ch
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

前往频道在 Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

显示更多
2 921
订阅者
-124 小时
+1487 天
+38530 天
帖子存档
የአብይ አህመድ ኮሎኔሎች በአማራ ህዝብ ላይ የሚፈፅሙት ሁለንተናዊ ጦርነት ነው። በጅምላ ጨራሽ መሳሪያ ከሚጨፈጭፉት ጎን ለጎን እናቶችን እና ልጃገረዶችን አስገድደው በመድፈር እየፈፀሙት ያለው የጦር
የአብይ አህመድ ኮሎኔሎች በአማራ ህዝብ ላይ የሚፈፅሙት ሁለንተናዊ ጦርነት ነው። በጅምላ ጨራሽ መሳሪያ ከሚጨፈጭፉት ጎን ለጎን እናቶችን እና ልጃገረዶችን አስገድደው በመድፈር እየፈፀሙት ያለው የጦር ወንጀል በብዙ መልኩ ያልተነገረ ነው። ዛሬ ደጋ ዳሞት ላይ የተሸኘው ኮሎኔል አበራ ከእጅ ስልኩ ከተገኘው ምስል ማረጋገጥ እንደሚቻለው በዚህ መልኩ ንፁሃንን ያዋርዳሉ። እነኝህን አለመታገል እንዴት ይቻላል። በዚህ ውጊያ አንድ የክፍለ ጦር አዛዥ፣ አንድ የኮሎኔል ማዕረግ ያለው የስታፍ አባል እና ሁለት ሻለቃ መሪዎች ይገኙበታል።

#ቴዎድሮስ_ዕዝ_በውሎው‼️ ሀ #የደጋዳሞት_ተጋድሎ_እና_ድል! ከጥዋቱ ጀምረን በተለያየ ስዓት የተለያየ መረጃ ሰናደርስ መቆየታችን ይታዎሳል አሁን ጠቅለል ያለ መረጃ ደርሶናል እንደሚከተለው እንዘግባልን በውጊያ የተሳተፉ የክ/ጦሮች 24ኛ ክ/ጦር ከስናን 54 ኛ ክ/ጦር እና 99ኛ ክ/ጦር ደጋ ዳሞት ሻለቃ የተሳተፉ ሲሆን የተገኙ ድሎች 1. ሁለት ኮረኔል አበረ እና ኮረኔል ፍቃዱ የተደመሰሱ እስከ ሙሉ አጃቢዎቻቸው 2. ሦስት የሻለቃ አመሪሮች እስከ አጃቢዎች  የተደመሰሱ 3. በርካ እግረኛ ሰራዊት የተደመሰሰ 4. አንድ 82 ሚሊ ሞርተር የተማረከ  እና ምድብተኛው የተደመሰሰ 5. ሁለት ድሽቃ አንዱ ባለ ክሻፋው 6. 8 ብሬን 7. 4 እስናይፕር  8. በመጠን ያልተቆጠረ ክላሽ እና ቁጥሩ ያልታወቀ ተተኳሽ! 9.  አንድ ፲ አለቃ እና በርካታ እግረኛ ተማርኳል። 10. መገናኛ ረዲኦ እና የጦር ሜዳ መነፀር 11. ሁለት እስታር ሽጉጥ ኮረኔል አበረ በሰከላ ወረዳ ከ20 በላይ ወጣቶችን ከብት ከሚጠብቁበት በመሰብሰብ ትምህርት ቤት በማጎር አንጋሎ በማረድ እና ምላሳቸውን በማውጣት በጭካኔ የቆረጠ አረመኔ ነበር። በተመሳሳይ ተማሪ ቃል ኪዳን አስገድዶ በመድፈር ሚስጢሩ እንዳይወጣ አንቆ የገደለ በአማራ ጥላቻ ያበደ የአብይ አሕመድ ቀኝ እጅ ነው በዚህ ውጊያ የተደመሰሰ።   ለ. #ብር_አዳማ_እና_ቋሪት_ገበዘማርያም ትንቅንቅ!    102ኛ ኮር 11ኛ ክፍለጦር እና 33ኛ ክፍለጦር የብር አዳማን ጠላት በመክበብ እና በማስጨነቅ ወደ ቋሪት ጓዙን ጥሎ እንዲፈረጥጥ አድርገውታል። ተከትለው ቋሪት ድረስ በመዝለቅ ከተመዋን በመቆጣጠር ጠላትን እያስጨነቁ አምሽተዋል።    በሁሉም ግንባር ያለ ጠላት መሄጃውን እየመቻቸ ይገኛል። በዚህ ምት የደነገጠው ጠላት ከእቅዱ በተቃራኒ ስለሆነበት ሙሉ ቀጠናውን ለመልቀቅ እየተገደደ ይገኛል። አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ ፣ አዲስ ተስፋ!   ©ቴዎድሮስ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ !   ሰኔ 19/2018ዓ.ም

የ206ኛ ከፍያለው ደሴ ኮር ገብርዬ ክፍለ ጦር ጥልቅ ውይይት አደረገ!!! የ206ኛ ከፍያለው ደሴ ኮር ስራ አስፈጻሚዎች በተገኙበት ገብርዬ ክፍለ ጦር ባደረገው ውይይት የግዳጅ አፈጻጸምን ፣​የሰራዊት
+3
የ206ኛ ከፍያለው ደሴ ኮር ገብርዬ ክፍለ ጦር  ጥልቅ ውይይት አደረገ!!! የ206ኛ ከፍያለው ደሴ ኮር ስራ አስፈጻሚዎች በተገኙበት ገብርዬ ክፍለ ጦር ባደረገው ውይይት  የግዳጅ አፈጻጸምን ፣​የሰራዊት ውስጣዊ አንድነትን በተመለከተ፣ ቀጠናዊ አንድነትን በተመለከተ እና የክፍለ ጦሩ አባላትና አመራሮች የተጣለባቸውን ወታደራዊ ግዳጅ በላቀ ብቃት ስለመወጣት  ሰፊ ውይይት አድርጓል። ተቋማዊ  ውይይቱ ​ለላቀ ወታደራዊ ዝግጁነትና ቁርጠኝነት፣ ክፍለ ጦሩ በማንኛውም ሰዓትና ወቅታዊ ሁኔታ የሚሰጡትን ተልዕኮዎች በውጤታማነት ለመወጣት የሚያስችል ሙሉ የአካል፣ የስነ-ልቦና እና የትጥቅ ዝግጁነትን በተመለከተ ጠንካራ ውይይት ተደርጎበታል። ​ይህ በእንዲህ እንዳለ  ውስጣዊ አንድነት ​የማንኛውም ወታደራዊ ስኬት ምስጢር በጠንካራ ውስጣዊ አንድነት በመሆኑ፣ በውይይቱ ወቅት ለዚህ ትልቅ ትኩረት ተሰጥቶት ​የአመራርና የሰራዊት መናበብ ፣ከአመራር እስከ ታችኛው የሰራዊት አባል ድረስ ያለው ግንኙነት በግልጽነት፣ በጋራ መከባበርና በጠንካራ ወታደራዊ ዲሲፕሊን ላይ የተገነባ  ሊሆን ይገባል በሚል አጽዕኖት ተሰጥቶት መድረኩ ተጠናቋል። ​ ድል ለአማራ ህዝብ !!! ድል ለአማራ ፋኖ !!! የ206ኛ ከፍያለው ደሴ ኮር ቃል አቀባይ ክፍል!!!

ከሠም ፪ኛ ኮር ነበልባል ክፍለ ጦር መብረቁ ሻለቃ በየረርና ከረዩ አውራጃ ኢራቡቲ ቀበሌ ላይ ድል ተቀዳጄ።               ሰኔ 19/10/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ከሠም ፪ኛ ኮር ነበልባል ክፍለ ጦር መብረቁ ሻለቃ በብልፅግናው ጥምር ጦር ላይ ታላቅ ገድል ፈፅሟል። ከምንጃር ሸንኮራ በኩል ተንቀሳቅሶ በዙ-23 ፣በሞርተር እና በድሽቃ ሽፋን እየሰጠ ወደ እራንቡቲ ቀበሌ ለመግባት እና  የነበልባል ክፍለ ጦር መብረቁ ሻለቃን ለማፈን የተንቀሳቀሰው የጠላት ኃይል ክፉኛ ተመቷል። በዚህ እልህ አስጨራሽ  አውደ ውጊያ የጠላት ከባድ መሳሪያ ዙ-23 በፋኖ ዶሽቃ በመመታቱ ወደ ኃላ ይዞ ለመመለስ ተገዷል። በመሸነፉ ክፉኛ የተበሳጨው የብልፅግናው አሽከር  አፀፋውን  ወደ ንፁሀንን አዙሯል። በዚሕም በዶሽቃዎቹና በሞርተሮቹ  የንፁሀንን  መንደር በመደብደብ በሰባት ግለሰቦች ላይ ጉዳት አድርሷል። ከተጎጅዎች መካከል 1.ስንታየሁ  አጥላው 2. ኃይለመሥቀል አጥላው 3.አባተ ተፈራ 4.ዘበናይ ካሳ 5.ሰብለ ሽመልሥ 6.አንዷለም አለሙ 7.አብርሃም ኃ/ሚካኤል የተባሉ  7 ግለሰቦች ሲሆኑ  ስንታየሁ የተባለው ግለሰብ በከፍተኛ መጎዳቱንና ለህይወቱ አስጊ ደረጃ ላይ መሆኑን የአካባቢው  ማሕበረሰብ  መረጃውን አድርሰውናል።    "ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!! የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

የ81ኛ ክፍለ ጦርን ብርቱ ክንድ መቋቋም ያቃተው የብልፅግና ሰራዊት ወደ ነበረበት መደበቂያው ፈርጥጦ ተመለሰ! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር ክንፍ የሆነው 81ኛ ክፍለ ጦር መቄት ወረዳ ወደ ደብረ ዘቢጥ ከተማ ሲንቀሳቀስ የነበረውን የአገዛዙ ሰራዊት ላይ ጥቃት በመፈፀም ሙትና ቁስለኛውን ይዞ ወደ መጣበት እየተዝረከረከ እንዲመለስ አድርገውታል። ሰኔ 19 ቀን 2018 ዓ/ም መነሻውን ከመቄት ወረዳ መቀመጫ ፍላቂት በማድረግ መዳረሻውን ደብረ ዘቢጥ ከተማ ለማድረግ የተንቀሳቀሰው የብልፅግና ሰራዊት ከቦታው ሳይደርስ መሐል ላይ በመቁረጥ ቅፅበታዊ ጥቃት አድርሰውበታል። በዚህ አውደ ውጊያ የሚሊሻ ሻምበል መሪውን ጌታ ገበየሁን ጨምሮ ስድስት ሆድ አደር ሚሊሻና አምስት የአገዛዙ መከላከያ ሰራዊት ሲደመሰስ ከ18 በላይ ቁስለኛውን በመያዝ ደብረ ዘቢጥ ከተማን ሳይረግጥ ወደ መሸሸጊያው ፍላቂት ከተማ ተመልሷል ሲል የ303ኛ አሳምነው ኮር  ህዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃውን አድርሷል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን መምሪያ ሰኔ 19/ 2018 ዓ/ም

ጀብደኛው ምኒልክ ዕዝ 101ኛ ኮር ከሶስት ቀናት በላይ በወሰደ አውደውጊያ በደመነፍስ የሚመራው የአገዛዙን ሰራዊት ብትንትኑንን በማውጣት ታላቅ ጀብዱን ተቀዳጄ! ምኒልክ ዕዝ 101ኛ ኮር 35ኛ ክፍለጦር  በአገዛዙ ሰራዊት ላይ መብራቃዊ ጥቃት በመፈፀም እና ራሱን የደቡቡ ዕዝ 205ኛ ኮር እያለ የሚጠራው የስርዓቱ ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት እና ከሌሎች የስርዐቱ  ጨፍጫፊ ኮሮች የተውጣጡ ሻለቃዎች በስምንት አቅጣጫ በመግጠም እጅን ከአፍ የሚያስጭን ታሪክ አስመዘገቡ። ነበልባሏ 35ኛ ክፍለጦር ሰኔ 16/2018 ዓ/ም እስከ ሰኔ 18 /2018 ዓ.ም በተደረገ ትንቅንቅ   በተለያየ አቅጣጫ ውጊያ የከፈተውን የአገዛዙ ሰራዊት ቀለበት ውስጥ በማስገባት በመደምሰስ ድልን ከመጎናፀፍ  ባለፈ በስርዐቱ ቅዠታም እና ጥቅመኛ ጀኔራሎች  የሚመራውን ውጊያ የሻለቃ መሪዎች፣ ሻለቃ ዘመቻዎች እንዲሁም  መቶ መሪዎች ጭምር በመደምሰስ በጠላት ላይ ከባድ የሽንፈት ጭዋን አስጎንጭቶታል።   የአማራ ሕዝብን የሀዘን ማቅ በማልበስ ዘላለማዊ ጭቆናን በሕዝብ ላይ ለማፅናት የሚንደፋደፈው ቅልብተኛው የአብይ አህመድ የግል ወታደር ከአንድ ኮር በላይ ሃይሉን በማሰለፍ 35ኛ ክፍለጦርን በወረባቦ  በሲልኮ  በኩል፣ በጃራ በኩል  ጀጀባና ቂለንቲ ፣  በሀራ በኩል በጃሮታና በሀብሩ ፣ በውጫሌ በኩል በጎራርባና ደብል ጉባ ና መርኮታ፣በጭፍራ በኩል  በሀደሬ ፣በጊራና በኩል  በፉጂና ሩጋ እና በመንጠራ   ፣በመርሳ  በኩል በአረዳ በሬ  ድረስ ግትልትል ወታደሮቹን  ለውጊያ ቢያሰልፍም የፋኖን የማድረግ አቅም ፍንትው አድርጋ ያሳየችው 35ኛ ክፍለጦር ከአንድ ኮር በላይ በግጠም ታሪክ መስራት ቻሉ። የ35ኛ  ክፍለጦር  አናብስቶች የጠላትን አላማ ቢስ ወታደር በሁሉም ግንባሮች ስቦ በማስገባት ዘመን አይሽሬ ድልን ለአማራ እንዲሁም ሁሌም በታሪክ ሊታወስ የሚችል የውርደት ሽንፈት ለጠላት ማከናነብ ችለዋል።   የ35ኛ ክፍለጦር 1ኛ ሻለቃ እና ቃኝ  ረመጦች ከአፉር ቂለንቲ የተንቀሳቀሰውን የጥላት ሀይል  ከስናይፐርና መትረየስ አልሞ ተኳሾች ሙትና ቁስለኛውን ሲያደርጉት ሙቱን አፈር ሳያለብስ ቁስለኛውን እያንጠባጠበ ወደ ሀሮየና ጃራ  እየፈረጠጠ ተመልሷል።ጠላት በዚህ አውደ ውጊያ ተራ ተዋጊውን ብቻ ሳይሆን አመራሮቹን እንኳ በክብር መቅበር የማይችል በክብረ ቢስ እና ሀገርን ለጥቅም በሸጡ አመራሮች የሚመራ መሆኑን ማሳየት የተቻለበት አውደ ውጊያ ሆኖ ተመዝግቧል። አማራን እንደ ሕዝብ ጠላት ብሎ በእብሪት ወደ ጦርነት የገባው የብልፅግናው አገዛዝ የፋኖን መብረቃዊ ምት መቋቋም ሲሳነው  ከባድ መሳሪያን በዘፈቀዳዊ ድብደባ በማድረግ በአማራ ህዝብ ላይ በገፍራ፣ በመነኞ፣ በወረባቦ ላይ  የሚገኙ  አርሶ አደሮች ና ንፁሀን ቤቶች ማቃጠል እና በህይወት ላይ አደጋ አድርሷል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ሩጋ መነዮ  በተባለ ቦታ ላይ ስርዐቱ በነጋዴዎች ላይ የዱቄት፣ የልብስ መስፊያ ማሽን እንዲሁም የመድሃኒት ቤት ዝርፊያ እና ቅሚያ አድርጓል።  በመጨረሻም 35ኛ  ክፍለጦር በዚህ አውደ ውጊያ የተገኙ የጠላት ንብረቶች፦   ✔️Ak ክላሽንኮቮ መሳሪያ-----8 ✔️የክላሽ ጥይት ተተኳሽ-----135 ✔️የመትረየስ ጥይት ተተኳሽ-- 350 ✔️የድሽቃ ጥይት ተተኳሽ---------50 ✔️ሬን ኮት/የዝናብ ልብስ---------5 ✔️ወታደራዊ የውሀ ኮዳ-----------10 ✔️የተደመሰሰ የጥላት ሰራዊት ሰባል--25 ✔️የተደመሰሰ የጥላት ወታደረዊ አመራር ………3 ✔️የቁስለኛ ብዛት        ……… 15  ✔️የተማረከ የጠላት ቁስለኛ ሰራዊት----1 መሆኑ ለማወቅ ተችሏል።   መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲል መረጃውን የ35ኛ ክፍለጦር ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃውን አድርሷል።   ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ   ሰኔ 19/2018 ዓ.ም

ስምህ ከጀግንነት ጋር አብሮ የሚጠራው ታላቅ መሪና ተዋጊ #አርበኛ ዝናቡ ልንገረው ! በዚህ ከባድ የጦርነት አውድማ ላይ እያሳየኸው ያለው ወደር የለሽ ጥበብና ፅናት የእውነተኛ ጀግና ማረጋገጫ ነው።
+1
ስምህ ከጀግንነት ጋር አብሮ የሚጠራው ታላቅ መሪና ተዋጊ #አርበኛ ዝናቡ ልንገረው ! በዚህ ከባድ የጦርነት አውድማ ላይ እያሳየኸው ያለው ወደር የለሽ ጥበብና ፅናት የእውነተኛ ጀግና ማረጋገጫ ነው። አንተ በተኩስ መሃል የምትወስደው እያንዳንዱ እርምጃ ለሠራዊቱ ብርታት፣ ለጠላት ደግሞ መርዶ ነው። በፊት መስመር ላይ ቆመህ የምታሳየው የማይናወጥ ወኔና ለአማራ እና ለነገዋ ኢትዮጵያ የምትከፍለው መስዋዕትነት ታሪክ በወርቅ ቀለም የሚዘክረው ታላቅ ገደል ነው። ያንተ መኖር ለሀገር ጋሻ፣ ለሕዝብ ደግሞ የድል ተስፋ ነው። ክንድህ አይዛል፣ ስምህ ለዘላለም በክብር ይኑር! #ድል ለአፋብን ይቀጥላል.......................... ከታች ያለውን የቴሌግራም ቻናላችን ይወዳጁን https://t.me/httpsuYkZrGfSZrNjNjFk

የጀብደኛዉ ምኒልክ ዕዝ አሃዶች ጠላትን ወደ ገዥ ቦታ ስቦ በማስገባት ታላቅ ጀብዱ ፈፀሙ! የ106ኛ ኮር 22ኛ ክፍለጦር እና 303ኛ ኮር 81ኛ ክፍለጦር በጥምረት ሰኔ 19/2018 ዓ/ም  ከጀግኖች መፍለቂያ መቄት ምድር ጠላትን ሲወቁት ውለዋል። የአገዛዙ ሰራዊት በመድፍ ታግዞ ጠዋት 12:00 ሰዓት ውጊያ የጀመረ ሲሆን እስከ ቀኑ 8:00 ሰዓት በዘለቀው አውደ ውጊያ በርካታው የጠላት ጥምር ሰራዊት ሙትና ቁስለኛ ተደርጓል። በመከላከያ ሰራዊት፣ሚኒሻና ፖሊስ ታግዞ ወደ ሞት ቦታ የገሰገሰው የኦህዴድና ብአዴን ቅጥረኛ ሰራዊት በመቄት ወረዳ ተራራዎች ላይ ሲደመሰስ ገሚሱ ቁስለኛ ተደርጓል። በሲሲጊ፣በሀናመኳትና በወቄጣ  ሜዳና ተራራዎች በአልሞ ተኳሽ ፋኖዎች ሲነጠፍ ውሏል። የጠላት ሰራዊት በበኩሉ የመቄትን ዛፍና ምድር በመድፍና ሞርተር 82 ሲደበድብ ውሏል። በዚህም የአገዛዙ የአማራን ህዝብ የማጥፋት ግስጋሴ ከ11 ጊዜ በላይ የመድፍ ቅንቡላ እና 15 የሞርተር ቅንቡላን ሲወረውር የዋለው አገዛዙ በበርካታ የአርሶ አደር ንብረቶችና ዛፎች ጭምር  ውድመት አድርሷል። በዚህ አውደ ወጊያ በጠላት ላይ የደረሰ ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራ፦ ✔️ የተደመሰሰ ከ17 በላይ ሲሆን ✔️ 31 ቁስለኞች ሲሆኑ በሁለት አምቡላንስና በአራት ባጃጆች ወደ ፍላቂት ሲያመላልስ ውሏል። መዳረሻውን ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ሕዝብ የሕልውና ተጋድሎ ይቀጥላል ሲል መረጃውን የ106ኛ ኮር ሚዲያና ኮሚኒኬሽን መምሪያ ሃላፊ አርበኛ እሸቱ አባተ መረጃውን አድርሷል። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያ ኮሚኒኬሽን መምሪያ ሰኔ 19/2018 ዓ/ም

#የጠላት_እንቅስቃሴ‼️ ከፍኖተ ሰላም ወደ ጅጋ 2 ድሽቃ፣ ሶስት ኦራል ፣አንድ ካሶኒ ሰራዊት የጫነና ዙ 23 የታጀበ ሀይል እየወጣነዉ መረጃዉ ለጀግኖች ይድረስ! በቀጠናው ያለህ 109ኛ ኮር ዝግጁ ሁን! በጅጋ -ቋሪት- ደጋዳሞት ወይንም በጅጋ -ደምበጫ- ደጋዳሞት እቅድ ሊኖረው ስለሚችል በደፈጣና በዝግጁነት ጠብቅ‼️ 19/10/2018 ዓ.ም

ሰበር ዜና!! ወታደራዊ ልምድና ክህሎትን በተካኑ ጠቢባን መሪዎች የሚመራው ምኒልክ ዕዝ 102ኛ ኮር 12ኛ ክፍለጦር በብልፅግናው አገዛዝ ዘረ-ፈጅ ሰራዊት ላይ መብራቃዊ ጥቃት ፈፀመ! የ102ኛ ኮር የጥንካሬ ምልክት የሆነው የ12ኛ ክፍለጦር ሰኔ 18/2018 ዓ/ም በተለያየ አቅጣጫ የመጣውን የአገዛዙ ሰራዊት ቀለበት ውስጥ በማስገባት ሰአገዛዙ ሰራዊት ላይ ከባድ ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ጉዳት አደረሰ። የጨፍጫፊውና የአምባገነኑ ስርዓት አላማ-ቢስ እና ግትልትል ሰራዊቱን በመያዝ በዞብልና በራማ በኩል በተለምዶ  ፅሀይ መግቢያ ድረስ አሰላለፍ በማድረግ እንቅስቃሴ ያደረገ ቢሆንም የ12ኛ ክፍለጦር  አናብስቶች በመልሶ ማጥቃትና መከላከል በሁሉም ግንባር  ጥቃት በመፈፀማቸው የአገዛዙን ሰራዊት የሽንፈት ፅዋን አከናንበውታል። የ12ኛ ክፍለጦር 1ኛ እና 3ኛ ሻለቃ የቁርጥ ቀን የአማራ ልጆች ከቀዩ ጋሪያ ቡኩ እስከ ጎቡ ጋሪያ በመዘርጋት በወሰዱት እርምጃ የጠላትን ሀይል ቀለበት ውስጥ በማስገባት ከስናይፐርና መትረየስ አልሞ ተኳሾች  የተረፈው  ሙትና ቁስለኛውን ሳያነሳ ወደ መንደፈራ ቀበሌ እየፈረጠጠ ተመልሷል። በዚህ ታሪካዊ ውጊያ ጠላት በዚህ አውደ ውጊያ የራሱን የሻለቃና የሻምበል አመራሮችን አስከሬን ሳያነሳ በመሸሹ ምን ያክል ጨካኝና ክብር የለሽ መሆኑን በገሀድ  ያሳየበት ተራ የወንበደ ቡድን መሆኑን አሳይቷል። በተጨማሪ የቀድሞው ታጠቅ ክፍለጦር የአሁኑ 65ኛ ክፍለጦር የጠላትን የሀይል ሚዛን በማዛባት ሞርተር 82 በመጠቀምና ሻለቃዎችን ከኮባ ወደ ጎለሻና ዳልቻ   በማስጠጋት ጠላት ባልጠበቀውና ባላሰበው ሁኔታ በመብረቃዊ ጥቃት በመመታቱ ወደ ኋላ እንዲያፈገፍግ ተገዷል። የ65ኛ ክፍለጦር ረመጦች ጠላትን እንዳንቀሳቀስ በማድረግ እና ከበባ ውስጥ በማስገባት ከሀብሎ መንደር  እስከ ጎቡ ጋሪያ  በመዘርጋት ከባድ ዋጋ አስከፍለውታል።            በተመሳሳይ ሁኔታ የ102ኛ ኮር ቃኝ በዋልካ መንደር  በኩል በመግባት አሰፍስፎ የመጣውን ጠላት አከርካሪ የሰበሩ ሲሆን እንዲሁም የ101ኛ ኮር የ11ኛ ክፍለጦር 1ኛ ሻለቃ አናብስቶች ወንድሞቻቸውን በማገዝ በአርበኛ ጌታየ ከበደ እየተመሩ ወደ ጮቢ በር በመሳብ ጠላትን መፈናፈኛ በማሳጣት ታሪካቸውን በቀይ ቀለም ፅፈዋል። ጠላት ሶስት (3) መድፍ ፣ አንድ ዙ-23 እንዲሁም አንድ ሞርተር-120 በማሰለፍ  ሆርማትና መንደፈራ ከባድ መሳሪያ በማስወንጨፍ ሙሉ አቅሙን የተጠቀመ ቢሆንም የ102ኛ ኮር ክንደ ብርቱዎቹን መቋቋም ባለመቻሉ ካለበት ቦታ እንዳይንቀሳቀስ በማድረግና የገባውን ሀይል እንዳይወጣ አድርገውታል። በመሆኑም የጠላት ግትልትል አላማ ቢስ ሰራዊት በሁሉም አቅጣጫ ወደ ኋላ በመመለስ ወታደራዊ መረጃና ኦፒ የሌለው የብልፅግና መራሹ አምባገነኑ ስርዓት በግምትና በቸልተኝነት የከባድ መሳሪያ ድብደባ በማድረግ በአማራ ህዝብ ላይ በአድስ ቅኝና በጃሮታ ቀበሌዎች ላይ ግብሩ የሆነውን ጦርነቱ የማይመለከታቸውን አራት (4) ሲቪል አርሶ አደሮች ህይወት ቀጥፏል። ከሞቱት ሲቪሎች መካከል የ80 አመቱ ሽማግሌ የ04 ጃሮታ ቀበሌ አቶ ጉብሳ ገብረ ህይወት እና ዘሀራ ኡመር የ8ዓመት ህፃን እንዲሁም የ05 አድስ ቅኝ ቀበሌ አቶ ሙሀመድ ኩቢ 50 ዓመትና አለምነሽ እያሴ የ43 ዓመት እድሜ  ይገኙበታል። የአንድ ቤተሰብ አባል የአቶጉብሳ ገብረ ሂይወት ልጅ ድርብ ጉብሳ፣ ሙሉ ቢሰጠኝ እንዲሁም የአቶ ሙሀመድ ኩቢ ባለቤትና ልጆች በሙሉ ከፍተኛ ቁስለኛ በመሆን በሞትና በህይወት መካከል ይገኛሉ። ጀብደኛው  የ102ኛ ኮር በአርበኛ ጌታቸው መልኩና በአርበኛ ዘውዱ ዳርጌ ወታደራዊ አዛዥነት እንዲሁም በአርበኛ በላይ መንግስቱና በአርበኛ ሻምበል ሞላ ማሩ  ዘመቻ መሪነት እየተመራ ዛሬም በከፍታ ማማ ላይ እየበረረ ይገኛል። በመጨረሻም በዛሬው እለት በ12ኛ ክፍለጦር በዚህ አውደ ውጊያ የተገኙ የጠላት ንብረትና ኪሳራ በዝርዝር እንደሚከተለው እንገልፃለን ✔️Ak ክላሽንኮቮ መሳሪያ-----28 ✔️ የክላሽ ጥይት ተተኳሽ-----670 ✔️የመትረየስ ጥይት ተተኳሽ-- 1834 ✔️የብሬን ሸንሸል-------------------6 ✔️የድሽቃ ጥይት ተተኳሽ---------434 ✔️ አይኮም /icom ----------------1 ✔️ወታደራዊ ሻንጣ---------------38 ✔️ሬን ኮት/የዝናብ ልብስ---------42 ✔️ወታደራዊ የውሀ ኮዳ-----------32 ✔️F1 ቦንብ------------------ ---18 ✔️የተደመሰሰ የጥላት ሰራዊት--89 ✔️የተማረከ የጠላት ቁስለኛ ሰራዊት----60 መሆኑን እንገልፃለን። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲል መረጃውን የ102ኛ ኮር ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ሃላፊ አርበኛ አታሎ ሙሉጌታ ፈንታው መረጃውን አድርሷል። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ  ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ሰኔ 19/2018 ዓ.ም

የብልፅግናው ወንበር ጠባቂ ሰራዊት ከሁለት ቀናት በፊት ወደ ደጋ ዳሞት ለመግባት ቢሞክርም ተቀጥቅጦ ተመልሷል ። ዛሬም ከቋሪት አቅጣጫ የጀግኖቹን ክንድ ሲቀምስ ውሏል። ዲሽቃ ተኳሹ ዝናቡ ልንገረው ደለለ 👏 ከሰራዊቱ ጋር እኩል ገብቶ የሚዋጋ የሚያዋጋ አመራር ነፍሴ ታከብረዋለች💪

የአገዛዙ ዙፋን ጠባቂ፣ የ76ኛ ክ/ጦ አዛዥ ኮለኔል አበራ በፈረስ ቤት፤ ደጋ ዳሞት ይበርት ሐሙስ ገበያ ከመደምሰሱ ጥቂት ቀደም ብሎ። ምስል👉 ከተማረከው ተንቀሳቃሽ የእጅ ስልኩ የተገኘ።ሰኔ 19/2
+2
የአገዛዙ ዙፋን ጠባቂ፣ የ76ኛ ክ/ጦ አዛዥ ኮለኔል አበራ በፈረስ ቤት፤ ደጋ ዳሞት ይበርት ሐሙስ ገበያ ከመደምሰሱ ጥቂት ቀደም ብሎ። ምስል👉 ከተማረከው ተንቀሳቃሽ የእጅ ስልኩ የተገኘ።ሰኔ 19/2018 ዓ.ም ፈረስ ቤት፤ደጋ ዳሞት!!

በደሴ ዙሪያ የአርበኞች ቤተሰቦች ታገቱ፤ የመሬት ደብተሮችም ተዘረፉ» ​ደሴ— በደቡብ ወሎ ዞን ደሴ ዙሪያ ወረዳ ቀበሌ 028 (ልዩ ስሙ ሰፋየት)በሚባለው አካባቢ የሚንቀሳቀሱ የአገዛዙ ታጣቂዎችና ሚሊሻዎች የአርበኞችንና የፋኖ መሪዎችን ቤተሰቦች በከፍተኛ ሁኔታ እያገቱና እያሰቃዩ መሆኑን ከአካባቢው የደረሰን መረጃ ያመለክታል። ​የአርበኛ ሐምሳለቃ ዜናው ማርቆስ ቤተሰቦች ላይ የደረሰው እገታ በቀን 19/10/2018 ዓ.ም በተፈጸመው በዚህ ጥቃት፣ የአማራን ሕዝብ ለማጥፋት የሚንቀሳቀሰው የአገዛዙ መዋቅር፣ የንጉሥ ሚካኤል አሊ ክፍለ ጦር መሥራችና የ104ኛ ኮር አሰልጣኝ የነበሩትን የአርበኛ ሐምሳለቃ ዜናው ማርቆስን ቤተሰቦች በድጋሚ አግቶ ወስዷል። ​ይህ የአገዛዙ ኃይል ከዚህ ቀደምም የሐምሳለቃ ዜናውን ቤተሰቦች አስሮ የለቀቀ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ግን «አርበኛውን አምጡ፤ ካላመጣችሁ መሬታችሁን አታርሱም» በሚል ከፍተኛ ዛቻና እንግልት እያደረሰባቸው ይገኛል። ታጣቂዎቹ የቤተሰቡን የእርሻ መሬት ደብተር ጭምር በጉልበት ቀምተው በመውሰድ፣ «ለመሬቱ ማስለቀቂያ ከፍተኛ ገንዘብ አምጡ» በማለት ቤተሰቡን እያሰቃዩት መሆኑ ታውቋል። ​ሐምሳለቃ ዜናው ማርቆስ በሸዋ አሳመነው ዕዝ በአሰልጣኝነት የቆዩ፣ በመካነ ሰላም ግንባር ሲመሩ የነበሩና ከታዋቂው አርበኛ አደም አሊ ጋር በመሆን የንጉሥ ሚካኤል አሊ ክፍለ ጦርን የመሠረቱ አንጋፋ ወታደራዊ መሪ መሆናቸው ይታወቃል። ​የአርበኛ ሙባረክ ቤተሰቦችም በተመሳሳይ ዜና፣ በዚሁ ቀበሌ 028 (ሰፋየት) ነዋሪ የሆኑት የሌላኛው አርበኛ ሙባረክ ቤተሰቦችም የዚህ ጥቃት ሰለባ ሆነዋል። ታጣቂዎቹ «አርበኛ ሙባረክን አምጡ» በሚል እናቱን፣ አባቱን፣ እህቱንና ወንድሙን በጅምላ አግተው ወስደዋቸዋል። ​በግንባር የአርበኞችንና የፋኖን ክንድ መቋቋም ያቃተው የብልጽግና ስምሪት፣ አሁን ላይ መከላከያ የሌላቸውን የቁርጥ ቀን የአማራ ልጆች አረጋውያን ወላጆችንና ቤተሰቦችን በማገት፣ ንብረት በመዝረፍና መሬት በመንጠቅ ላይ የተመሠረተ የበቀል እርምጃ እያካሄደ እንደሚገኝ የደረሰን ዘገባ ያመላክታል። ​ለጊዜው የታጋቾቹ ያሉበት ሁኔታና የተወሰዱበት ስፍራ በውል አልታወቀም። ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተልን ለተመልካቾቻችን የምናደርስ ይሆናል።