ch
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

前往频道在 Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

显示更多
2 940
订阅者
-1524 小时
+287 天
+37030 天
帖子存档
​እንደ አማራ፣ የህዝቤ ስቃይና እንግልት በእያንዳንዱ የሰውነት ክፍሌ ውስጥ ይሰማኛል፤ ህመሙ እጅግ በጣም ይገባኛል። እኔ እኮ በኩራት የምናገረው ንፁህና ትክክለኛ የአማራ ልጅ ነኝ! ነገር ግን ይህ
​እንደ አማራ፣ የህዝቤ ስቃይና እንግልት በእያንዳንዱ የሰውነት ክፍሌ ውስጥ ይሰማኛል፤ ህመሙ እጅግ በጣም ይገባኛል። እኔ እኮ በኩራት የምናገረው ንፁህና ትክክለኛ የአማራ ልጅ ነኝ! ነገር ግን ይህ ማነነቴ ብቻ በቂ አልሆነም፤ እኔ ያው እኔው ነኝ—ትክክለኛ የአማራ ልጅ። ​ሆኖም ግን፣ በህይወቴ ምንም ዓይነት ወንጀል አልሰራሁም፣ ዛሬም አልሰራም፣ ነገም ሰርቼ አላውቅም። በንፅህና እየኖርኩ ለምን ይሄ ሁሉ መከራ እንደሚደርስብኝ ባይገባኝም፣ #Dawit #Amhara 12/10/2018 ዓ.ም #የቴሌግራም ገፃችን ይወዳጁ!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!! https://t.me/httpsuYkZrGfSZrNjNjFk

​እንደ አማራ፣ የህዝቤ ስቃይና እንግልት በእያንዳንዱ የሰውነት ክፍሌ ውስጥ ይሰማኛል፤ ህመሙ እጅግ በጣም ይገባኛል። እኔ እኮ በኩራት የምናገረው ንፁህና ትክክለኛ የአማራ ልጅ ነኝ! ነገር ግን ይህ
​እንደ አማራ፣ የህዝቤ ስቃይና እንግልት በእያንዳንዱ የሰውነት ክፍሌ ውስጥ ይሰማኛል፤ ህመሙ እጅግ በጣም ይገባኛል። እኔ እኮ በኩራት የምናገረው ንፁህና ትክክለኛ የአማራ ልጅ ነኝ! ነገር ግን ይህ ማነነቴ ብቻ በቂ አልሆነም፤ እኔ ያው እኔው ነኝ—ትክክለኛ የአማራ ልጅ። ​ሆኖም ግን፣ በህይወቴ ምንም ዓይነት ወንጀል አልሰራሁም፣ ዛሬም አልሰራም፣ ነገም ሰርቼ አላውቅም። በንፅህና እየኖርኩ ለምን ይሄ ሁሉ መከራ እንደሚደርስብኝ ባይገባኝም፣

የጠላት ኃይል በ81ኛ ክፍለ ጦር በተደረገበት ከበባ አካላዊ እና ቁሳዊ ኪሳራ ደረሰበት!! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር 81ኛ ክፍለ ጦር በሚንቀሳቀስበት ሰሜን ወሎ ዞን መቄት ወረዳ  የተንቀሳቀሰው የብርሃኑ ጁላ ጦር  ያላሰበውን ቁሳዊ እና ሰብዓዊ ኪሳራ አስተናግዶ ተመልሷል ። መነሻውን ከፍላቂት ከተማ በማድረግ ወደ ሃና መኳት (መስቀል) እየተግተለተለ የተጓዘ ቢሆንም የአፓርታይዱ አብይ አህመድ ዙፋን አስጠባቂ ከተሰበሰበበት ልዩ ቦታው ጫት ውሃ እስከ ዳንዴ በር  መከማቻውን ግማሽ ፍላቂት ከተማን ጨምሮ የጠላት ሃይል ላይ የማያዳግም እርምጃ ወስደውበታል። ውጊያው ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ/ም ከቀኑ 8:00 እስከ ምሽቱ 3:00 የተካሄደ ሲሆን ከ81ኛ ክፍለ ጦር 1ኛ መቶ አለቃ ዳንኤል ሻለቃ፣ 2ኛ ኮሎኔል ሰሎሞን አሻግሬ ሻለቃ እና የከፍለ ጦሩ ቃኝዎች  አውደ ውጊያው ላይ የጎላ ሚናቸውን እና ክንደ ብርቱነታቸውን በበላይነት አረጋግጠዋል። በተደረገው አውደ ውጊያ 14 የጠላት ሃይል ሲደመሰስ ከ16 በላይ ቁሰለኛውን በመያዝ ወደ መደበቂያው ፍላቂት ከተማ ፈርጥጦ ተመልሷል። በዚህ የተበሳጨው የአገዛዙ ወንበር አስጠባቂ ሃይል የንፁሃንን ቤትና ንብረት ያወደመ ሲሆን በመድፍ ሲደበድብ ሁለት ንፁሃን ግለሰቦች ውድ ህይወታቸውን ሲያጡ 1ቁስለኛ እና ሁለት መኖሪያ ቤት በመድፍ መፍረሱን የአይን እማኞች አረጋግጠዋል። ሰሞኑን ከአውደ ውጊያ ጎን ለጎን የጁላን ሃይል ስቦ በማስገባት ፣ በማፍረስ እና በማስከዳት ደረጃ  በየቀኑ ወደ ፋኖ በሚቀላቀሉት የስርዓቱ ወታደሮች የተበሳጨው  ቀሪው ፀረ-አማራ ስብስብ በንፁሃን ግለሰቦች ላይ ጥላቻውን አጠናክሮ ቀጥሎበታል ሲል የ303ኛ አሳምነው ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃውን አድርሷል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያ እና ኮሚዩኒኬሽን  መምሪያ!!          ሰኔ:- 12/ 2018 ዓ/ም

በአጭሩ አርበኛውን ስናስበው! ክረምቱ ግም ሲል... የሰኔ ሚካኤል ዕለት! 1958 ዓም ​በዛሬዋ ዕለት—የክረምቱ መባቻ ነጎድጓድ ምድሪቱን በሚያናውጥበት ሰማይ ለምድር የነገ የኢትዮጵያን በረከትና ዝናብ ለማውረድ በሚያሽሞረሙርበት በዚች ታላቅ የሰኔ ሚካኤል ዕለት—በይፋት እና ጥሙጋ አውራጃ ልዩ ስሟ ኬብሮይ ማርያም በምትባል ምድር የታሪክና የጽናት ተምሳሌት የሆነ አንድ ታላቅ ሰው ወደዚች ዓለም ተቀላቀለ። ​እንደማንኛውም የገጠር ልጅ በአፈር እየፈጨ “ሀ ግዕዝ” ብሎ ፊደል ቆጥሮ፣ ዳዊትንም ደግሞ አድጓል። በአስኮላውም ገፍቶ በመሄድ ታላቅ የሥነ-ጽሑፍ ሰው ለመሆን በቅቷል። የኋላ ኋላም እየጎለመሰ ሲሄድ ብዕር የልቡን ትርታ ትናገርለት ዘንድ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል ተወዳጃት፤ የቃል ኪዳን አጋሩም አደረጋት። ​የአማራ ብሔርተኝነት ራሱን አደራጅቶ ከጥፋት ይከላከል ዘንድ መዐሕድ በክቡር ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ ሲመሰረት እርሱ በድርጅቱ ጽሕፈት ቤት በታማኝነትና በትጋት አገልግሏል። ኋላም ያንን ታሪክ ሰሪ ትውልድ ከዛሬው ትውልድ ጋር የሚያገናኝ ሕያው ድልድይ ይሆን ዘንድ የትናንቶቹን ገድልና አበርክቶ በመጻሕፍት ገጾች እያነጸ—አንድ፣ ሁለት፣ ሦስት እያለ ከአሥራ አምስት በላይ ድንቅ መጻሕፍትን ለትውልድ አውርሷል። አርበኛው ከፃፋቸው መፅሐፎቹም በከፊል ፦ ‎ ‎1. ኮብላይ ‎2. ጥብቅ ሚስጥር ‎3. ነፀብራቅ ‎4. ማጎርሚ ሳቢብ ‎5. እኔና ህይወቴ ‎6. ከኢትዮጲያ ወንዞች ማዶ ‎7. ሞትን ቀደምኩት ‎8.  የቃል ፅናት ‎9. የጥላቻ መንፈስ ‎10. ፋና ወጊዮች ‎11. የጠፋው ተራራ ትንሳኤ ‎12. አዳኝና ገዳይ ‎13. ያላለቀው ጦርነት ‎14. ሰኔ 15 ሴራ .... ​ብዕርን በውብ ማዕዛ የሚያናግረው ስዕላዊ ድርሰትን በአንባቢው አእምሮ ውስጥ ድቅን አድርጎ የሚስለው የያኔው ጋዜጠኛና ደራሲ በጊዜው የቀመር ኡደት ውስጥ ይህ ትውልድ ከተጋረጠበት የህልውና አደጋ ራሱን ይታደግ ዘንድ ብዕሩን ከጠመንጃ አስተሳስሮ ጫካ ወርዶ ሕዝቡን አደራጅቶም ለመምራትም በቅቶ ነበር ። የዚህ ትውልድ ግንባር ቀደም የነጻነት ምልክትና ፊትአውራሪ የነበረው ይህ ሰው ለስራው እውቅናን ልክብሩ ሽልማቱን ተሸልሟል... ...እርሱ ግን የአማራን ብሔርተኝነት ከመጻሕፍት ገጾች አውርዶ መሬት ላይ እንዲያርፍ እውነት ሆኖ ነፍስ እንዲዘራና በፅኑ መሠረት ላይ እንዲቆም “ያላለቀው ጦርነት” ብሎ ለታጋዩ ትውልድ ውርስ አድርጎ ሰጥቷል። ​ዛሬ በአካል እኛ መሃል ባይኖርም እርሱ ያሳየን የነጻነት መንገድና የቃል-ኪዳኑ ጽናት ግን በየበረሃው ባለው ትውልድ ልብ ውስጥ የብርሃን ጮራ ፈንጥቋል፤ የተስፋ ስንቅንም አስታጥቋል። ስጋ ታሳሳለች እናም እንደስናፍጭ ቅንጣት በሆነችው እምነቴ ውስጥ ​ፈጣሪ አምላክ ካለህበት የእስር የፈተናና ጽልመት ህይወት ውስጥ በሰላምና በጤና አውጥቶ ለብርሃንና ለነጻነት ቀን ያብቃህ! ​መልካም የልደት መታሰቢያ ዕለት ለቃል ኪዳኑ ሰው ለጋዜጠኛ እና ደራሲ አሰግድ መኮንን!

አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ የ102ኛ ኮር የሴት አርበኞች መሰራታዊ ፍላጎት፣ አደረጃጀት፣የትግል አቋምና ፅናት፣ መብትና ግዴታን በተመለከተ የጋራ አጀንዳ በመያዝ ውይይት አደረጉ። ሰኔ 11/2
+1
አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ የ102ኛ ኮር የሴት አርበኞች መሰራታዊ ፍላጎት፣ አደረጃጀት፣የትግል አቋምና ፅናት፣ መብትና ግዴታን በተመለከተ የጋራ አጀንዳ በመያዝ ውይይት አደረጉ። ሰኔ 11/2018ዓ/ም የምኒልክ ዕዝ የሴቶች ጉዳይ መምሪያ ሀላፊ ፋኒት ዚነት አደምና የ102ኛ ኮር  የሴቶች ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ፋኒት እርጎ ማርዬ በተገኙበት ውይይቱ ተካሂዷል። በውይይቱ በርካታ ጠንካራ ሀሳቦች በሴት አርበኞች በሰፊው ተነስተዋል። በዚህም የ102ኛ ኮር የሴቶች ጉዳይ መምሪያ ሀላፊ ፋኒት እርጎ ማርየ  የ102ኛ ኮር የሴት አባላት ወር በገባ የስብሰባ ጌዜዎችንና የስራ ሪፖርት የሚደረግባቸው ቀኖችን ገለፃ አድርጋለች። በመጨረሻም የአፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ የሴቶች ጉዳይ መምሪያ ሀላፊ ፋኒት ዚነት አደም ስለሁሉም አጀንዳዎች ማብራሪያ ከሰጠች በኋላ በተለይም ስለ ወደፊት የትግሉ አቅጣጫና የአማራ ህዝብ እጣ ፈንታ ምን እንደሚመስል ማብራሪያ ሰጥታለች ሲል የ102ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃዉን አድርሷል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!! አፋብን ወሎ ቤተ- አማራ ምኒልክ ዕዝ  ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!! ሰኔ 12/2018ዓ.ም

🔥ከሽራሮ አዲ-ፀፀር ግንባር እስከ ወሎ ቤተ አማራ ​ሰንሰለታማ ተራሮች‼️ የአሳምነው ትውልድ ቀየ ላስታ ያፈራችው የጦር ጠበብት አርበኛ ሻንበል ወዳጀ ደሴ! ከፊቱ ላይ የሚታዩት የፈተና መስመሮች፣ የቆሰለው እግሩ እና በልቡ ውስጥ ያለው የህዝብ ፍቅርን ለተመለከተ ሰው አርበኛው በወገን ፍቅር የነደደ መሆኑን ይገነዘባል። አርበኛ ሻንበል ወዳጀ ደሴ፡ ከወጣትነት እስከ ጉልምስና እድሜው ድረስ ሙሉ ሕይወቱን ለአማራ ህዝብና ለሀገሩ ዳር ድንበር የገበረ የዘመናችን አንፀባራቂ ጀግና ነው። ​ ​በ1982 ዓ/ም የድሮውን መከላከያ ሠራዊትን ተቀላቅሎ ለ14 ዓመታት ያህል በበረሃና በጋራ ሸንተረሮች ላይ ደሙንና ላቡን አፈስሷል።  ፍርሃትን ፈፅሞ የማያውቀውና ጀግንነት መለያው የሆነው የዛኔው ወጣቱ ተዋጊ አርበኛ ሻምበል ወዳጄ፡ በየግንባሩ በሚያስመዘግባቸው አስደናቂ ጀብዱዎች የመቶ አለቃ ማዕረግ ሊያገኝ ችሏል። ​ወዳጀ ደሴ ተዋጊ ብቻ አልነበረም። የጦር ሜዳ ስልትን ጠንቅቆ የሚያውቅ፣ የጠላትን ካምፕ የሚያናጋ ደፋር አዋጊ ጭምር እንጂ።  ከ1990ዎቹ መጀመሪያዎች ጀምሮ በነበረው የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት በታሪካዊው #የሽራሮ_ግንባር—አዲ ፀፀር ላይ #ምድር_በባሩድ_ስትናወጥ፣ ሻንበል ወዳጀ ከባድ ተጋድሎ በማድረግ በውጊያ በመቁሰል ጭምር ለእናት ሃገሩ ታላቅ ታሪክ ፅፏል። በህክምና ቦርድ ተሰናብቶ ወደ ትውልድ ቀዬው፣ ወደ ታሪካዊቷ ሰሜን ወሎ ዞን ላስታ ወረዳ፣ ላሊበላ ከተማ ተመለሰ። ​ሻንበል ወዳጀ ደሴ ለ20 ዓመታት በላሊበላ ምድር ከቆሰለ እግሩ ጋር እየታገለ፣ የሰላም ህይወትን መራ በዚህ ቆይታዉ ላሊበላ ከተማ ዉስጥ የተሻለ ህይወትን ይመራ ነበር። ነገር ግን ታሪክ ለሁለተኛ ጊዜ ደጃፉን አንኳኳ። በ2013 ዓ.ም የሰሜኑ ጦርነት ሲቀሰቀስና "ሀገር ተወረረች፣ ህዝብህ አደጋ ላይ ወደቀ" የሚለው ጥሪ በመላ አማራ ክልል ላይ ሲያስተጋባ፣ አርበኛው ቤቱ ሊቀመጥ አልቻለም። ​የቆሰለ እግሩን ረሳው፤ ሽበት የወረረውን ራሱን በኩራት ቀና አድርጎ የአማራ ልዩ ሃይልን ተቀላቀለ። በወጣትነቱ ያካበተውን የጦርነት ልምድ በመጠቀም፣ ወጣቶቹን እያደራጀና እየመራ በጦርነቱ ግንባር ቀደም ተጋድሎን በማድረግ #አይሰበርም የተባለዉን #ባላጎ_ምሽግን ከጓዶቹ ጋር ሆኖ በመስበር ደማቅ ታሪክን በደሙ ፃፈ። የብልፅግናው አገዛዝ የአማራ ልዩ ኃይልን ለማፍረስ በወሰነ ማግስት፣ አርበኛ ሻንበል ወዳጀ ደሴ የታገለለትን አላማ አሳልፎ ለመስጠት አልፈቀደም ነበር። ወዲያውኑ በላሊበላና አካባቢው ወደሚንቀሳቀሰው የነጻነት ጋሻ አሳረኛዉ ፋኖ ተቀላቀለ። ​በዚህ የሽምግልና እድሜው እሱ ለወጣቶቹ ፋኖዎች፦​መካሪና ዘካሪ ነው—በችግር ጊዜ ተስፋ እንዳይቆርጡ የልብ ብርታታቸዉ ነው ፣ የውጊያ ስልትንና ጥበብን ያካፍላቸዋል። አሁንም ድሩስ ​አዋጊና ተዋጊ ነው። የጦር መሳሪያውን ይዞ በግንባር ቀደምትነት ይሰለፋል። የማይበገረው፡ የጦር ጠበብቱ፣ የአማራው አለኝታ በአሁን ሰዓት በአፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ የግዙፉ 303ኛ አሳምነው ኮር በከፍተኛ አመራርነት እያገለገለ ይገኛል። አርበኛ ሻንበል ወዳጀ ደሴ የአሁኑ 303ኛ ኮር እዚህ መድረስ ታላቅ አብርክቶ አድርጓል። ከሻለቃ ብርጌድ ከብርጌድ ክፍለ ጦር ከክፍለ ጦር ኮር ድረስ እስከሚደርስ #የላስታ_ሰንሰለታማ_ተራሮች ሳይበግሩት ተንቀሳቅሶ አደራጅቷል። ሻንበል ወዳጀ ከላስታ እሰከ መቄት ፣ከመቄት እስከ ዋድላ፣ከዋድላ ራያ ፣ ከራያ አንባሰል ድረስ በመንቀሳቀስ የፋኖ አደረጃጀት አሁን ላይ እዚህ መድረስ ትልቅ ስራ ሰርቷል። ​ከ1982 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ—ከወጣትነት ጉልበት እስከ ጉልምስና እድሜዉ ለአማራ ህዝብ ህልውናና ክብር ሲል ትውልድ የሚኮራበት ደማቅ አሻራ እያስቀመጠ ይገኛል። የእሱ ሕይወት የአንድ ሰው ታሪክ ብቻ አይደለም፤ የህዝብ ፅናት፣ የነጻነት ጥማትና የማይበገረው የአማራ ማንነት መገለጫ እንጂ። አርበኛው ድል ለአንተና ለህዝብህ ይሁን! 12/10/2018 ዓ.ም

አርበኛ ዘመን ካሴን ያወቁት አስራ ምናምን አመታት በላይ ይሆናል።ያኔ በሚዲያ በሚነገረው ልክ ብቻ ለማወቅ ችያለሁ።በአካል አግኝቼው በአማራ ህዝብ ጉዳይ ፣ አገራዊ ጉዳይ ፣ ህዝባችን የመጣበትን እጅግ ውሰብሰብ የህልውና አደጋ ከዚሁ አደጋ ለመውጣት ከትውልዱ የሚጠበቀውን እና ማድረግ የሚገባንን በትንሹ ለማውጋት ከቻልኩ በጣት የሚቆጠሩ አመታት ይሆናሉ። "የነብርን ጅራት ከያዙ አይለቁ "በሚለው አማራዊ ብሂል በአካል አግኝቼ ከአወራሁት በኃላ አርበኛው በተለመው ርዕይና መስመር ከእኔ የሚጠበቀውን ለማድረግ ተሰልፌ እገኛለሁ።ይህ ዘላለማዊ ቃል ኪዳን ነው! ከመሪያችን ጋር በመተዋወቄና ወለም ዘለም በሌለው የአርበኛ ዘመነ ካሴ አብዮታዊ የትግል መስመር ውስጥ ያገኘሁት ነገር ፦ ➡️ቅንነት ➡️ ፅናት ➡️ብርታት ➡️ሀቀኝነት ➡️እውነት ➡️በጎነት ➡️ተስፋ ➡️አሸናፊነት በጥቅሉ አርበኛ ዘመነ ካሴ ለተበደሉና ለተገፉ የሚቆም የትግል መንፈስ (ቀናኢ አስተሳሰብ) ከውስጥህ ካለህ ያንን ቅዱስ መንፈስ ቀስቅሶ በአንድ ጀንበር ከትግል ሜዳ ላይ ከፊት ረድፍ ተሰላፊ ያደርግሃል።በቁስ የማይለካ መንፈሳዊ እርካታ ውስጥ ይከትሃል።ነገር ግን ከአርበኛ ዘመነ ካሴ ጋር በመጠጋት የተለየ ጥቅም፣አንዳች ፍላጎት አሳካለሁ ብሎ የቀረበ ግለሰብ ወይም ቡድን የፈለገውን ሲያጣ ይርቃል።በአካልም በመንፈስም ከትግሉ ይሸሻል ።"ያጣ ምንድን ፥ተሳድቦ ይሄዳል!" አንደዚህ አይነት ነገር ትላንት ተከስቷል ፣ዛሬም አለ ፣ነገም ይኖራል! መፍትሄው መፅናት ብቻ ። እንፅና! ክፋት ለማንም፣በጎነት ለሁሉም! አዲስ ትውልድ፣አዲስ አስተሳሰብ ፣አዲስ ተስፋ! Hailemichael Bayeh

የብልፅግና ሰራዊት አባላት ሙሉ ትጥቃቸውን ይዘው ፋኖን ተቀላቀሉ፤ የአገዛዙ መፈራረስ መፋጠኑ ቀጥሏል ሰኔ 12/2018 ዓ.ም ============= ​ የምህረት ጥሪውን በመቀበል፣ ከብልፅግና ሰራዊት 102ኛ ኮማንዶ ክፍለጦር 5ኛ ሻለቃ የተወጣጡ ሁለት የሰራዊቱ አባላት ሙሉ ትጥቃቸውን ይዘው የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝን በሰላም ተቀላቅለዋል። ወጣት ፈለቀ በላይነህ እና ወጣት ጌትነት ተፈሪ የተባሉ የ102ኛ ክፍለጦር አባላት ዘመናዊ የክላሽንኮቭ መሣሪያና ሙሉ ትጥቅ በመያዝ ለመሐመድ ቢሆነኝ ኮር አስቴ ጎማ ተራራ ክፍለጦር እጃቸውን ሰጥተዋል። እጃቸውን የሰጡት የሰራዊቱ አባላት እንደገለጹት፣ የአብይ አገዛዝ ሰራዊት በአሁኑ ወቅት የውጊያና ግዳጅ የመፈጸም አቅሙ ሙሉ በሙሉ ተዳክሟል። በአገዛዙ መዋቅርና በሰራዊቱ ውስጥ ከፍተኛ የሆነ የእርስ በእርስ መከፋፈል እና ሽብር መፈጠሩን ገልፀው ይህም ብልፅግና የመፈራረስ ጉዞ ላይ መሆኑን ያሳያል ብለዋል።በመሆኑም በክ/ጦሩ አመራሮች ጥሩ አቀባበል የተደረገላቸው ወንድሞች ቀጣይ የበደልነውን ህዝብ እንክሳለን ያሉ ሲሆን ለቀሪ ጓዶቻቸው የኛን ብልህነት ተከተሉ ሲሉ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል። '' ክብር ለትግሉ ሰማዕታት'' ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! ​ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

"ፋኖን እወደዋለሁ" ያለው ፻ አለቃ ዘናቦ አሽቆ የ6ኛ ዕዝ 602ኛ ኮር 32ኛ ክ/ጦር ሁለተኛ ሬጅመንት ብሬን ተኳሽ በዛሬው ዕለት ከደብረ ማርቆስ ከተማ በመውጣት 206ኛ ኮር 14ኛ ክ/ጦር ንጉስ ተክለሃይማኖት ሻለቃን ተቀላቅሏል። አገዛዙ የተሳሳተ መልዕክት በማስተላለፍ ሰራዊቱ እንዳይከዳ ፋኖ ይገድላል እያለ ያስፈራን ነበር ነገር ግን እኔ ዛሬ ፋኖን ተቀላቅየ በፍቅር ተንከባክበውኛል ሲል ከ14ኛ ክ/ጦር ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ጋር በነበረው ቆይታ ገልጿል። ፻ አለቃ ዘናቦ አሽቆ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ፋኖን እንዲቀላቀሉ በኦሮሞኛና በሲዳማኛ ቋንቋ መልዕክት ያስተላለፈ ሲሆን ፋኖን እወደዋለው ሲል ተሰምቷል። ሰኔ 11/2018 ዓ.ም አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ! አዲስ ተስፋ! የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት

በአማራ ሳይንት ግንባር በ2 ጄኔራል መኮንኖች የተመራው ውጊያ ውጤት ሽንፈት ሆነ!! እስከ ሰኔ 30 ድረስ ፋኖን አፀዳለው በማለት እየቃዥ ያለው የፋሽስቱ አብይ አህመድ መንግሥት ወደ ምዕራብ ወሎ ግን
+1
በአማራ ሳይንት ግንባር በ2 ጄኔራል መኮንኖች የተመራው ውጊያ ውጤት ሽንፈት ሆነ!! እስከ ሰኔ 30 ድረስ ፋኖን አፀዳለው በማለት እየቃዥ ያለው የፋሽስቱ አብይ አህመድ መንግሥት ወደ ምዕራብ ወሎ ግንባር በብዛት የላከው ሰራዊት እንደ ጨው እየሟሟ ሲሆን የ11ኛ ዕዝ ዋና አዛዥ ጄኔራል አድማሱ አለሙ እና ምክትሉ ሜ/ጄኔራል ዘውዱ ሰጣርጌ መድፍ ጭምር ይዘው በመግባት በዛሬው እለት አማራ ሳይንት ወረዳ ውስጥ በ3 ግንባሮች ተኩስ ቢከፍቱም የአፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር 47ኛ ክፍለ ጦር ታቦር ተራራ ሻለቃ ፋኖወች አይቀጡ ቅጣት ቀጥተው በርካታ ጠላትን መደምሰስ እና ማቁሰል ችለዋል:: የታቦር ሻለቃ ፋኖዎች በጠላት ላይ በወሰዱት እርምጃ ቁጥሩ በውል ያልታወቀ የመከላከያ ሰራዊት አባል ሲደመሰስ እና ሲቆስል ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ መንገድ ሲመራቸው የነበረው የአማራ ሳይንት ወረዳ ሚሊሻ ፅ/ቤት የሚሊሻዎች ዘመቻ መሪ አድርጎት የነበረው አቶ ሙሉጌታ የተባለ ግለሰብ ከነ አጃቢዎቹ ተሸኝቷል:: በ3 ግንባሮች ማለትም በጓሜዳ፣ ተድባበ ማርያም እና ዋሮ በኩል እልፍ አእላፍ ሰራዊት አሰልፎ የተንቀሳቀሰው ጠላት አሁን ላይ አስከሬን እና ቁስለኛ ተሸክሞ እየተመለሰ ነው:: ጄኔራሎቹ ያሰቡት ሳይሳካላቸው ቀርቶ ደም ግፊት እና ስኳራቸው ተባብሶባቸው ለጤና ቀውስ ተዳርገዋል:: ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ሰኔ 11/2018ዓ.ም

ከህልውና ተጋድሎ ጎን ለጎን፤ አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የነገውን አማራ በትምህርት እና ዕውቀት የመገንባት ታሪካዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ ነው!!       ሰኔ 11/2018  ዓ.ም ​ትግሉ ዘርፈ ብዙ ስለሆነ በትምህርት መሸነፍ የነገን ትውልድ አሳልፎ ለመስጠት መጋበዝ በመሆኑ፣ በትግሉ መስመር ውስጥ ሆኖም መማርና ማስተማርን ማስቀጠል እንድሁም ለአማራ ህዝብ ህልውና በትግል አውድማ ላይ እያለንም ታጋዮች ሌት ተቀን መሰልጠን እና ማወቅ የህልውናው ተጋድሎ አንዱና ዋናው አካል ነው። ​የአማራ ሕዝብ በአሁኑ ወቅት ሁለንተናዊ በሆነ የህልውና ጦርነት ውስጥ እንደሚገኝ ይታወቃል። አገዛዙ (ብልፅግና)አማራን በህይወት፣በስነ-ልቦና ፣በኢኮኖሚ፣ በማኅበራዊ ጉዳይ ለማዳከም ሌሊትና ቀን እየሠራ ባለበት በዚህ ፈታኝ ወቅት፣ የሕዝብ ልጅ የሆነው የፋኖ ኃይል ግን በአንድ እጁ ጠላትን እየመከተ በሌላ እጁ ደግሞ የነገዋን አማራ የሚረከበው ትውልድ በዕውቀት እንዲታነፅ የጀርባ አጥንት እየሆነ ይገኛል። ​​የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ በተቆጣጠራቸው በሁሉም አካባቢዎች፣ የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ሙሉ በሙሉ በሰላም እንዲጠናቀቅ አድርጓል። ይህ ብቻ ሳይሆን፣  ዛሬም የተጀመረው የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና የመምህራንን እና የተማሪዎችን ሙሉ የደህንነት ዋስትና በማረጋገጥ በሰላማዊ ሁኔታ እየተካሄደ ይገኛል። ​በአንዳንድ አካባቢዎች የነገውን ትውልድ ጨለማ ለማልበስ የሚንቀሳቀሰው የአገዛዙ ኃይል ፈተናውን ለማደናቀፍ ሙከራዎችን ቢያደርጉም፣ በጀግናው ሰራዊታችን ተጋድሎ እና በአመራሩ ንቃት መክሸፍ ችለዋል። ከ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና በተጨማሪ፣ በአንዳንድ አካባቢዎች ከ9ኛ አስከ 11ኛ ክፍል የ2ኛ መንፈቅ ዓመት ማጠቃላይ ፈተና ያለምንም የደህንነት ስጋት፣ ዕዙ ባደረገው ሁሉን አቀፍ ድጋፍና ጥበቃ በስኬት እየተከናወኑ ይገኛሉ። ትምህርት የአንድን ማኅበረሰብ ነጻነት፣ ክብርና መጻኢ ዕድል የሚወሰን ታላቅ መሣሪያ በመሆኑ ጠላት የአማራን ሕዝብ ለማዳከም ከሚጠቀምባቸው ስልቶች አንዱ ትውልዱን ካለማወቅና ካለመማር ጨለማ ውስጥ መክተት እና ተቋማትን በድሮንና በመድፍ መምታት ነው።ይንንም በተለያዩ አካባቢዎች አድርጎታልም። ይሁን እንጂ የዕዙ አመራር ይህንን ሴራ ቀድመው በመረዳትና  በመገምገም፣ ትምህርት ቤቶች እንዳይዘጉና በተሟላ ሁኔታ በጦርነት ውስጥ ሆኖ መማር አዳጋች ቢሆንም ቢያንስ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው እንዳይርቁ እና የነገ አገር ተረካቢ ተማሪዎች ፈተናቸውን ያለምንም ስጋት እንዲወስዱ ሌት ተቀን እየተጉ ይገኛሉ። ሰራዊታችንም  ወደ ጦር ግንባር በመሰለፍ ብልፅግናን ከማፈራረስ ባለፈ፣ የማኅበረሰቡን ሰላምና ደህንነት በመጠበቅ ረገድ የመሪነት ሚናውን እየተወጣ ነው። መምህራን ያለምንም የደህንነት ስጋት ሙያዊ ግዴታቸውን እንዲወጡ ማድረጉ፣ ተማሪዎችም በሰላም ተፈትነው ወደ ቤታቸው እንዲመለሱ ሌሊትና ቀን በንቃት መጠበቁ ፋኖ የሕዝብ አለኝታ መሆኑን በድጋሚ ያረጋገጠበት ታላቅ ታሪካዊ ክስተት ነው። ​የአማራ ሕዝብ የህልውና ትግል የነገን ብሩህ ትውልድ የመቅረጽም ጭምር መሆኑን ይህ የፈተና ሂደት  ዓይነተኛ ማረጋገጫ ነው። ''ክብር ለትግሉ ሰማዕታት'' ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!   ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

የምኒልክ ዕዝን ከባድ ምት መቋቋም ያቃተው የብልፅግና አገዛዝ ሰራዊት በየቀኑ እየፈረሰ ፋኖን እየተቀላቀለ ይገኛል! ሰኔ 11/2018 ዓ.ም ብልፅግና ሥልጣኑን ይጠብቅለት ዘንድ የተመካበት ሠራዊት በመፍረስ አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር 47ኛ ክ/ጦር አትሮንስ ሬጅመንትን መዳረሻቸው አድርገዋል። የአማራ ህዝብን ለመከራና ሰቆቃ ለመዳረግ በዕብሪትና በማን አለብኝነት አማራን አንገት ለማስደፋት እና ለመጨፍጨፍ ወደ ጦርነት የገባው የኦህዴድ/ብልፅግና ቅጥረኛና ወንጀለኛ ቡድን በግድ ያግበሰበሰው ሠራዊት መኮብለልና መበተን የመጨረሻ አማራጭ የሌለው አማራጩ ሆኖ ቀጥሏል። የጦር ጠበብቶች ስብስብ የሆነውን ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር የተቀላቀሉ የአገዛዙ ሰራዊቶች፦ ✅ 50 አለቃ ሰማው አማረ......11ኛ ዕዝ 205ኛ ኮር 83ኛ ክ/ጦር ሻንበል መሪ ስናይፐር በመያዝ የተቀላቀለ ✅10 አለቃ ዳዊት ዳኛቸው............ከ19ኛ ክ/ጦር ✅መሠረታዊ ወታደር አማኑኤል አዲሴ.......ከ19ኛ ክ/ጦር ✅መሠረታዊ ወታደር ጥላሁን አማረ...........ከ19ኛ ክ/ጦር ወደ 105ኛ ኮር ገቢ የሆነ የጠላት መሳሪያ፦ ➥1 ጥቁር ስናይፐር ከነ ሙሉ ትጥቁ ➥3 ጥቁር ክላሽ ➥600 የክላሽ ተተኳሽ ➥9 የክላሽ ካዝና ➥2 የእጅ ቦንብ ➥ 3 የወገብ ትጥቅ 50 አለቃ ሰማው አማረ ስለ አገዛዙ ሀሳቡን ሲያስረዳ " የህዝብ ልጆች እንዳልሆን ሁሉ በህዝብ እንድንጠላ አድርጎናል። በሀገር መከላከያ ሠራዊት  የንፁሃን ቤት ሆን ተብሎ በከባድ መሳሪያ ተቃጥሏል፤ ሀብትና ንብረት ወድሟል።ከሚሰራው ግፍ አኳያ የተቋሙ አባል መሆንና መባል እጅግ በጣም አሳፋሪ ነው። መለያውን ለብሸ መታየት ያሳቅቀኛል። ሁሉም ተዋጊ ኃይል መውጣት ይፈልጋል፤ ጊዜና ምቹ ሁኔታ ብቻ ነው የሚጠብቀው። ሁሉም አባል በጥርጣሬ ነው የሚታየው፤በተለይ አማርኛ ተናጋሪ የሆነ ወታደር መታሰር መፈታት የዕለት ተዕለት እጣ ፋንታችን ነበር"ብሏል። መከላከያ አባላቱ ፋኖን ሲቀላቀሉ የ105ኛ ኮር ም/ዘመቻ ኃላፊው አርበኛ ጎሹ ታረቀና የአትሮንስ ሻለቃ አመራሮችና አባላት ደማቅ አቀባበል ያደረጉላቸው ሲሆን በተደረገላቸው አቀባበልም ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲል የ47ኛ ክፍለጦር ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃውን አድርሷል። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ሰኔ 11/2018ዓ.ም

202ኛ ኮር 🙏 👉 የአማራ ፋኖ በአማራ ከልል ትምህርት በተቋረጠባቸው አካባቢዎች ትምህርት እንዲጀመር በታላቅ ቁርጠኝነት አውጆ የነበረ ሲሆን፤ ይህ ራዕይ ዛሬ ፍሬ አፍርቶ በቁጥጥር ስር ባሉ ቀጠና
+3
202ኛ ኮር 🙏 👉 የአማራ ፋኖ በአማራ ከልል ትምህርት በተቋረጠባቸው አካባቢዎች ትምህርት እንዲጀመር በታላቅ ቁርጠኝነት አውጆ የነበረ ሲሆን፤ ይህ ራዕይ ዛሬ ፍሬ አፍርቶ በቁጥጥር ስር ባሉ ቀጠናዎች ሁሉ አገር አቀፍ የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በድል እየተሰጠ ይገኛል። የአገዛዙ ካድሬዎች ትናንት "ትምህርት ተስተጓጎለ" ብለው የለፈፉበትን ፕሮፓጋንዳ ዛሬ የአማራ ፋኖ የውሃ ሽታ አድርጎታል። ህዝቡን በባርነት ለመግዛት የሚጥሩት ስግብግብ ባለሥልጣናት፣ ፋኖ በፈጠረው የትምህርት ምህዳር ፊት መቆሚያ አጥተዋል። በጠመንጃ አስገድደው ሊያቆሙት ያልቻሉት ይህ ታላቅ የትምህርት እንቅስቃሴ፣ የአገዛዙን የውድቀት ጊዜ እጅግ እንዳፋጠነው ግልጽ ነው። የ202ኛ ኮር በጌምድር ክፍለ ጦር በሚያስተዳድራቸው ቀጠናዎች በአሁኑ ወቅት ሳንኪሳ፣ ፈንታይ፣ ናርቸቻ፣ ጨውድባ፣ ስምራ-ሮቢት፣ ገምበልዋ፣ ሰራቆ፣ ጉራንባ፣ ደምቢያ ሮቢት፣ ሰራባ፣ ዳብሎ ሚካኤል እና አቸራን ጨምሮ በበርካታ ቀጠናዎች የትምህርት ሂደቱን በጀግንነት እያካሄደ ይገኛል። ​ይህ ክንውን፣ ፋኖ የትውልድን የወደፊት ዕድል ለመጠበቅ የጦር ሜዳ ውሎውን ከትምህርት ገበታ ጋር አስተሳስሮ እንደሚንቀሳቀስ የሚያሳይ ታሪካዊ ማረጋገጫ ነው። ፋኖ የጦር ሜዳ ጀግና ብቻ ሳይሆን የህዝብ አስተዳዳሪ እና የወደፊት የኢትዮጵያ ተስፋ ጠባቂ መሆኑን በአደባባይ ያረጋገጠበት ነው። ክብር ለጀግኖቻችን🙏 ድል ለአማራ ፋኖ ✌️ ድል ለተገፋው የአማራ ህዝብ! ሰኔ 11/2018 ዓ.ም