረሻም፣ ውድ አማራውያን ወንድሞቼ እና እህቶቼ... የእነዚያን የቅንጦት ኑሯቸውን ትተው፣ ሞትን እንደ ጓደኛ ቆጥረው በየበረሃውና በየገደሉ የሚሰቃዩትን የፋኖ ታጋይ ወንድሞቻችንን ሁኔታ ስታዩ ልባችሁ በሃዘን አይፈርስም? ​አስቡት፣ ፈጣሪ የሰጣቸውን ውድ ነፍሳቸውን ለአማራ ህዝብ ነፃነት ሲሉ ለመስጠት በቆረጡበት በዚህ ሰዓት፣ ስም እየሰጡ ወንድምን ከወንድም ጋር ማገዳደል ምን ዓይነት መርገምት ነው? ስለዚህ፣ እባካችሁ... ከእንግዲህ መከፋፈል ይብቃን። እጃችንን ለአንድነት እንዘርጋ፤ ታጋይ ወንድሞቻችንን እናክብር፣ ከጎናቸውም እንቁም። ​የልባችንን ስብራት የምናክመውና ክብራችንን የምናስመልሰው፣ ሁልጊዜም በውስጣችን በሚያስተጋባው በዚያ ታላቅ የጀግና ንግግር ነው፦ ​"አማራ ሆይ! አንገትህን ቀና አድርግ፤ አንተ የጀግኖች ዘር ነህ! አማራነት ኩራት ነው፣ ክብሩን ለማስከበር ደግሞ አንድ መሆን የግድ ይላል። ጠላት የሚንበረከከው በልመና ሳይሆን በአንድነትህና በክንድህ ጥንካሬ ነው!" ብርጋዴር ጄኔራል አሳምነው ጽጌ ​ድል ለአማራ ልጅ ፋኖ!! ​ድል ለፋኖና ለታጋይ ድርጅታችን! አፋብን!! #Dave #Amhara

የንጉሥ ሣህለ-ስላሴ ክፍለ ጦር ለ3ኛ ዙር የፋኖ ሰራዊት አባላትን አስመረቀ!!! ​ሐምሌ 06 ቀን 2018 ዓ.ም ​በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ፣ የአፄ አምደ ፅዮን ኮር ስር የሚገኘው ንጉሥ ሣህለ-ስላሴ ክፍለ ጦር ለተከታታይ ወራት የፖለቲካና ወታደራዊ ስልጠና ሲሰጣቸው የነበሩትን የ3ኛ ዙር ምልምል መደበኛ የፋኖ ሰራዊት አባላትን ሐምሌ 5 ቀን 2018 ዓ.ም አስመርቋል። በሳሲት ክላስተር በተካሄደው የፋኖ ሰራዊት ምርቃት ፕሮግራም ላይ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ከፍተኛ አመራሮች፣ የኮር፣ የክፍለ ጦር እንዲሁም የተጉለትና ቡልጋ አውራጃ የቀበሌ አመራሮች ተገኝተዋል። የክፍለ ጦሩ ዋና አዛዥ መቶ አለቃ ደሞዝ አሽኔ ለተመራቂዎቹ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን፣ የሰልጣኞችን መታወቂያና ሰርተፍኬት አበርክተዋል። ለስኬቱ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላትም ምስጋና አቅርበዋል። በምርቃ መርሃ ግብሩ የዕዙ የፖለቲካ አመራሮች የተገኙ ሲሆን አርበኛ መስፍን ተስፋዬ እና አርበኛ ሀኪም ግዛቸው ሣህለ ተጉለትና ቡልጋ የበርካታ ነገስታት መፍለቂያ መሆኑን በመጥቀስ፣ ተመራቂዎቹ የዚህ ታሪካዊ ማህበረሰብ አካል በመሆናቸው የተሰማቸውን ኩራት ገልጸዋል። የተጉለትና ቡልጋ አውራጃ የሳሲት ክላስተር ዋና አስተዳደሪ አርበኛ ኃይሉ ለገሰ ለተመራቂዎቹ የቃል ኪዳን አደራ የሰጡ ሲሆን፣ ለአሰልጣኞች የማበረታቻ ሽልማት እንዲሁም ለክላስተርና ቀበሌ አመራሮች የክብር እውቅና በመስጠት በደማቅ ሁኔታ ተጠናቋል። ክብር ለትግሉ ሰማዕታት ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን ​የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

ሰበር ዜና!! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ወሎ ቤተ አማራ ጀብደኛዉ ምኒልክ ዕዝ 24ኛ ክፍለጦርና እና 35ኛ ክፍለጦር   በጋራ ታላቅ ጀብድ በመፈፀም ድል ተቀዳጁ። የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄ ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ከ104ኛ ኮር 24 ክፍለጦር  እና ከ101ኛ ኮር 35 ከወልዲያ ፣ ከመርሳ : ከሳንቃ እንዲሁም ከዕዜት ስርዐቱ በብዛት አግተልትሎ ወደ ደቡብ ወሎ ዞን አምባሰል ወረዳ 015 ቀበሌ ልዩ ቦታው  ወፉጮና ቋሆ  ወደ ተባለ ቦታ ዛሬ ሀምሌ 05/2018 ዓ.ም  ከጥዋቱ 2:30 አካባቢ ሲንቀሳቀስ የነበረው ይህ የስርዐቱ ወንበር ጠባቂ ጦር በተጠና  እና ውጤታማ በሆነ ደፈጣ በ35ኛ ክፍለጦር  እና በ24 ክፍለጦር በርመጠበቂያ  እየተባለ በሚጠራ ቦታ ላይ በመደምሠስ ድል ተጎናፀፉ።   በዚህ አውደ ውጊያ ዛሬ ሀምሌ 05/2018 ዓ.ም ከጥዋቱ 2:30 ጀምሮ በተደረገ ተጋድሎ የስርዐቱን ጦር በተጠና ደፈጣ ጥቃት ከ75 በላይ መደምሰስ ሲቻል ከ30 በላይ በማቁሰል ድል መጎናፀፍ ሲቻል ፣ይህ ከተለያየ ቦታ በገፍ ተሰባስቦ የመጣ ሀይል ነፍስ አውጭኝ በማለት ወደ መጣበት እየተበታተነ ተመልሷል። በዚህ የተበሳጨው የጥላት ሀይል   ከመርሳ እና ከጀነቶ ጀኔራል መድፎችን ከጥዋቱ 4:00 ጀምሮ በዘፈቀደ ወደ ህዝባችን ያለ ማቋረጥ እሰከ ቀኑ 9:30 ድረስ ሙትና ቁስለኛውን ለማውጣት እየወረወረ ወይም እያስወነጨፈ ውሏል።በመጨረሻም በአራት ኦራል ሙትና ቁስለኛውን ወደ መርጦና ወልዲያ እያጓጓዘ አመሸቶ ፣ በከባድ መሳሪያ ሽፉን እየሰጠ እያግተለተለ ያመጣውን ቅጥረኛ ሰራዊት ወደ  ዕዜት ና መርጦ ጀግኖቹና ነበልባሎቹ 24ኛ እና 35ኛ ክፍለጦር መልሰውታል ሲል የአፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ  የ24ኛ  ክፍለጦር ቃል አቀባይ  ፉኖ አሉላ ዮሀንስ መረጃውን ልኮልናል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ  ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!! ሀምሌ 05 /2018 ዓ.ም