ch
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

前往频道在 Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

显示更多
2 926
订阅者
+3224 小时
+3727 天
+36630 天
帖子存档
ከአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ወታደራዊ ስልጠና መምሪያ የተላለፈ የስልጠና ጥሪ!! ! "እምቢ ለሕልውናዬ! እምቢ ለነፃነቴ"! የአማራ ሕዝብ የሕልውናና የነፃነት ትግል በጀግኖች የአማራ ፋኖ አርበኞች በሚያደርጉት መራራ ተጋድሎ አሁን ላይ የመጨረሻውና ወሳኙ ምዕራፍ ላይ ደርሷል። ፀረ አማራውና ሀገር አውዳሚው የብልፅግና አገዛዝ በየግንባሩ በደረሰበት ከባድ ወታደራዊ ሽንፈት ምክኒያት የመቃብር አፋፍ ላይ ቆሞ የመጨረሻ ጣዕረ ሞቱን እያሰማ ይገኛል። ይህ ተጋድሎ፡ የአማራን ሕዝብ በጅምላ እየጨፈጨፈ፣ በጅምላ እያፈናቀለና እያሳደደ የሚገኘውን ከዚህ አልፎ አገሪቱን በጦርነት እያመሰ ወደ አዘቅት እያምዘገዘጋት የሚገኘውን የብልፅግና አገዛዝ ገርሶ፡  የአማራን ሕዝብ ሕልውና ማስከበርና የፍትሕ ርትዕ ማስፈን፡ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በሰላም ወጥቶ በሰላም የሚገባበትና በየትኛውም የሀገሪቱ አከባቢ በነፃነት ተንቀሳቅሶ ሀብት ንብረት የሚያፈራበትን፣ ሁሉም ብሔር ብሔረሰቦች በእኩል አይን የሚታዩበትን፣ ተማሪዎች ተምረው ስራ ይዘው ሀገር የሚያገለግሉበትን፣ ድሃ የማይበደልበትን ፍትህ የማይጓደልበትን መንግስት ለመመስረት የሚደረግ ታሪካዊ ትግል ነው። ስለሆነም፦ ➛ ይህ ትግል የጥቂቶች ሳይሆን የመላው የአማራ ሕዝብ የጋራ እጣ ፈንታ በመሆኑ፡ ነገ ነፃ በምትወጣዉ ሀገርና በሚገነባው ፍትሐዊ አገዛዝ ስርዓት ላይ "እኔም ዋጋ ከፍዬበታለሁ፡ የኔም ድል ነው" ብሎ በኩራት ለመቆም ➛ ነፃ በወጡና ወደፊት ነፃ በሚወጡ ቀጠናዎች የሕዝባችንን ሰላም፣ ሕግና ፍትሕ በአስተማማኝ ሁኔታ ለማስከበር ➛  አገዛዙ በተስፋ መቁረጥ ውስጥ ሆኖ ለጉልበት ሥራ፣ ለትምህርትና ለገበያ የሚንቀሳቀሱ ወጣቶችን አፍኖ ለጦርነት የሚማግድበትን እኩይ ድርጊት ሙሉ በሙሉ ለመግታትና ወጣቱን ከአጋች ኃይሎች ለመጠበቅ እድሜያችሁ ለትግል የደረሰ የወሎ ቤተ-አማራ ወጣቶችና የመላው አማራ ልጆች በሙሉ፡ በምኒልክ ዕዝ ስር በሚገኙ በሁሉም ቀጠናዎች በፍጥነት በመመዝገብ የታሪክ አሻራችሁን እንድታስቀምጡ የክተት ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። ከዚህ በታች ያለውን መስፈርት የምታሟሉ መታችሁ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑኑን እናሳውቃለን። ꕺ በማህበረሰቡ ዘንድ በጥሩ ስነምግባር የሚታወቅ/የምትታወቅ ꕺ በክልሉ ውስጥና ውጭ ከሚገኙ ከየትኛውም ቀበሌዎች መታወቂያ ማቅረብ የሚችል/የምትችል ꕺ ከማንኛውም ደባል ሱሶች ነፃ የሆነ/የሆነች ꕺ ሙሉ የአካልና የአዕምሮ ጤነኛ የሆነ/የሆነች ꕺ ከማንኛውም ወንጀል ነፃ የሆነ/የሆነች ꕺ በአማራነቱ የሚኮራና የአማራን ሕልውናና ነፃነት ለማስከበር ሙሉ ቁርጠኝነት ያለው/ያላት ማሳሰቢያ፦ ስትመጡ መታወቂያችሁን በሁለቱም በኩል ኮፒ አስደርጋችሁ መያዝ ይጠበቅባችኋል ::      ህልዉናችን  በተባበረ ክንዳችን! መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!   የጀብደኛው ምኒልክ ዕዝ ወታደራዊ ስልጠና መምሪያ ኃላፊ                          ነሃሴ 10/2018ዓ.ም

03 የአገዛዙ የሠራዊት አባላት 01 ብሬን ፣01 ስናይፐርና 03 ክላሽኮቭ ከእነ ሸንሸሉና ተተኳሹ በመያዝ የበረኸኛው ቀስተ ደመና ፋኖን ተቀላቀሉ‼️ በአማራ ላይ ሁለንተናዊ የጅምላ ፍጅት እየፈጸመ የሚገኘው የኦሕዴድ መሩ የብልጽግና ሥርዓት ሎሌ የሆነው የመከላከያ ተብየ በገፍ እየፈራረሰ ፋኖን እየተቀላቀለ ይገኛል። በዛሬው ዕለት ማለትም በቀን 09 ለ10/12/2018 ዓ.ም ሌሊት በራሱ አጠራር የ10ኛ ክፍለ ጦር 1ኛ ሬጅመንት ሁለት ሻምበል መሪዎችና አንድ ብሬን ተኳሽ የመከላከያ አባላት #01_ብሬን_ከእነ_ሸንሸሉ፣ #01_ስናይፐር፣ #01_ኮፍ_ክላሽኮቭና #02_ሁለት_እግር_ክላሽኮቭ በመያዝ አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር 14ኛ ክፍለ ጦር የደብረ ኤልያስ በረኸኛው ቀስተ ደመና ሻለቃን ተቀላቅለዋል። በአገዛዙ የጭካኔ ጥግ በእጅጉ የተሳቀቀው የመከላከያው የሠራዊት አባል ከዕለት ወደ እየጨመረ በመጣው የሥርዓቱ ግፍና የንጹሐን መጨፍጨፍ ከዚህ ተቋም በመክዳት በዙሪያው ወደ ሚገኘው ወረዳውን በመምራት ላይ ወደሚገኘው የደብረ ኤልያስ ቀስተ ደመና ፋኖ ከእነ ቡድንና የነፍስ ወከፍ መሳሪያው እየተቀላቀለ ይገኛል። ከአሁን በፊትም ከሁለት ሳምንት በፊት በተመሳሳይ መልኩ አንድ ስናይፐር መረከባችን የሚታወቅ ነው። እኛም እንላለን በፍቅርና በሰላም ለሚመጣ የምሕረት ደጃችን ክፍት ነው። 10/12/2018 ዓ.ም

"በአዲስ አበባ ከተማ እና ነዋሪወቿ ላይ የተደቀነው የህልውና አደጋ በድርጅታችን ቁርጠኝነት፣ በህዝባችን ፅናትና በፀረ ብልፅግና ብሔራዊ ኃይሎች ትብብር በሚታጀበው የትግላችን አይቀሬ ድል የሚመመከት ይሆናል" ከአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን)፤ በአዲስ አበባ ጉዳይ የተሰጠ የአቋም መግለጫ ! ነሐሴ 09/2018 ዓ.ም ዘረ ፈጁ የብልፅግና አገዛዝ ''አገራዊ ምክክር'' በሚል ስም በኢትዮጵያ፤ በአዲስ አበባ ከተማ የሚያካሂደው የድራማ መድረክ የህዝብ ውክልና የሌለበት፣ ተጨማሪ ቀውስ የሚያዋልድ እና የአገዛዙን ዕድሜ ለማራዘም የተነደፈ የአረመኔው አገዛዝ የፖለቲካ አሻጥር መሆኑን ከዚህ በፊት ባወጣነው መግለጫ አቋም መውሰዳችን ይታወቃል። ሆኖም ግን አገዛዙና አጋሮቹ ይህንን ከጥፋት መንገዳቸው እንዲመለሱ ያቀረብንላቸውን ጥሪ በመተው ''በምክክር'' ስም የከተሞችንና አካባቢዎቻቸውን የታሪክ፣ የዴሞግራፊ፣ መልክአምድራዊና የይዞታ ቅርፃቸውን ለማዛባትና በተለይም ነባር የአዲስ አበባ ከተማ ኗዋሪዎችንና የአማራን ህዝብ ህልውና አደጋ ላይ ለመጣል የጥፋት መንገድ ላይ መሆናቸውን ተገንዝበናል። አዲስ አበባ ከተማ እንደገና ከመቆርቆሯና ከአሁኑ መጠሪያዋ ቀደም ብሎ ''በራራ'' በመባል የምትታወቅ፣ በመካከለኛው ክፍለ ዘመን በጦርነት ሳቢያ እስከወደመችበት ጊዜ ድረስ የአማራ ነገስታት መቀመጫና የአማራ ህዝብ ጥንተ-ርስት እንደሆነች የታሪክ መዛግብትና አርኪዮሎጂያዊ ማስረጃዎች በግልፅ ያረጋግጣሉ። ዳግማዊ አፄ ምኒልክ እና እቴጌ ጣይቱ ብጡል አዲስ አበባ ከተማን በድጋሚ ሲቆረቁሯት፣ ባዶ መሬት ላይ ሳይሆን የአባቶቻቸውን ታሪካዊ ይዞታ፣ ርስትና ውርስ መነሻ በማድረግ ነው። ይህ ታሪካዊ እውነት ሊሸረሸርም ሆነ ማንም አምባገነናዊ አገዛዝ በጊዜያዊ ስልጣን ህዝብ ባላመነበት ፖለቲካዊ ውሳኔ ሊሰርዘው የማይችለው ፅኑ የታሪካችን አንድ አካል ነው። ከተማዋ የአማራ ጥንተ-ርስት መሆኗ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ በሂደት የሁሉም የኢትዮጵያ ህዝብ መኖሪያ፣ የባህልና የኢኮኖሚ ማዕከል፣ እንዲሁም የአንድነት ተምሳሌት ሆና ተገንብታለች። ከዚህ አኳያ ድርጅታችን የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) አዲስ አበባ የኗዋሪዎቿ፣ የሁሉም ኢትዮጵያዊያን መኖሪያ፣ የኢትዮጵያ ዋና ከተማ፣ የአፍሪካ መናገሻና የዓለም አገራት የዲፕሎማሲ ማዕክል መሆኗን ሙሉ በሙሉ ያምናል፤ ይቀበላልም። በዚህ መነሻ፣ ከተማዋ የብዝኃነትና የጋራ እድገት ማዕከል እንጂ የአንድ ዘረ ፈጅ አገዛዝ ብቸኛ መጫወቻ ስፍራ ልትሆን እንደማትችልም ድርጅታችን ያረጋግጣል። የአማራ ህዝብ፣ አዲስ አበባን ጨምሮ በመላ አገሪቱ በስፋት በሚኖርባቸው አካባቢዎች፤ ፍትሐዊ የስልጣንና የሀብት ተጠቃሚነቱ መረጋገጥ እንዳለበት ድርጅታችን ያምናል። በአሁኑ ወቅት፣ የኦህዴድ ብልፅግና አገዛዝ አዲስ አበባን በብቸኝነት የአንድ ወገንና ብሔር በበላይነት እንዲቆጣጠራት ለማስቻል የሚሰራው ሕግን የጣሰ፣ የዴሞግራፊና የጂኦግራፊ ለውጥ በምንም መልኩ ሕጋዊ፣ ሞራላዊ፣ ፖለቲካዊና ታሪካዊ ተቀባይነት የሌለው መሆኑን እንገልፃለን። አገዛዙ ''አገራዊ ምክክር'' በሚል የፖለቲካ ሽፋን በከተማዋ ላይ የሚያካሄደው ሴራና አሻጥር የከተማዋን ነባር ኗዋሪዎች መብት የሚጥስ፣ የሁሉም ኢትዮጵያዊያን የጋራ መኖሪያነቷን የሚክድና ታሪካዊ እውነታውን ለማዛባት የተሸረበና የአንድ ቡድን የበላይነትን በህዝባችን ላይ በኃይል ለመጫን ያለመ በመሆኑ፣ የዚህን አምባገነን አገዛዝ ዕድሜ ለማሳጠር መላው የአዲስ አበባ ከተማ ኗዋሪዎችን ጨምሮ ኢትዮጵያውያን ድርጊቱን እንዲያወግዙት፣ እንዲቃወሙትና እንዲታገሉት በድርጅታችን አፋብን ስም ጥሪ እናቀርባለን። እንዲሁም በከተማዋ ቀደም ብለው ይኖሩ የነበሩትም ይሁን አሁንም የሚኖሩት 80 በመቶ ( በ1999 ዓ.ም በተካሄደው ህዝብና ቤት ቆጠራ መሰረት) የሚሆኑት ነባር ኗዋሪዎች አማራዎች ናቸው። በመሆኑም የህዝብ ስብጥርንም ሆነ ታሪካዊ እውነታን በኃይልና በተሳሳተ ፖለቲካዊ ውሳኔ ለመቀየር የሚደረገውን ማንኛውም የአገዛዙን ሴራ አጥብቀን የምንታገለው መሆኑን እንገልፃለን። የአማራ ህዝብ በገዛ አገሩ ከገጠመው ሁለንተናዊ የህልውና አደጋ ባሻገር ድርጅታችን የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) የትጥቅ ትግል ውስጥ ለመግባት ካስገደዱት ምክንያቶች መካከል፦ በአዲስ አበባ ከተማ በአገዛዙ የተደቀነው የዴሞግራፊ ለውጥ አደጋ፣ የከተማዋን ቀደምት ባለቤቶችና ነባር ኗዋሪዎች በማፈናቀልና ማንነታቸውን በማጥፋት፣ የአማራ ህዝብ ከከተማዋ ጋር ያለውን ታሪካዊ እና ማህበራዊ ትስስር በመበጣጠስ ከህዝቦች ተፈጥሯዊ መስተጋብር ውጭ በሆነ መልኩ የባህል፣ የቋንቋና የተለያዩ አመለካከቶችን በኃይል ለመጫን የሚደረገው ሩጫ ይገኝበታል። በመሆኑም፣ ድርጅታችን አፋብን ከምንጊዜውም በላቀ ሁኔታ ውስጣዊ አንድነቱንና አደረጃጀቱን ጠብቆ በመጓዝ፣ አምባገነኑና ከፋፋዩን አገዛዝ በጀመርነው ትግል ከስሩ ነቅለን በመጣል፣ ለአማራ ህዝብ ብሎም ለሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚስማማ፣ የዜጎችን ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች የሚያከብር ሥርዓተ መንግስት በመገንባት ፍትህ፣ እኩልነትና የሕግ የበላይነትን ከመትከል ባሻገር አዲስ አበባ የኗዋሪዎቿ፤ የሁሉም ኢትዮጵያዊያን የጋራ መኖሪያና ዋና ከተማ፤ የአንድነትና የእድገት ማዕከል ሆና እንድትቀጥል ይታገላል። አገሪቱ ከገባችበት ጥልቅ የህልውና፣ የፍትህና የእኩልነት ቀውስ መውጣት የምትችለው የህዝቧን ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች በኃይል በማፈን፣ አገሪቱን የማያቋርጥ እርስ በእርስ ጦርነት ውስጥ በማስገባት ወደ ገደል እየመራት ያለውን ዘረ ፈጁን የብልፅግና አገዛዝ፤ በሕዝባዊ ትግል ሙሉ በሙሉ መገርሰስ ሲቻል ብቻ መሆኑን አፋብን በፅኑ ያምናል። በስተመጨረሻ የኦህዴድ ብልፅግና አገዛዝ በአዲስ አበባ ከተማና በህዝባችን ላይ በምክክር ስም የጠነሰሰው ዓይን ያወጣ የፖለቲካ አሻጥር የፈጠረው የህልውና በድርጅታችን ቁርጠኝነት፣ በህዝባችን ፅናትና በፀረ ብልፅግና ብሔራዊ ኃይሎች ትብብር በሚታጀበው የትግላችን አይቀሬ ድል የሚመመከት ይሆናል። የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን)

ነሐሴ 09/2018 ዓ.ም የአገዛዙ ጦር በመፍረስ የአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ 206ኛ ከፍያለው ደሴ ኮር ገብርዬ  እና ጀኔራል ኃይሌ ዘ ውባንተ ክፍለ ጦርን ​እየተቀላቀለ ይገኛል ! የአማራን ህዝብ ማህበረ ፖለቲካ ስሪትን ለማጥፋት ቀን ከሌት የሚሰራው የብልጽግናው ስርዓት ባለፉት ሶስት ዓመታት ሁሉንም ፀረ ህዝብ ስራዎችን ሰርቷል። ስለሆነም እራሱን በታሪክ ምዕራፍ ውስጥ  ለማቆየት በስርዓቱ ላይ ያነጣጠረ ትግል ላይ እሚገኘው የአማራ ህዝብ ከውጊያ ባሻገር ስቦ በማስከዳት የዕዝ ሰንሰለቱን  በማፍረስ ላይ ነው። ስለሆነም በተከታታይ ሁለት ቀናት የአገዛዙ  መከላከያ እና አድማ ብተና አባላት  አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ 206ኛ ከፍያለው ደሴ ኮር ገብርዬ ክፍለ ጦር እና ጀኔራል ኃይሌ ዘ ውባንተ ክፍለ ጦርን ተቀላቅለዋል። 1.​ማሩ ይግዛው  2.አሻግረው ፈንታ 3.ዝናቤ መልኬ 4.ወርቁ ሲሳይ 5. ብሩክ አዝመራው ​ሲሆኑ ​ክፍለ ጦሮቹም ወታደራዊ ሥነ-ምግባርን የተከተለ መንገድ አቀባበል አድርገውላቸዋል። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!ዠ

ከአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ ዕዝ ለመላው ደጋፊ ሕዝባችን የተላለፈ ጥብቅ ማሳሰቢያ! ​ከተቋማችን አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ ዕዝ እውቅና ውጭ በኮሮች እና በክፍለ ጦሮች ስም በተለያዩ ከተሞች ድጋፍ እየተጠየቀ መሆኑን አረጋግጠናል። ​በከፍተኛ የሕዝብ ድጋፍ እስካሁኗ ሰዓት ድረስ የዘለቀውን ትግላችንን ለማደናቀፍ የሚንቀሳቀሱ ቡድኖች ፣ ከዕዛችን እውቅና ውጭ በተለያዩ ከተሞችና ቀጣናዎች ድጋፍ እየጠየቁ መቆየታቸውን ከተለያዩ ምንጮቻችን አረጋግጠናል። ​ስለሆነም ዕዛችን እስካሁን ያዋቀረው ምንም ዓይነት የድጋፍ አሰባሰቢ ኮሚቴም ሆነ ግብረ-ኃይል እንደሌለ ለመላው ሕዝባችን እና ደጋፊያችን እያሳወቅን ፣ በዚህ ሕገ-ወጥ ድርጊት ላይ የተሰማራችሁ ቡድኖችና ግለሰቦች ከድርጊታችሁ እንድትቆጠቡ እናሳስባለን። ​በመሆኑም አስፈላጊ የሆኑ የድጋፍና የትብብር ጥሪዎች ሲኖሩ፣ ጥያቄው በቀጥታ እና ይፋዊ በሆነ መንገድ በዕዛችን በኩል የሚቀርብ ይሆናል። ስለሆነም መላው ደጋፊያችንና ህዝባችን ከይፋዊ የዕዛችን ዕውቅና ውጭ የሚደረጉ ማናቸውንም የድጋፍ ጥሪዎች ባለመቀበል ግዴታችሁን እንድትወጡ አጥብቀን እናሳስባለን። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! ​አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ ዕዝ

የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን)--ወታደራዊ የግንባር አውደ-ውሎ እና የህዝብ አደረጃጀት መረጃዎች፦      ነሐሴ 9/2018 ዓ.ም። ​፩. የአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ሰራዊት በጎንደር ግንባር የፈጸመው አመርቂ ድል፦ ​የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ስር የሚገኙት ዞብል፣ ጃኖ እና በጌምድር ክፍለ ጦሮች ባካሄዱት የተቀናጀ ኦፕሬሽን በጠላት የሰው ኃይል እና ወታደራዊ ቁሳቁስ ላይ ከፍተኛ ኪሳራ አደረሱ። ​መዳረሻውን ጨውድባ አድርጎ ሲንቀሳቀስ የነበረው እና በህዝብ ላይ በደል ሲፈጽም የቆየው የጠላት ኃይል፤ ይዞታውን ለማስፋት በማሰብ ከምዕራብ ደንቢያ ጫዊት፣ ከደልጊ ጣቁሳ ወረዳ፣ ከጭልጋ ከተማ እና ከጫንድባ ያደረገው እንቅስቃሴ በሁለቱ ክፍለ ጦሮች የተቀናጀ የመልሶ ማጥቃት እርምጃ “ጫንድባ አምባተራራ” ላይ ከፍተኛ ምት አርፎበታል። ​በጫንድባ አምባተራራ የደረሰበትን የከፋ ምት መቋቋም የተሳነው የጠላት ስብስብ በሌላኛው አውደ ውጊያ በኳክ አቅጣጫ ተጨማሪ የማጥቃት ሙከራ ለማድረግ ቢሞክርም፣ በክፍለ ጦሮቹ በተናበበና በተደራጀ አፀፋዊ ምት ከፍተኛ ኪሳራ ደርሶበታል። ​፪. የፋሽስቱ አገዛዝ ሰራዊት አባላት እየፈረሱ ፋኖን እየተቀላቀሉ ነው። ​የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ወሎ ጠቅላይ ግዛት ሚኒሊክ ዕዝ 101ኛ ኮርን የጠላት አገዛዝ ሠራዊት አባላት እየፈረሱ በመቀላቀል ላይ ይገኛሉ። ​በዚህም መሰረት፡- ✔️የ47ኛ ክፍለ ጦር አምስተኛ ሻለቃ አባል አንድ ጥቁር ክላሽ ከ200 የክላሽ ተተኳሽ ጋር፣ ✔️የ45ኛ ክፍለ ጦር አምስተኛ ሻለቃ ሁለት አባላት ሁለት ጥቁር ክላሽ፣ 240 የክላሽ ተተኳሽ እና አምስት F1 ቦንቦች፣ ✔️የ46ኛ ክፍለ ጦር አንደኛ ሻለቃ የሻለቃ አመራሩ አጃቢ 110 የክላሽ ተተኳሽ፣ አንድ ጥቁር ክላሽ እና የሻለቃውን የመገናኛ ሬድዮ በመያዝ 11ኛ እና 15ኛ ክፍለ ጦሮችን ተቀላቅለዋል። ​በአጠቃላይ ከ45ኛ፣ 47ኛ እና 46ኛ ክፍለ ጦሮች አፋብን ወሎ ጠቅላይ ግዛት ሚኒሊክ ዕዝ 101ኛ ኮርን፡- • ​4 ጥቋቁር ክላሾች • ​550 የክላሽ ተተኳሾች • ​5 የF1 ቦንቦች • ​1 የመገናኛ ሬድዮ ይዘው መቀላቀላቸውን የ101ኛ ኮር ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ አስታውቋል። ​፫. በሰሜን ወሎ ዞን የመቄት ወረዳ ጊዜያዊ ሕዝብ አስተዳደር ተዋቀረ ​የአማራ ሕዝብ የገጠመውን የህልውና አደጋ ለመቀልበስ እና አስተዳደራዊ ፍትሕ ለማስፈን በሚደረገው ፖለቲካዊ የትጥቅ ትግል መዋቅራዊ ስራዎችን ማጠናከር ተችሏል። በዚህም መሰረት በአፋብን ወሎ ጠቅላይ ግዛት ምኒልክ ዕዝ እና በሰቆጣ/መቄት አደረጃጀት ኃላፊዎች ሰፊ ውይይት ተደርጎ የመቄት ወረዳ ጊዜያዊ ሕዝብ አስተዳደር የሚከተለው መዋቅር ተዘርግቷል፦ ~1ኛ. ዋና አስተዳዳሪ፡ 50/አ መንግስቱ ካሳ ~2ኛ. ም/አስተዳዳሪ፡ ምስጋን ዘውዱ ~3ኛ. የፖለቲካ ጉዳዮች መምሪያ፡ ኢ/ር አበባው ተስፋው ~4ኛ. ሰላምና ደህንነት መምሪያ፡ 100/አ በጊዜው ታደሰ ~5ኛ. ማህበራዊ ጉዳዮች መምሪያ፡ ሳሙኤል አያሌው ~6ኛ. ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ፡ አንተነህ አምሳሉ ~7ኛ. መረጃና ደህንነት መምሪያ፡ ኮስትር (እሚያምረው) ~8ኛ. ፋይናንስ መምሪያ፡ ውበት እባቡ ~9ኛ. ሎጅስቲክስ መምሪያ፡ አለበል መኩሪያው ~10ኛ. ወጣቶች ጉዳይ መምሪያ፡ ጌታሁን ቢሰጥ ~11ኛ. ም/ሎጅስቲክስ መምሪያ፡ ንጋት ሙጨ ~12ኛ. ም/ሰላምና ደህንነት መምሪያ፡ ቢራራ ፀጋነው ~13ኛ. ሕግ መምሪያ ዋና ዳኛ፡ መንግስቱ ያለው ~14ኛ. ሕግ ክፍል ጸሐፊ፡ መርሻ መልካም ~15ኛ. ሕግ ክፍል አባል፡ አዳነ መንግስቴ ~16ኛ. ሕግ ክፍል ገንዘብና መዝገብ ያዥ፡ ዮርዳኖስ ጫኔ ~17ኛ. ሴቶች ጉዳይ መምሪያ፡ ማህሌት አስናቀ ​የአማራ ሕዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል...... ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!! ​የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) የወታደራዊ ቃል አቀባይ

በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ 1ኛ ምኒልክ ዕዝ የሰሜን ወሎ ዞን መቄት ወረዳ ጊዜያዊ ሕዝብ አስተዳደር መልሶ የማደራጀት ስራ ተሰራ...! ሕዝባችን የአማራ ሕዝብ እንደ ሕዝብ የገጠመውን የህልውና አደጋ ለመቀልበስ በሚደረገው ፖለቲካዊ የትጥቅ ትግል ሕዝብን አስተባብሮ እና ሕዝቡ የትግሉ ባለቤት መሆኑን ተገንዘቦ እንዲታገል ለማድረግ እንዲሁም  ሕዝብም አስተዳደራዊ ፍትሕ እንዲያገኝ የሕዝብ አስተዳደር መዋቅር መዘርጋትና ማደራጀት ዕዛችን 1ኛ ምኒልክ ዕዝ አበክሮ እየሰራ ይገኛል። በመሆኑም በሰሜን ወሎ ዞን የመቄት ወረዳ ጊዜያዊ ሕዝብ አስተዳደርን በተጓደሉ እና በተሻሻሉ መምሪያዎች የሚያስፈልገውን የሰው ኃይል በመሙላት ትግሉ እና የመቄት ወረዳ ሕዝብ በሚፈልገው ልክ መልሶ የማደራጀት ስራ ተሰርቷል። መዋቅራዊ ስራዎችን የአፋብን 1ኛ ምኒልክ ዕዝ አደረጃጀት መምሪያ ኃላፊ አርበኛ አሰፋ መሰለ ፣ የዕዙ ም/ሕዝብ አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ አርበኛ መምህር ጋሻው ሙሉጌታ ፣ የ303ኛ ኮር ፖለቲካ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ መምህር በሪሁን ደምሌ እና አደረጃጀት መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ጋሻው አበበ እንዲሁም የ16ኛ ኮር ፖለቲካ መምሪያ ኃላፊ መምህር መኩሪያ አጋዥ እና የአደረጃጀት መምሪያ ኃላፊ አርበኛ አወቀ ብዙአየሁ በጋራ ሰፊ ውይይት በማደርግ ያዋቀሩ ሲሆን  ዝርዝር ስማቸው እና ኃላፊነታቸው ከዚህ በታች ተገልፀዋል። 1ኛ.ዋና አስተዳዳሪ:-50/አ መንግስቱ ካሳ 2ኛ.ም/አስዳዳሪ:-ምስጋን ዘውዱ 3ኛ.የፖለቲካ ጉዳዮች መምሪያ:-ኢ/ር አበባው ተስፋው 4ኛ.ሰላምና ደህንነት መምሪያ:-100/አ በጊዜው ታደሰ 5ኛ.ማህበራዊ ጉዳዮች መምሪያ:-ሳሙኤል አያሌው 6ኛ.ህዝብ ግንኙነት መምሪያ:-አንተነህ አምሳሉ 7ኛ.መረጃና ደህንነት መምሪያ:-ኮስትር(እሚያምረው) ከአመት በፊት ቆስሎ በቤት ያለ። 8ኛ.ፋይናስ መምሪያ:-ዉበት እባቡ 9ኛ.ሎጅስቲክ መምሪያ:-አለበል መኩሪያው 10ኛ.ወጣቶች ጉዳይ መምሪያ:-ጌታሁን ቢሰጥ 11ኛ.ም/ሎጀስቲክ መምሪያ:-ንጋት ሙጨ 12ኛ.ም/ሰላምና ደህንነት መምሪያ:-ቢራራ ፀጋነው 13ኛ.ህግ መምሪያ ዋና ዳኛ:-መንግስቱ ያለው 14ኛ.ህግ ክፍል ጸሀፊ:-መርሻ መልካም 15ኛ.ህግ ክፍል አባል:-አዳነ መንግስቴ 16ኛ.ህግ ክፍል ገንዘብና መዝገብ ያዥና:-ዮርዳኖስ ጫኔ 17ኛ. ሴቶች ጉዳይ መምሪያ:- ማህሌት አስናቀ በማድረግ ተዋቅሯል መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ወሎ ቤተአማራ ምኒልክ ዕዝ  ህዝብ ግንኙነት መምሪያ! ነሐሴ 09/2018 ዓ.ም

የአደረጃጀት ዜና ነሐሴ 09/2018 ዓ.ም አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር ጣና ገላውዲዎስ ክፍለ ጦር ላለፉት ሶስት ተከታታይ ቀናት ሲያካሂድ የቆየውን ጥልቅ ወታደራዊና ፖለቲካዊ የግምገማ መድረክ በስኬት በማጠናቀቅ አጠቃላይ የመዋቅርና የአደረጃጀት ሪፎርም ማድረጉን ይፋ አድርጓል። ከታሪካዊው የጎንደር አንድነት ማግስት ጀምሮ የሰራዊቱን ወታደራዊ ዝግጁነት ከማሳደግ ባሻገር ህዝባዊ ደጋፍ መሰረቱን በማጠናከር ረገድ በርካታ ውጤታማ ስራዎችን ሲያከናውን የቆየው ኮሩ ፣ የአሁኑ አደረጃጀታዊ ሽግግር የትግል ጉዞውን ወደ ላቀ የስልታዊና የተግባር ብቃት ደረጃ ለማሸጋገር ያለመ ስራ ሰርቷል ። ​ይህ ከፍተኛ የግምገማና የስራ አመራር መድረክ የዕዝ፣ የኮርና የክፍለ ጦር ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች በተገኙበት የተካሄደ ሲሆን፣ በቆይታውም የሰራዊቱን ያለፉት ጊዜያት ኦፐሬሽናል እንቅስቃሴዎች፣ የውጊያ ብቃት፣ የአመራር ድክመቶችና ጥንካሬዎች በዝርዝርና በግልጽነት ተገምግሟል። በመድረኩ በተካሄደው ጥልቅ ሂስና ግለ-ሂስ መሰረት፣ ክፍለ ጦሩን በቀጣይነት ለላቀ ወታደራዊ ድል የሚያዘጋጁና የትግሉን ህዝባዊ አላማ በጽናት የሚያስፈጽሙ ብቁ አመራሮችን በጥብቅ መስፈርት በማወዳደር የመለየትና አዲስ የስራ ኃላፊነት የመስጠት ስራ ተከናውኗል። ​በዚሁ የመዋቅር ማሻሻያ መሰረት ባለፉት የትግል ዓመታት በወታደራዊ ስትራቴጂካዊ ልምዳቸው፣ በፖለቲካዊ ብስለታቸው፣ በውጊያ ሜዳ መሪነታቸው፣ በከፍተኛ የስነ-ምግባር አርአያነታቸውና በትግል ጽናታቸው የላቀ አፈጻጸም ያሳዩ አመራሮች ወደ ፊት እንዲመጡና ክፍለ ጦሩን በበላይነት እንዲመሩ መድቧል። ​​በመሆኑም:- 1.​አርበኛ ክንዳለም መለሰ == ዋና ሰብሳቢ 2.​አርበኛ ዘመኑ ገብሬ (ባበይ ) == ምክትል ሰብሳቢ 3.​አርበኛ ሙሉቀን ሲሳይ ==ዋና ወታደራዊ አዛዥ 4.​አርበኛ ፀዳሉ አበበ ==ምክትል ወታደራዊ አዛዥ 5.​አርበኛ ፈለቀ ካሳሁን == ዋና ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ 6.​አርበኛ ውበቱ ሞላ == ምክትል ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ 7.​አርበኛ አዳነ ማተቤ == ፖለቲካ መምሪያ ኃላፊ 8.​አርበኛ ፍቅሩ ባየ ==ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ 9.​አርበኛ አሳፈው ሞሀበው = ወታደራዊ አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ 10.​አርበኛ አብርሃም አምበሉ == ጽህፈት ቤት ኃላፊ 11.​አርበኛ አንሙት ዋለልኝ == ፋይናንስ መምሪያ ኃላፊ 12.​አርበኛ በላይ አማረ == ሎጂስቲክስ መምሪያ ኃላፊ 13.​አርበኛ ታደለ ምሬ ==ስልጠና መምሪያ ኃላፊ 14.​አርበኛ ጌታቸው ባየ == አደረጃጀት መምሪያ ኃላፊ 15.​አርበኛ መብሬ ደጀን ==ህዝብ አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ 16.​አርበኛ በቀለ በላይ ==ቀጠናዊ ትስስር መምሪያ ኃላፊ 17.​አርበኛ መምህር ፈንታሁን ገብሬ== ግዥ መምሪያ ኃላፊ 18.​አርበኛ ንጉስ ገላው== የሰው ኃይል መምሪያ ኃላፊ 19.​አርበኛ ደፋሩ አረጋ ==ኦርዲናንስ መምሪያ ኃላፊ 20.​አርበኛ ቴዎድሮስ አስፋው == ኦዲትና ቁጥጥር መምሪያ ኃላፊ 21.​አርበኛ አማን ዋሴ == ጤና መምሪያ ኃላፊ 22.​አርበኛ መልኬ ደስታ ==** 23.​አርበኛ ውብድል ካሴ – ህግ እና ስነ-ምግባር መምሪያ ኃላፊ ሆነው ተወድበዋል ሲል መረጃውን ያደረሰን የክፍለ ጦሩ ህዝብ ግንኙነት ነው። ​ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! ​አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!

የጅሁር ወጣት አመረረ! - የራስ አበበ አረጋይ የመንፈስ ልጆች

ዱርቤቴ ከተማ ታላቅ ድል ነሀሴ 9/2018ዓ.ም የአፋብን ቴዎድሮስ እዝ 105ተኛ ኮር 55ተኛ ክ/ጦር ቃኝ እና መሀንዲስ ወደ ዱርቤቴ ከተማ አስተዳደር ሰርጎ በመግባት ልዩ ስሙ ጁፊ ባታ ላይ በእንቅስ
+1
ዱርቤቴ ከተማ ታላቅ ድል ነሀሴ 9/2018ዓ.ም የአፋብን ቴዎድሮስ እዝ 105ተኛ ኮር 55ተኛ ክ/ጦር ቃኝ እና መሀንዲስ ወደ ዱርቤቴ ከተማ አስተዳደር ሰርጎ በመግባት ልዩ ስሙ ጁፊ ባታ ላይ በእንቅስቃሴ ላይ በነበረ የአረጋ ከበደ መንበር አርጠባቂ ሚኒሻ እና አድማ ብተና ላይ በወሰደው የደፈጣ እርምጃ በአንድ ሲኖ ትራክ መኪና ተጭነው ሲንቀሳሱ የነበሩ የmላት አባት ሙሉ በሙሉ ተደምስሰዋል ። በዚህም አንድ ብሬን ከ 20 በላይ ክላሽ እና የቃታ መሳሪያ መማረክ የተቻለ ሲሆን ዱርቤቴ ሆስፒታል በዚህ ሰአት በkuስለኛ ተጥለቅልቋል ። ውጊያውን የ55ተኛ ክ/ጦር ዘመቻ ሀላፊ አርበኛ ስላባት አቤ በታላቅ ጀግንነት መርቶታል ። ምስጌ ዘድንግል

የጥንቃቄ መልእክት ለ201ኛ ክ/ እና ለ64ኛ ክፍለ ጦር ቴዎድሮስ ዕዝ ​በድሮማ እና በአካባቢው በሚገኙ የ64ኛ ክፍለ ጦር የመንቀሳቀስ ቀጠናዎች ላይ የአገዛዙ ኃይል ጥቃት ለማድረግ ዝግጅት እያደረገ
የጥንቃቄ መልእክት ለ201ኛ ክ/ እና ለ64ኛ ክፍለ ጦር ቴዎድሮስ ዕዝ ​በድሮማ እና በአካባቢው በሚገኙ የ64ኛ ክፍለ ጦር የመንቀሳቀስ ቀጠናዎች ላይ የአገዛዙ ኃይል ጥቃት ለማድረግ ዝግጅት እያደረገ መሆኑ ስለተመለከተ፥ በቀጠናው የሚገኙ ሁሉም የወገን ኃይሎች ሊንከባለል የሚችልን ማንኛውንም ግብአት ለመከላከል እና የአካባቢውን ደህንነት ለማክበር ከወዲሁ ከፍተኛ ተጠንቀቅ ላይ እንዲቆሙ፤ የቅኝት ስራዎችን በማጠናከርና የመረጃ ልውውጥን በመቃኝት አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት ሁሉ አጠናቀው እንዲጠብቁ መረጃውን አዘውትሩ። ​09/12/2018 ዓ. ም

የፋሽስቱ አገዛዝ የ45ኛ የ46ኛ እና የ47ኛ ክፍለ ጦር አባሎች እየፈረሱ ፋኖን እየተቀላቀሉ ነዉ። የአገዛዙ ሰራዊት አባሎች እየፈረሱ የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄ(አፋብን) ወሎ ቤተ አምሓራ ሚኒሊክ
+3
የፋሽስቱ አገዛዝ የ45ኛ የ46ኛ እና የ47ኛ ክፍለ ጦር አባሎች እየፈረሱ ፋኖን እየተቀላቀሉ ነዉ። የአገዛዙ ሰራዊት አባሎች እየፈረሱ የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄ(አፋብን) ወሎ ቤተ አምሓራ ሚኒሊክ ዕዝ 101ኛ ኮርን እየተቀላቀሉ ይገኛሉ። የ47ኛ ክፍለ ጦር አምስተኛ ሻሐቃ አባል አንድ ጥቁር ክላሽ ከ200 የክላሽ ተተኳሽ ጋር በመያዝ እና ከ45ኛ ክፍለ ጦር አምስተኛ ሻለቃ ሁለት አባሎች ሁለት ጥቁር ክላሽ፣240የክላሽ ተተኳሽ እና አምስት F1 ቦንብ በመያዝ 101ኛ ኮር 15ኛ ክፍለጦርን ሲቀላቀል የ46ኛ ክፍለ ጦር የአንደኛ ሻለቃ የሻለቃ አመራሩ አጃቢ 110 የክላሽ ተተኳሽ አንድ ጥቁር ክላሽ እና የሻለቃውን የመገናኛ ሬድዮ በመያዝ 11ኛ ክፍለጦርን ተቀላቅለዋል። በአጠቃላይ ከ45ኛ፣ከ47ኛ እና 46ኛ ክፍለ ጦሮች አፋብን ወሎ ቤተ አምሓራ ሚኒሊክ ዕዝ 101ኛ ኮርን አራት(4) ጥቋቁር ክላሽ ሶስት መቶ አስር(550)የክላሽ ተተኳሽ አምስት F1 ቦንብ አንድ(1) የመገናኛ ሬድዮ በመያዝ ተቀላቅለዋል ሲል 101ኛ ኮር ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ መረጃዉን አድርሷል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!! ነሀሴ 09/2018 ዓ.ም