ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
前往频道在 Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
显示更多2 936
订阅者
-324 小时
+3667 天
+38130 天
帖子存档
የራንቦ ክፍለ ጦር ልዩ የወታደራዊና ፖለቲካዊ አቅም ግንባታ ተሃድሶ መርሃ ግብር አካሔደ!!
ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም
የአፋበን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የአፄ አምደ ፅዮን ኮር አካል የሆነው የራንቦ ክፍለ ጦር የተሳካ ልዩ የፖለቲካና ወታደራዊ አቅም ግንባታ ስልጠና (ተሃድሶ) ማድረጉን የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል አስታወቀ።
ከሐምሌ 01-16/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት የድርጅትና የዕዝ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ስልጠናው ሲጠናቀቅ በተጋባዥነት የተገኙት የአፋብን ተ/ምክትል ሊቀመንበር አርበኛ መከታው ማሞ በተገኙበት ተጠናቋል። የዚህ ልዩ የተሃድሶ መርሃ ግብር ዋና ዓላማዎች፦
➧ የዓላማ አንድነት መፍጠር፦ ስለ ትግሉ አሁናዊ ሁኔታ፣ ስለ ማህበረሰብ አያያዝ እና ስለ ውስጣዊ አንድነት
➧ ስለ ጠላት አሰላለፍና ቁመና
➧ በወታደራዊ ታክቲኮች
➧በፖለቲካ ግንባታ
በነዚሕ አንኳር ነጥቦች ላይ ስልጠናውን አጠናቋል። በስልጠናው በማጠቃለያ መርሀግብር ላይ የተጋበዙት የአፋብን ተ/ምክትል ሊቀመንበር አርበኛ መከታው ማሞ " ከግል ቤታችን ወጥተን የጋራ ቤታችን በሆነው ድርጅት መሠባሠባችን ለአማራ ታሪካዊ" ያሠኘዋል ሲሉ ገልፀዋል። የመድረኩ ተሳታፊ የሆኑት የኮርና የክፍለ ጦሩ አመራሮችና አባላት በሰጡት አስተያየት፤ መድረኩ ቀደም ሲል የነበሩ በርካታ ብዥታዎችን ያጠራና የተናጠል ትግሉን ወደ ህብረትና ብቃት አረጋጋጭ ሊሆን እደሚችል ገልጸዋል። ለህልውና ትግሉ የሚከፈለውን መስዋዕትነት በሙሉ ልብ ለመወጣትና ድርጅቱ ካስቀመጠው ግብ ላይ ለመድረስ ቁርጠኛ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
"ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!
"ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
16/11/2018 ዓ.ም
ከሲያደብርና ዋዩ ወረዳ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ ዘርያዕቆብ ኮር በነጎድጓድ ክ/ጦር ግንቦት ወር ላይ በልዩ ኦፕሬሽን የተያዙት የኦሮሞ ብሔር ተወላጅ የሆነው የሚሊሻ አመራር አቶ ነጋሽ ተስፋዬ የሰጡት ቃለ-ምልልስ :-
===================
-የፋኖ አያያዝ በጎና፣ለተቋምሕግ እና ሰብአዊነት የተገዛ ነው።
-ፋኖ አላማ ያለው ሀይል እንጂ ከዬትኛውም ሕዝብ ጋር ጥል የለውም። -ጠላቱ የብልፅግና አገዛዝ ብቻ መሆኑን አይቻለሁ። የሚሉና ለአድማ ብተና እና ሚሊሻ ያቀረቡት ጥሪ :-
+4
አራት የአገዛዙ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ከነ ሙሉ ትጥቃቸው የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦርን ተቀላቀሉ!
ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም
የብልፅግናው ስርዓት ግብዓተ-መሬቱ መቃረቡን ተከትሎ ከመቸውም ጊዜ በላይ ጦረኛው አገዛዝ የሚመካበት ወታደሮች አነ ሙሉ ትጥቃቸው ንቅናቄውን እየተቀላቀሉ ሲሆን ትላንት ረብዕ አራት የመከላከያ ሰራዊት አባላት ከነ ሙሉ ትጥቃቸው የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ ዓምደ ጽዮን ኮር የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦርን ከነ ሙሉ ትጥቃቸው መቀላቀላቸውን የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል በምስል አስደግፎ ለዕዙ የዜና ክፍል በላከው የግንባር መረጃ አስታውቋል።
ወደ ፋኖ ከተቀላቀሉት ውስጥ 3ቱ የ15ኛ ክፍለ ጦር አባላት ሲሆኑ አንዱ የ101ኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦር አባል መሆኑን ኮሩ አክሎ ገልጿል።
"ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!
"ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
🎯 ፍትሐዊው ባለ ሚዛን!
(አዲሱ ደረበ)
የአማራ ሕዝብ ሁሌም ቢሆን ፍትሐዊ፣ ባለሚዛንና ሥርዓት አዋቂ ሕዝብ ነው። ለመንግሥት፣ ለሕግና ለመንግሥታዊ አሠራር ያለው ቀናኢነትና አክብሮት ለዘመናት የጸና ቢሆንም፣ ይህ በጎ እሴቱ ግን ግፍና ጭቆና በእርሱና በወገኖቹ ላይ ሲጫኑ እጁን አጣጥፎ እንዲቀመጥ አድርጎት አያውቅም። ዛሬማ ይልቁን በአማራዊ ማንነቱ ላይ የህልውና አደጋና የዘር ማጥፋት ጥቃት ተደቅኖበት እንዴት ዝም ይላል? ወትሮም ቢሆን ኢ-ፍትሐዊነትንና ጥቃትን እምቢ ለማለትና ለመፋለም ቦዝኖ የሚያውቅ ሕዝብ አይደለም!
እውነቱ አሁን እንደሚታየው ነው፤ እንኳን አሁን መላው አማራ በየአቅጣጫው አለሁ ብሎ በአንድነት ተሰልፎ ይቅርና፣ ወትሮም ቢሆን በየትኛውም አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ በአጥቢያው ተደራጅቶ ግፈኞችንና ወራሪዎችን ለመታገል አንዲት ሰከንድ የማያመነታ ብርቱና ኩሩ ሕዝብ ነው። የታሪክ መዝገብ ለዚህ ሕያው ምስክር ነው፤ የፋሽስት ጣሊያንን እብሪትና ወረራ፤ ዘመናዊ የጦር መሣሪያና የመርዝ ጋዝ ሳይበግረው ዱር ቤቴ ብሎ ተፋልሟቸዋል። በቀደሙት ስርአቶች ሁሉ የመሬት ግብር ጭቆና በበረታበት ወቅትም፣ የማይከሰሱና የማይጠየቁ የሚመስሉትን መሳፍንቶች አልገብርም ብሎ በመሬት ግብር እምቢተኝነት አንቀጥቅጧቸዋል።
በአህጉር ደረጃ ገናና ስምና ግዙፍ የጦር ግንባር የነበረውን የደርግን መራር ግፍና ቀይ ሽብር የመታገልና የመቋቋም ታሪካዊ ውርስ ያለው ነው፤ ለዚህም የጀግኖች ምድር አቸፈር፣ በለሳና ሰቆጣ ሕያው ምስክሮች ናቸው። እንዲሁም የወያኔ ኢሕአዴግን ዘረኛ አገዛዝ ከዘረኝነት፣ ከጠባብነትና ከመድሎ እንዲወጣ ያለ ምንም ፍርሃትና ተሸማቃቂነት በአደባባይ የተጋፈጠውና የታገለው ይኸው ሕዝብ ነው።
ዛሬማ መደራጀት፣ መቀራረብና በጋራ የአማራነት ጉዳይ ላይ በጋራ መሰለፍን ዘመኑም፣ የታሪክ አጋጣሚውም ፈቅዶለታል! ትናንት የፋሽስት ጣሊያን የመርዝ ጋዝ ያልበተነውና ያላበረከከው ሕዝብ፣ ዛሬ በፋሽስቱ አብይ አሕመድ ድሮን በፍጹም አይንበረከክም። የደርግን አሰቃቂ ቀይ ሽብር በጽናት የተሻገረው አቅሙ፣ በዛሬው ገዢ ቡድን የዘር ማጥ*ፋት ዘመቻ አይፈታም። የወያኔ የትጥቅ ማስፈታት አዋጅና በሐውልት ማቆም አንገት አስደፊነት ተግባር ያልተሰበረው ወኔ፣ በዛሬው የብአዴንና የአገዛዙ ሱሪ የማስፈታት ዘመቻ ከቶ ድል አይደረግም።
ጥቅሙን፣ ጉዳቱንና ክብሩን አሳምሮ የሚያውቅ፣ ፍትሐዊ ባለሚዛን የሆነው የአማራ ሕዝብ—ትናንት ጅራፍ እያጮኸ ያልተሰማውን አጠቃላይ ብሶቱን፣ ዛሬ በእውነተኛው የፋኖ ክንድና በጥይት አረር እየታገለ፣ መብቱንና ሕልውናውን እያስከበረ ይገኛል። ከትናንት እስከ ዛሬ ባልተለወጠው የገዢዎች ክፋት፣ ሴራና የወገናችን መራር አኗኗር ውስጥ አንድ ቋሚና የማይናወጥ ትልቅ እሴት አለ፤ እርሱም የአማራ ሕዝብ እምቢ ባይነትና የማይበገር ወኔ ነው!
ድል ለአማራ የህልውና ትግል! 🎯
በጦር ሜዳ ላይ የሚፈሰው ደም ሁሉ የሚጠራው ሞትን አይደለም አንዳንዱ ደም የፍቅር፣ የፅናት እና የጓደኝነትን ህይወት የማዳን ብቃት ጭምር እንጅ!
የሸዋ ምድር በባሩድ ጭስ ስትሸፈን። የነጎድጓድ ያህል የሚያንቀጠቀጠው የመድፍ ድምፅ የአየር ላይ ውጥረት ሲፈጥር፣ በዚያ ሁሉ ሁከት መካከል ግን ታላቁ የአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ንጉሣዊውንና ታሪካዊውን ዓፄ ዘርዓያዕቆብ ፩ኛ ኮርን አስከትሎ የወገናቸውን ክብር ለማስጠበቅ በጽናት ይፋለማል። በዚያ የትግል አውድማ ውስጥ የሚገኘው የነጎድጓድ ክፍለጦር ደግሞ የጠላትን አጥር የሚሰብረው በመብረቃዊ እርምጃው ነው።
ነገር ግን የዚህ ሁሉ ታላቅነት እውነተኛው ሚስጥር ያለው በመሳሪያው ጥንካሬ ላይ ብቻ አይደለም። የጥይት ማዕበሉ ሰማዩን ሲሰነጥቀው፣ በደም የተጨማለቀውን የትግል ጓዱን አቅፎ የሚቃተት ህይወቱ በሰከንዶች መካከል ልትጠፋ ስትል... ከባሩዱ ጭስ መካከል በፍጥነት እየሮጡ የሚመጡ የብርሃን መላእክት ናቸው ።
እነሱም የነጎድጓድ ክፍለጦር ህክምና ቡድን የራሳቸውን ደረት ለጥይት መስጠት የሚያስፈራቸው ጊዜ የለም፤ ምክንያቱም በእጃቸው ላይ ያለው የጓደኛቸው ውድ ሕይወት ነው። አትተውኝ በሚል ድምፅ የተናገረውን የትግል አጋራቸውን አቅፈው ሲያነሱ፣ የሕክምና ቡድኑ አባል እንባውን እየጠረገ በጆሮው አልተውህም እስከመጨረሻዋ የልብ ምቴ ድረስ አልተውህም ዛሬ እኔ እየተነፈስኩ የአንተ ህይወት አታልፍም የሚሉ ተወርዋሪ ተርቦች እንጅ!
መድኃኒታቸው ቁስልን ብቻ አይደለም የሚያከመው የተሰበረውን መንፈስ ይጠግናል፣ ተስፋ የቆረጠውን ልብ መልሶ ያስመታል።በዓፄ ዘርዓያዕቆብ ፩ኛ ኮር በነጎድጓድ ክፍለ ጦር የሚገኙት እነዚህ የሕክምና ጀግኖች፣ በጦርነቱ እሳት መሃል የቆሙ እውነተኛ የፍቅርና የጽናት አምዶች ናቸው። ጠላት በጥይት ሲያፈርስ እነሱ በእጃቸው ሕይወትን ይገነባሉ እነሱ በጦርነቱ ነጎድጓድ ውስጥ የሚበሩ፣ ሕይወትን የሚያስቀጥሉ የወገን አለኝታዎች ናቸው!
ሰበር አሳዛኝ መረጃ!!
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የደቡብ ወሎ ሐገረ ስብከት የዓባይ ቅድስት አርሴማ ገዳም 7(ሰባት) መነኮሳት በድሮን ህይወታቸውን አጡ።
ዛሬ ሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ዓባይ በረሃ ያለችዋ ቅድስት አርሴማ ገዳም መነኮሳት በፀሎተ ቅዳሴ ላይ እያሉ በደረሰባቸው የአካንች ድሮን ድብደባ ሰባት መነኮሳት ወዲያውኑ ህይወታቸው ሲያልፍ 10 መነኮሳት ደግሞ በከባድ ሁኔታ ቆስለዋል።
ዓለም በቃኝ ብለው የመነኑ ገዳማውያን ጭምር ለመጨፍጨፍ ርህራሔ የሌለው አረመኔው የብልፅግና አገዛዝ ተመሳሳይ የዘር ማጥፋት ወንጀሎችን በቤተ ክህነቷ አባቶች፣ መናንያን እና ምዕመናን ላይ እንዲሁም በአማራ ህዝብ ላይ በጅምላ መፈፀም ከጀመረ ዓመታትን አስቆጥሯል።
ይህንን ስርዓት መታገል ሀገርን እና ህዝብን ማዳን ነው።
+8
ሰበር አሳዛኝ መረጃ!!
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የደቡብ ወሎ ሐገረ ስብከት የዓባይ ቅድስት አርሴማ ገዳም 7(ሰባት) መነኮሳት በድሮን ህይወታቸውን አጡ።
ዛሬ ሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ዓባይ በረሃ ያለችዋ ቅድስት አርሴማ ገዳም መነኮሳት በፀሎተ ቅዳሴ ላይ እያሉ በደረሰባቸው የአካንች ድሮን ድብደባ ሰባት መነኮሳት ወዲያውኑ ህይወታቸው ሲያልፍ 10 መነኮሳት ደግሞ በከባድ ሁኔታ ቆስለዋል።
ዓለም በቃኝ ብለው የመነኑ ገዳማውያን ጭምር ለመጨፍጨፍ ርህራሔ የሌለው አረመኔው የብልፅግና አገዛዝ ተመሳሳይ የዘር ማጥፋት ወንጀሎችን በቤተ ክህነቷ አባቶች፣ መናንያን እና ምዕመናን ላይ እንዲሁም በአማራ ህዝብ ላይ በጅምላ መፈፀም ከጀመረ ዓመታትን አስቆጥሯል።
ይህንን ስርዓት መታገል ሀገርን እና ህዝብን ማዳን ነው።
+3
በእነማይ ወረዳ ወይራ ጠልማ ቀበሌ የሚገኘው የአገዛዙ ቅጥረኛ የሚሊሻ አባላት 64ኛ ክ/ጦር እየተቀላቀሉ ይገኛል።
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
በአማራ ህዝብ ላይ በረካታ ግፎችን እየሰራ የሚገኘው የአብይ አህመድ አገዛዝ መንገድ መሪ የነበሩ ቅጥረኛ የሚሊሻ አባላት አገዛዙ በህዝባችን እየፈፀመ ያለውን ብልሹ አሰራር ምክንያት ከጠልማ ቀበሌ ከአገዛዙ የሚሊሻ ካንፕ በመውጣት ወደ ፋኖ ተቀላቅለዋል።
1ኛ.አወቀ ባሤ ዘላለም ሚሊሻ አንድ ኮሪያ ክላሽ 90 ጥይት 2 ካዝና
2ኛ.ሸገዉ ቢደርሥ አለሙ ሚሊሻ አንድ ኮሪያ ክላሽ 75 ጥይት
3ኛ.ባዩ እጅጉ ልመንህ ሚሊሻ ብሬን እረዳት አንድ ኮሪያ ክላሽ 30 ጥይት በመያዝ አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ተቀላቅለዋል።
አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!!
ሐምሌ15/2018 ዓ.ም
አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት
+1
23ኛ ክ/ጦር ወታደራዊ ድል አስመዝግቧል‼️
በአፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 104ኛ ኮር ስር የ23ኛ ክ/ጦር አርበኞች ሰሞኑን ባደረጉት ከባድ ተጋድሎ ከወታደራዊ አዛዦች ጀምሮ የጠላትን ጦር ቆርጦ በመደምሰስና ለሕልውና ትግሉ ወሳኝ የሆኑ የቡድንና የነፍስ ወከፍ የጦር መሣሪያዎችን በመማረክ አንፀባሪቂ ድል ተቀዳጅተዋል።
15/11/2018 ዓ.ም
ሁለት የፓራ ኮማንዶ አባላት ከነሙሉ ትጥቃቸው የአፋብን 54ኛ ክፍለ ጦርን ተቀላቀሉ
[አሻራ ሚዲያ ሐምሌ 15/2018 ዓ.ም]
በምስራቅ ጎጃም ዞን በሕዝቡ ላይ ግፍና በደል ሲፈጽም ከቆየው የብልፅግና ሥርዓት ሰራዊት የመክዳትና ወደ ሕዝባዊ ወገን የመቀላቀሉ እንቅስቃሴ ይበልጥ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
ከምስራቅ ጎጃም ዞን ሞጣ ወረዳ የነበሩ ሁለት የብልፅግና ሥርዓቱ የፓራ ኮማንዶ ኃይል አባላት—ጌታሰው ፈንቴ እና ይታየው ፍላቴ—የአገዛዙን ጨካኝ አካሄድ በመቃወም ከነሙሉ ወታደራዊ ትጥቃቸው በመክዳት የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 54ኛ ክፍለ ጦርን ተቀላቅለዋል።
ወደ ወገናቸው የተቀላቀሉት እነዚህ የፓራ ኮማንዶ አባላት የደረሱበት ቦታ ሲደርሱ፤ የ54ኛ ክፍለ ጦር ምክትል ሰብሳቢ ሻለቃ ሰፊ፣ የ54ኛ ክፍለ ጦር የኮማንዶ ኃይል አዛዥ ሻለቃ ይከበር የሽዋስ እንዲሁም ሌሎች የወታደራዊ ክፍሉ አመራሮች በተገኙበት እጅግ ደማቅና ወታደራዊ ክብር የተሞላበት አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
የአሻራ ሚዲያ ያነጋገራቸው እነዚህ የክፍለ ጦሩ አመራሮች በሰጡት አስተያየት፤ የአገዛዙ የጀርባ አጥንት የነበሩ የልዩ ኮማንዶ አባላት የሕዝባቸውን ጥሪ ተቀብለው ከነመሣሪያቸው መቀላቀላቸው የአገዛዙ ሰራዊት ያለበትን ከፍተኛ የሥነ-ልቦና ስብራትና የውድቀት ማፋጠን ማሳያ መሆኑን ገልጸው፣ አሁንም በስህተት ውስጥ የሚገኙ የአገዛዙ ወታደሮች የጌታሰውና የይታየውን አርአያነት በመከተል ወደ ሕዝባዊ ትግሉ እንዲቀላቀሉ ጥሪ አቅርበዋል።
አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ! አዲስ ተስፋ!
ሐምሌ 15/2018 ዓ.ም
አሻራ ሚዲያ/ኃይሌ ሙሉ
የዳዊትና የጎልያድ ትንቅንቅ በደጋ ዳሞት ምድር!
አስራ አንድ የጦር መኮንኖች በአንድ ሻለቃ ፊት ግራ ሲጋቡ! የጦር ሜዳ ሳይንስንና የኃይል ሚዛንን ሙሉ በሙሉ ያቃወሰው የደጋ ዳሞቱ ታሪካዊ ፍልሚያ!"
ዛሬ በታሪካዊቷና በቆራጦች ምድር በደጋ ዳሞት፣ ታሪክ በደማቅ ቀለም ዳግም ተጽፏል። የአራት ኪሎው አገዛዝ ያለ የሌለ ኃይሉን አሰባስቦ፣ በርካታ ከባድ መድፎችን፣ የታንክ ሰራዊትንና ዘመናዊ መሣሪያዎችን አስፎክሮ የላካቸውን 4 ጀነራሎች እና 7 ኮሎኔሎችን በአጠቃላይ 11 የጦር መኮንኖችን በአማራ ፋኖ ኩራት በሆነው በጀግናው ሻለቃ ዝናቡ ልንገረው የሚመራው የቴዎድሮስ ዕዝ አፈር ድሜ አብልቷቸዋል።
የመደበኛ ውትድርና ስልጠና የወሰዱት፣ የብረትና የመሳሪያ ብዛትን ተማምነው የመጡት እነዚህ አስራ አንድ ከፍተኛ የጦር መኮንኖች፤ የደጋ ዳሞትን ምድር በቁጥጥር ስር ለማዋል ትልቅ ዝግጅት አድርገው ነበር። ነገር ግን የጦር ስልትና የብረት ኃይል ብቻውን ውጊያን እንደማያሸንፍ የደጋ ዳሞቱ ፍልሚያ አስመስክሯል! የጠላት ዝግጅት፦ አራት ጀነራሎችና ሰባት ኮሎኔሎች፣ በከባድ መሳሪያዎችና በሰው ኃይል ታጅበው ገቡ። የፋኖ ምላሽ ሻለቃ ዝናቡ ልንገረው፣ የሕዝብን እውነተኛ የነጻነት ስሜትና የቴዎድሮስን ወኔ አንግቦ በጥቂት ታጋዮች የጠላትን ሰራዊት መላቅጡን አጠፋው!
አራት ጀነራሎችና ሰባት ኮሎኔሎች ተደማምረው በአንድ የፋኖ ሻለቃ አመራር ፊት መቆም አቅቷቸው ሲጨነቁ፣ ሲጠበቡና ወደኋላ ሲያፈገፍጉ ውለዋል። ይህ ክስተት የጦር መሳሪያ ብዛት ሳይሆን የሞራል የበላይነትና የታጋዩ እውነተኛ ወኔ ድል አድራጊ መሆኑን ለአለም አቀፍ ማህበረሰብ በግልጽ ያሳየ ህያው ምስክር ነው!
ይህ ተአምራዊ ድል በወታደራዊ ስልት ብቻ የተገኘ አይደለም፤ በደጋ ዳሞት አርሶ አደርና ቆራጥ ሕዝብ የማይወላወል ደጀንነት እንጂ! ሕዝቡ፦ ቀለቡን አዘጋጅቶ፣ መረጃውን አቅርቦ፣ ልቡንና ጸሎቱን ሰጥቶ ከጎን ቆመ! የቴዎድሮስ ዕዝ፦ የሕዝቡን አደራ አንግቦ የጠላትን ግርማ ሞገስ አፈር ድሜ አበላው!
የደጋ ዳሞት ምድር ዛሬም እንደ ትላንቱ የጀግኖች መብቀያ እንጂ የፈሪዎችና የአብይ አህመድ ወንበር አስጠባቂ መፈንጫ አትሆንም! የጀግናው ሻለቃ ዝናቡ ልንገረው ክንድና የፋኖዎች ወኔ ነገም አዲስ ታሪክ መስራቱን ይቀጥላል። ታሪክ አይረሳም! የእውነትና የነጻነት ጉዞ በደማቅ ድል መታጀቡን ይቀጥላል!
🔥 ድል ለአማራ ህዝብ
⭐️ ከፍታና ዝና ለጀግናው ሻለቃ ዝናቡ ልንገረውና ለቴዎድሮስ ዕዝ! አድርሱልኝ Dave Amhara
የድምሰሳ_ፕሮፓጋንዳው_ከሽፏል‼️ (ሰፋ ያለ እና የተሟላ ትንተና)
በጎጃም ምድር የተካሄደውን ወቅታዊ የጦርነት ሁኔታ እና የጠላትን እንቅስቃሴ በተመለከተ የሚከተሉት ዋና ዋና ነጥቦች ጎልተው ወጥተዋል።
1. የጠላት የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ እና የከባድ መሳሪያ ድብደባዎች
ምንም አይነት ወታደራዊ ድል ማስመዝገብ ያልቻሉት የሌተናል ጄኔራል መሐመድ ተሰማ (የምስራቅ ዕዝ) እና የሜጄር ጄኔራል ብርሃኑ ጥላሁን (የ6ኛ ዕዝ) የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ ሙሉ በሙሉ መክሸፉ ተገልጿል።
የጥቃቱ ስፋት፡ በጎጃም ምድር ከ275 በላይ የመድፍ ጥቃቶች ተፈጽመዋል።
የተሰማሩ የጦር መሳሪያዎች፡ ቢኤም (BM)፣ ዘ-23 (ZSU-23) እና ሞርተሮች ጥቅም ላይ ውለዋል።
የዒላማው ሁኔታ፡ ጥቃቶቹ ከ40 እስከ 20 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኙ ንጹሐን መንደሮች ላይ ያነጣጠሩ ነበሩ።
2. የአገዛዙ ሰራዊት አቋም እና የውጊያ ሁኔታ
የአገዛዙ እግረኛ ሰራዊት በሜዳ ላይ ምንም ዓይነት የውጊያ ፍላጎት እንደሌለው ተመላክቷል። ራሱን በረጅም እርቀት አስቀድሞ ለመከላከል ሲል በእያንዳንዱ እንቅስቃሴው መድፎችን እና ቢኤም (BM) በመጠቀም ያለ ምንም ትክክለኛ ውጊያ የንጹሐንን ሕይወት እየቀጠፈ ይገኛል። በዚህም የተነሳ በሰራዊታችን ላይ የደረሰ ምንም ዓይነት ጉዳት የለም፤ ይልቁንም የሜካናይዝድ ጥቃቱ ሙሉ በሙሉ በንጹሐን ዜጎች ላይ ያነጣጠረ ነው።
3. ከባድ መሳሪያ ጥቃት የተፈጸመባቸው አቅጣጫዎች እና አካባቢዎች
ሀ. የምስራቅ ዕዝ (ሌተናል ጄኔራል መሐመድ ተሰማ) የተንቀሳቀሰባቸው መስመሮች፦
ከአዲስ ቅዳም - ፋግታ - ፍኖተ ሰላም - ገነት አቦ - ጉጥልማ - ፈረስ ቤት
ከአዴት - ብር አዳማ - ጠጠር ማርያም - ሃሙስ ገበያ
ከአዴት - ዋሸራ - ገረገራ - አስተርዮ
ለ. 6ኛ ዕዝ (ሜጄር ጄኔራል ብርሃኑ ጥላሁን) የተንቀሳቀሰባቸው መስመሮች፦
ከደንበጫ - በአንጀኔ - ፈረስ ቤት
ከደንበጫ - ገሊላ - ዋዳን - ኮረብታ - ውሃበር
ከደብረ ማርቆስ - አማኑኤል - ደብረቀለሞ - ደጋሰኝ - ረዕቡ ገበያ
ከደብረ ማርቆስ - ረዕቡ ገበያ - ደብረዘይት
ከትኖራ - መርጡለ ማርያም - ሞጣ - ድጎፂዮን - ውሃበር
ከቁይ - ጎዛምን - ደባይ ጥላት ግን ደጋማ ክፍል
4. የሰራዊታችን አጸፋዊ እርምጃዎች እና ድሎች
የጠላትን ስልታዊ እቅድ ውድቅ በማድረግና ከሚጠበቀው ውጪ ጀብድ በመፈጸም ረገድ፦
206ኛ ኮር 34ኛ ክ/ጦር በኮርክ ከተማ ድል አስመዝግቧል።
102ኛ ኮር 33ኛ ክ/ጦር ደግሞ በምርኮ የቀጠለውን ውጊያ በዋሸራ አቅጣጫ አጠናክሮ ቀጥሎበታል።
