ch
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

前往频道在 Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

显示更多
2 941
订阅者
+224 小时
+3727 天
+36730 天
帖子存档
አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ 204ኛ ወንዱ አስቻለው ደሴ ኮር ታዲዬስ ታንቱ ክፍለ ጦር ድል ተቀዳጀ። ከአርባያ ከተማ አቅጣጫ ወደ ምዕራብ በለሳ ቀጠና  እሩኝ ከተማ የተንቀሳቀሰው  የአገዛዙ  ኃይል  ላይ ብርቱ ክንድ አርፎበታል። በዘለሜ እና ፍንጭ ሚካኤል ሁለት  አቅጣጫ የገባው  የአገዛዙ ሰራዊት  ሐምሌ 28 /2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 12:00 --6:15 ሰዓት በቆየ አውደ ውጊያ ከፍተኛ ድል ተቀዳጅቷል። ጠላት ከተንቀሳቀሰበት አርባያ መረጃው የነበረው ክፍለ ጦሩ ወታደራዊ እስትራቴጂካዊ ቦታዎችን በመለየት 11 የመከላከያና የሚሊሻ አካላት የደመሰሰ ሲሆን፣ ከ20 በላይ ቀላል እና ከባድ የአካል ጉዳት አድርሶበታል። ​ያቀደውን ወታደራዊ ግብ ማሳካት ያልቻለውና በደረሰበት ከፍተኛ ምት ሞራሉ የፈረሰው የጠላት ኃይል ፣ከፊት ለፊት ውጊያው በመሸሽ በንጹሃን ዜጎች ላይ ጭፍጨፋ ፈጽሟል፣ ድብደባና እንግልት አድርሷል ፣በኃብትና ንብረት ላይ ጉዳት አድርሷል። 1ኛ.አቶ አድነው ሙጨ====በአገዛዙ የተረሸነ የእሩኝ ከተማው ባላሀብት፤ 2ኛ.ወ/ሮ ዙፋን አንባቸው==== በአገዛዙ የተረሸነች የከተማው ነዋሪ፤ 3ኛ.የግለሰብ የንግድ መንቀሳቀሻ ሞተር ተሽከርካሪ ጭነው ወስደዋል፤ 4ኛ.ሁለት በርሜል የህል ወፍጮ ነዳጅ በመድፋት ኪሳራ አድርሰዋል። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!

ሐምሌ 29/2018 ዓ.ም ​አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በበላይ ዘለቀ ዕዝ ግዙፉ ሜጀር ጀኔራል ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር ህዝባዊ ውይይት አካሄደ! ​ሐምሌ 29/2018 ዓ.ም የፋርጣ ወረዳ ሲቪል መዋቅር ከኮሩ ዋና ሰብሳቢ አርበኛ አመኑ አለማንተ ጋር በመተባበር ህዝባዊ የውይይት መድረክ አካሂዷል።​የፋርጣ ወረዳ ህዝባዊ አስተዳደር አባላት እና የኮሩ ዋና ሰብሳቢ በተገኘበተሰ በዚህ መድረክ፣ በእምባይኮ ቀበሌ ከ400 በላይ ቁጥር ያለው ህዝብ በተገኘበት ጥልቅ ውይይት ተካሂዷል። ​ህብረተሰቡ ጠንካራና ገንቢ ሀሳቦችን በማንሳት በሚከተሉት ዋና ዋና አጀንዳዎች የተወያየ ሲሆን፦ 1ኛ ​በወረዳው ጊዜያዊ ህዝባዊ አስተዳደር ውስጥ ያሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮች፤​ 2ኛ በወረዳው ጊዜያዊ አስተዳደር ውስጥ የሚታዩ ጠንካራና ደካማ ጎኖች፤ 3ኛ ​የአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ ዕዝ አመራርና የትግሉ ወቅታዊ ቁመና ( ጠንካራና ደካማ ጎኖች) ፤ እንዲሁም ህዝባችን ዕዙ ለሚሰጠው ማንኛውም ወታደራዊ ግዳጅ ያለውን ዝግጁነት በተጨማሪም ህዝባችን ትግሉን በአቋም መደገፍና በቁርጠኝነት መታገል እንዳለበት ሙሉ በሙሉ በመስማማት ሀሳብ ሰጥቶበታል። በትግሉ ውስጥ የሚታዩ አንዳንድ የመልካም አስተዳደር ችግሮች መስተካከል እንዳለባቸው ፤ እንዲሁም ህዝቡን አላግባብ የሚያንገላቱ የቀበሌ ሲቪል መዋቅር አመራሮች መጠየቅ እንዳለባቸው በዝርዝር በማንሳት የተሳካ ስብሰባ ማድረግ ተችሏል። ​የሜጀር ጀኔራል ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር ዋና ሰብሳቢ አርበኛ አመኑ አለማንተ በበኩሉ መልስና ማብራሪያ የሰጠ ሲሆን ህዝባችን እንደወትሮው ሁሉ ከጎናችን በመሆን መደገፍ እንዳለባቸውና የህልውና ትግሉም አሁን ላይ አንድ ወጥ በሆነ ድርጅት መስመር እየተጓዘ መሆኑን ገልጸዋል። ስለሆነም አደረጃጀቶቹ እስከ ታች ድረስ በመውረድ አፋብን ጠንካራ ሰራዊት እየገነባ መሆኑን በመጠቆም፣ይህ ደግሞ በአንድ ጊዜ ሳይሆን በሂደት እያደገ የሚሄድ መሆኑን ለተሰብሳቢው አስገንዝበዋል። ​በተጨማሪም የአማራ ህዝብ ከብልፅግናው አገዛዝ እየደረሰበት ያለው የህልውና አደጋ በቁርጥ ቀን ልጆቹ በፋኖ ብርቱ ክንድ በተጠናና በተደራጀ መንገድ እየተመከተ መሆኑን አስረድተዋል። በቀበሌም ሆነ በወረዳ የተቋቋመው ጊዜያዊ ሲቪል መዋቅር፣ አፋብን በሚያዘጋጀው መርህና ህገ-ደንብ መሰረት ህብረተሰቡን ማስተዳደር እንደሚገባው ተገልጿል። ​ከዚህ አሰራር ውጭ ህዝቡንና ትግሉን የሚጎትት ጊዜያዊ የሲቪል አመራር መጠየቅ እንዳለበት ጠቁመዋል። ይህም ሲደረግ በአፋብን የሚወርዱ መመሪያዎችን መሰረት በማድረግ፣ እስከ ታች ወርዶ ስልጠናና የአቅም ግንባታ በመስጠት ሊሆን እንደሚገባ ገልጸዋል። ስለሆነም የአማራ ህዝብ የተጋረጠበትን የህልውና አደጋ በተናበበ መልኩ መመከት፣ ለአሸናፊነት የሚያበቃ ጠንካራ አደረጃጀት መፍጠርና ታጋዩን ከመልካም አስተዳደር ችግሮች ማላቀቅ እንደሚያስፈልግ አጽንኦት ሰጥተው አስገንዝበዋል። ​ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! ​አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!

ሐምሌ 29/2018 ዓ.ም ​አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በበላይ ዘለቀ ዕዝ ግዙፉ ሜጀር ጀኔራል ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር ህዝባዊ ውይይት አካሄደ! ​ሐምሌ 29/2018 ዓ.ም የፋርጣ ወረዳ ሲቪል መዋቅር ከኮሩ ዋና ሰብሳቢ አርበኛ አመኑ አለማንተ ጋር በመተባበር ህዝባዊ የውይይት መድረክ አካሂዷል።​የፋርጣ ወረዳ ህዝባዊ አስተዳደር አባላት እና የኮሩ ዋና ሰብሳቢ በተገኘበተሰ በዚህ መድረክ፣ በእምባይኮ ቀበሌ ከ400 በላይ ቁጥር ያለው ህዝብ በተገኘበት ጥልቅ ውይይት ተካሂዷል። ​ህብረተሰቡ ጠንካራና ገንቢ ሀሳቦችን በማንሳት በሚከተሉት ዋና ዋና አጀንዳዎች የተወያየ ሲሆን፦ 1ኛ ​በወረዳው ጊዜያዊ ህዝባዊ አስተዳደር ውስጥ ያሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮች፤​ 2ኛ በወረዳው ጊዜያዊ አስተዳደር ውስጥ የሚታዩ ጠንካራና ደካማ ጎኖች፤ 3ኛ ​የአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ ዕዝ አመራርና የትግሉ ወቅታዊ ቁመና ( ጠንካራና ደካማ ጎኖች) ፤ እንዲሁም ህዝባችን ዕዙ ለሚሰጠው ማንኛውም ወታደራዊ ግዳጅ ያለውን ዝግጁነት በተጨማሪም ህዝባችን ትግሉን በአቋም መደገፍና በቁርጠኝነት መታገል እንዳለበት ሙሉ በሙሉ በመስማማት ሀሳብ ሰጥቶበታል። በትግሉ ውስጥ የሚታዩ አንዳንድ የመልካም አስተዳደር ችግሮች መስተካከል እንዳለባቸው ፤ እንዲሁም ህዝቡን አላግባብ የሚያንገላቱ የቀበሌ ሲቪል መዋቅር አመራሮች መጠየቅ እንዳለባቸው በዝርዝር በማንሳት የተሳካ ስብሰባ ማድረግ ተችሏል። ​የሜጀር ጀኔራል ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር ዋና ሰብሳቢ አርበኛ አመኑ አለማንተ በበኩሉ መልስና ማብራሪያ የሰጠ ሲሆን ህዝባችን እንደወትሮው ሁሉ ከጎናችን በመሆን መደገፍ እንዳለባቸውና የህልውና ትግሉም አሁን ላይ አንድ ወጥ በሆነ ድርጅት መስመር እየተጓዘ መሆኑን ገልጸዋል። ስለሆነም አደረጃጀቶቹ እስከ ታች ድረስ በመውረድ አፋብን ጠንካራ ሰራዊት እየገነባ መሆኑን በመጠቆም፣ይህ ደግሞ በአንድ ጊዜ ሳይሆን በሂደት እያደገ የሚሄድ መሆኑን ለተሰብሳቢው አስገንዝበዋል። ​በተጨማሪም የአማራ ህዝብ ከብልፅግናው አገዛዝ እየደረሰበት ያለው የህልውና አደጋ በቁርጥ ቀን ልጆቹ በፋኖ ብርቱ ክንድ በተጠናና በተደራጀ መንገድ እየተመከተ መሆኑን አስረድተዋል። በቀበሌም ሆነ በወረዳ የተቋቋመው ጊዜያዊ ሲቪል መዋቅር፣ አፋብን በሚያዘጋጀው መርህና ህገ-ደንብ መሰረት ህብረተሰቡን ማስተዳደር እንደሚገባው ተገልጿል። ​ከዚህ አሰራር ውጭ ህዝቡንና ትግሉን የሚጎትት ጊዜያዊ የሲቪል አመራር መጠየቅ እንዳለበት ጠቁመዋል። ይህም ሲደረግ በአፋብን የሚወርዱ መመሪያዎችን መሰረት በማድረግ፣ እስከ ታች ወርዶ ስልጠናና የአቅም ግንባታ በመስጠት ሊሆን እንደሚገባ ገልጸዋል። ስለሆነም የአማራ ህዝብ የተጋረጠበትን የህልውና አደጋ በተናበበ መልኩ መመከት፣ ለአሸናፊነት የሚያበቃ ጠንካራ አደረጃጀት መፍጠርና ታጋዩን ከመልካም አስተዳደር ችግሮች ማላቀቅ እንደሚያስፈልግ አጽንኦት ሰጥተው አስገንዝበዋል። ​ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! ​አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!

ብልጦች ነፍሳቸውን ያድናሉ ጅሎች በህይወት ሳይኖሩ እንኳ የት እንደ አሉ አይታወቁም ለቤተሰብ እዳ ይሆናሉ ለአንድ ወንበር አስጠባቂ ብለው ለማነኛውም የአገዛዙ ሰራዊት መፈራረሱን ቀጥሏል‼ በ404ኛ ህ
+2
ብልጦች ነፍሳቸውን ያድናሉ ጅሎች በህይወት ሳይኖሩ እንኳ የት እንደ አሉ አይታወቁም ለቤተሰብ እዳ ይሆናሉ ለአንድ ወንበር አስጠባቂ ብለው ለማነኛውም የአገዛዙ ሰራዊት መፈራረሱን ቀጥሏል‼ በ404ኛ ህዳሴ ኮር 95ኛ ክፍለ ጦር የነበሩ አራት የመከላከያ ሰራዊት አባላት በቀን 28/11/2018 ዓ.ም አገዛዙን በመክዳት የወገን ጦር የሆነውን የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 105ኛ ኮር 66ኛ ክፍለ ጦር 2ኛ ሻለቃን በይፋ ተቀላቅለዋል። ። የተቀላቀሉት አባላት ስም ዝርዝር፦ ✅ አስር አለቃ ከድር አሜ ✅ ም/አስር አለቃ አብርሃም ሞገሴ ✅ መሰረታዊ ወታደር ዮሐንስ ብላቴ ✅ መሰረታዊ ወታደር ሲሳይ ፍቃዱ የመከላከያ ሰራዊት አባላቱ ሲናገሩ፡- "አብይ አህመድ ለስልጣኑ ሲል የመከላከያ ሰራዊቱን እያስጨረሰና ህዝቡን በጅምላ እየጨፈጨፈ በመሆኑ፣ ይህን ግፈኛ አገዛዝ አንቀበልም!" ብለዋል። ድል ለአፋብን! ✊ አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!

የዓላማ ጽናት ተምሳሌትና የአማራ ህዝብ የመኖር ነፃነት አለኝታ አርበኛ አማረ ታዘዘ! ​ታላቅ አርበኛ ላስተዋውቃችሁ! (በእርግጥ አብዛኞቻችሁ ልታውቁት ትችላላችሁ) ​ስሙ አማረ ታዘዘ ይባላል፤ በታላቁ
የዓላማ ጽናት ተምሳሌትና የአማራ ህዝብ የመኖር ነፃነት አለኝታ አርበኛ አማረ ታዘዘ! ​ታላቅ አርበኛ ላስተዋውቃችሁ! (በእርግጥ አብዛኞቻችሁ ልታውቁት ትችላላችሁ) ​ስሙ አማረ ታዘዘ ይባላል፤ በታላቁ የዓፄ ዘርዓያዕቆብ ፩ኛ ኮር (አፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛህ አሳምነው እዝ) ውስጥ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ በመሆን ህዝብንና ሰራዊቱን በአንድነት አስተሳስሮ የሚመራ፣ የትግሉ አስተማማኝ አምድ ነው። ​ትግሉን በዕውቀት፣ በስልትና በመሪነት ጥበብ የሚያንቀሳቅስ ዘመናዊና ባለራዕይ አርበኛ ሲሆን፣ በሚከተሉት ታላላቅ እሴቶቹ ይታወቃል። በትምህርትና በዕውቀት የተካነ የዲግሪ ምሩቅ በመሆኑ የትግሉን አቅጣጫ በጠለቀ አስተዋይነት፣ በሰለጠነ አስተሳሰብና በበሰለ መሪነት ይመራዋል። ​በትግል አውደ ውጊያ ቆራጥና ጀግና፦ በሜዳው ላይ እጅግ ሲበዛ ታታሪና ወደፊት ተራማጅ ሲሆን፣ በርካታ የማይረሱ የጀግንነት ገድሎችን የፈጸመ የፊት አውራሪ ነው። በወታደራዊ ስልትና ብልሃት ረቀቅ ያለ፦ በጠላት በኩል የሚሸረቡ ስውርና ውስብስብ ሴራዎችን ቀድሞ በመገንዘብና በማንበብ፣ እነዚያን አደጋዎች በረቀቀ ጥበብ፣ በብቃትና በስልት የማከሸፍ ልዩ ችሎታ ያለው መሪ ነው! ​በምንም ዓይነት ማስፈራሪያ፣ ፈተናና መከራ የማይበገር፣ ለተሰለፈበት ህዝባዊ ዓላማና ነፃነት ቅድሚያ የሰጠ፣ የማይናወጥ የብረት አቋም ባለቤት ነው! ​ይህ ቆራጥ አርበኛ እውነተኛ የአባቶቹ ልጅ ነው፤ ታሪካዊቷ የሸዋ ምድርም እንግዲህ እንደነዚህ ያሉ ለዓላማቸው የታመኑ፣ ወደኋላ የማይሉና ለህዝባቸው ጋሻ የሆኑ ጽኑ አርበኞች የታደለች ፍጹም የጀግኖች መፍለቂያ ናት! Amare Tazeze አማረ ታዘዘ አርበኛው በርታ! የሽዋ መሬት ያበቀለችው የአማራ ህዝብ የመኖር ነፃት አለኝታና ኩራት ፈጣሪ ይጠብቅህ! ታናሽ ወንድምህ Dave Amhara

ይበልጣል መኮንን አድስ አለም ክ/ጦር በአገዛዙ ጥምር ጦር ላይ  ድል ተቀዳጀ። የአፋብን ወለጋ/ቢዛሞ አንሻ ሰይድ ዕዝ ይበልጣል መኮነን አድስ አለም ክ/ጦር በቅርቡ የሪፎርም ስራ ካከናወነ ቦኋላ እደተለመደው በአገዛዙ ኃይሎች ላይ ትልልቅ ድሎቺን እያስመዘገበ ይገኛል። ትናት የኔቶርክ አክሰሶችን በሙሉ በማጥፋት እኩለቀን የተጀመረ አውደውጊያ መነሻውን በምስራቅ ወለጋ ኪረሞ ወረዳ ሀሮ ከተማ በመድረግ ወደባጊን ቀበሌ በተቀሳቀሰ የጥላት ጥምር ጦር እርምጃ ተወሰደበት። ጥላት የደረሰበትን ምት መቋቋም አቅቶት አስከሬኑን በየቦታው በማዝረክረክ እና በረካታ ቁስለኞቺን በመኪናዎች በመጫን መገዶቺን ክርቺም አርገው በመዝጋት የአንሻ ሰይድ ዕዝ አናብስቶቺ ውስጥ ላይ እየተርመሰመሰ ይገኛል።አውደ ውጊያውም ዛሬም ላይ እደቀጠለ ሲሆን ተለዋጭ ነገሮች ሲኖሩ የምናሳውቅ ይሆናል። ግፍ የወለደን:ግፈኞቺን የምቀጣ የአንሻ ሰይድ ወድሞች ነን‼️ አፋብን ወለጋ/ቢዛሞ አንሻ ሰይድ ዕዝ ምክትል የህ/ግንኙነት መምሪያ     ነሐሴ 29ቀን2018ዓም

ለአጣዬ(ኤፌሶን) ከተማ ነዋሪወች የተሰጠ የቅድመ ጥንቃቄ መግለጫ ። በኤፍራታና ግድም ወረዳ፣ የስምጥ ሸለቆዋ እንብርት የአትክልት እና ፍራፍሬዋ ባለቤት፣ብዙ አርበኞች የተሰውባት እና የቆሰሉባት የደም ከተማ ዛሬም ከተማዋን ነጻ ለማውጣት ብዙወች ከጥላት ጋር አንገት ለአንገት ተናንቀው በዱር በገደሉ የሚዋደቁላት ታሪካዊቷ አጣዬ ከተማ በከባድ ውጥረት፣ ስጋት እና ሰቆቃ ውስጥ ትገኛለች። የአረመኔው ዐቢይ አሕመድን ወንበር ለማስጠበቅ የሚሯሯጡ የብአዴን ቅጥርኞች፣ ከተማዋን እና የአካባቢውን ነዋሪዎች መሬት እንደ ዳቦ ቆራርሰው እየተቀራመቱት እንደሚገኙ ከስፍራው የሚወጡ መረጃዎች አረጋግጠዋል። ​በከተማዋ ከፍተኛ ስትራቴጂካዊ እና የኢኮኖሚ እሴት ያላቸው አልማ፣ዝግባ እንዲሁም ሰላማ የተባሉ ለም መሬቶች ለፖለቲካ ፍጆታ እና ለወረዳ አመራሮች ለኦህዴድ መከላከያ አመራሮች እጅ መንሻ እየዋለ ውሎ አድሯል። በቦታዎቹ ​ለመከላከያ ሰራዊት አመራሮች ህጋዊ ሽፋን ለመስጠት ሲባል ሙሉ ካርታ እና ፕላን ተዘጋጅቶ እየተሰጣቸው ይገኛል። የሰራዊቱ አመራሮችም የተሰጣቸውን ካርታ እና ፕላን መነሻ በማድረግ ሰሞኑን ቦታዎቹን በከፍተኛ ዋጋ በመሸጥ ላይ ሲሆኑ ​ለሚሊሻ አባላት፦ በአንጻሩ ለአካባቢው ጥበቃ ከፊት የሚሰለፉት ሚሊሻዎች ያላካርታ እና ፕላን ባዶ መሬት ብቻ እንዲረከቡ በመደረጉ ምንም አይነት የመጠቀም ወይም የመሸጥ መብት እንዳይኖራቸው ተደርጓል። እንዲሁም ​የከተማዋን ምጣኔ ሀብት እና የንግድ እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር ለማዋል የታለመ አዲስ መመሪያ በማውጣት ​ማንኛውም ባለሀብት መሬት መሸጥም ሆነ መግዛት በግልጽ የተከለከለ መሆኑን እያወቁ​ ይህንን መመሪያ ተላልፎ መሬት ለመግዛት ወይም ለማልማት የሚሞክር ማንኛውም ባለሀብት፣ የገዛው ንብረት እና መሬት ድርጅታችን እርምጃ ይወስዳለ በዚህ ድርጊት ላይ ተሳትፎ የተገኘ አካል ለሚወሰደው ማንኘውንም እርምጃ ድርጅታችን ሀላፊነት አይወስድም የተወረረው መሬትም እንደሚወረስ ጥብቅ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል። ​ይህ አሰራር የከተማዋን ነፃ የንግድ እንቅስቃሴ ያነቀ እና ህዝቡን በራሱ መሬት ላይ የበታች ያደረገ እንደሆነ ነዋሪዎች በምሬት ይናገራሉ። ​የአማራ ፋኖ አሳምነው ዕዝ የሰባት ለሰባ ክፍለ ጦር ​በአጣዬ ከተማ እና በበደለው ህዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለውን የመሬት ቅርጫ፣ አድልዎ እና የኢኮኖሚ ውክባ ለማስቆም አስፈላጊውን አብዮታዊ እርምጃ እንደሚወስድ እና ​ክፍለ ጦሩ በአካባቢው የሚካሄደው ህገ-ወጥ የመሬት ሽያጭ እና የንብረት መቃረም በአስቸኳይ እንዲቆም ያስጠነቀቀ ሲሆን፣ ድርጊቱ የሚቀጥል ከሆነ ጥብቅ እርምጃ እንደሚወስድ ይገልጻል። " ክብር ለትግሉ ሰማዖታት ህልዉናችን በተባበረ ክንዳችን ! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነዉ ዕዝ ከ7ለ70 ክፍለ ጦር !!!

​በጀግኖቻችን ደም የተመሰረተውን አንድነታችንን እናጸናለን! ​ዳግማዊ ቴዎድሮስ 5ኛ ኮር ንስር በለሳ ቅጣው እጅጉ ክፍለ ጦር አመራሮችና አባላት ሐምሌ 05/2018 ዓ.ም በተበሰረው የጎንደር አንድነት
+1
​በጀግኖቻችን ደም የተመሰረተውን አንድነታችንን እናጸናለን! ​ዳግማዊ ቴዎድሮስ 5ኛ ኮር ንስር በለሳ ቅጣው እጅጉ ክፍለ ጦር አመራሮችና አባላት ሐምሌ 05/2018 ዓ.ም በተበሰረው የጎንደር አንድነት የተሰማቸውን ላቅ ያለ ደስታ የዕዝ አመራሮች በተገኙበት ገልጸዋል። ​ስለሆነም ለወደቁት ጀግኖቻችን ክብርና ለፈሰሰው ደም ስንል፣ ማንኛውም ዓይነት ቅሬታና ጥያቄ ቢኖር እንኳ ከወንድሞቻችን ጋር በአንድ ጥላ ስር፣ በገነባነው የአንድነት ቤት ውስጥ ሆነን በመወያየት መፍትሔ መስጠት እንደምንችል አጥብቀን እናምናለን ሲሉም አጋርተዋል። ​በቀን 28/11/2018 ዓ.ም ውይይት ያደረጉት አመራሮቹ፣ የጎንደርን አንድነት ለማምጣት በየግንባሩ የተከፈለው የወንድሞቻችን የሕይወት መስዋዕትነት እጅግ ከባድና ውድ በመሆኑ ይህን ማጽናት ደግሞ ታሪካዊ ግዴታችን ሊሆን ይገባል ያሉ ሲሆን፣ ለሚሰጠን ማንኛውም ግዳጅ ዝግጁ መሆናችንን እንገልጻለን ብለዋል። ​በመሆኑም የጠላትን አጀንዳ በመሸከም ለግል ጥቅማቸው ሲሉ አንድነትን ለማፍረስ የሚታትሩና የሕዝቡን ትግል የሚጠልፉ ፀረ-አንድነት ግለሰቦች ድርጊታቸውን በአስቸኳይ ሊያቆሙ ይገባል ብለዋል። ​በውይይቱ የተገኙት የአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ አመራሮች ለታላቁ የጎንደር ሕዝብና ላለፉት ጀግኖች የማይመጥኑ፣ ከየቁጥቋጦው ስር የሚሰጡ አደናጋሪ መግለጫዎች በአስቸኳይ ቆመው፣ ማንኛውም "ታጋይ ነኝ" የሚል አካል አለኝ የሚለውን ችግርና ጥያቄ በተገነባው ጠንካራ ቤትና መዋቅር ስር ብቻ ማቅረብ እንዳለበት አምኖ ወደ ቤቱ እንዲቀላቀል ሲሉ እናሳስባለን ብለዋል። ​ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!

አገዛዙ ሚሊሻን ወደ ትግራይ ድንበር ለግዳጅ ቢያዘጋጅም ሚሊሻው የአገዛዙን ትዛዝ በመቃወም ህዝባዊ ፋኖን እየተቀላቀሉ ይገኛሉ!! ~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~ በሸበል በረንታ ወረዳ የሚ
+2
አገዛዙ ሚሊሻን ወደ ትግራይ ድንበር ለግዳጅ ቢያዘጋጅም ሚሊሻው የአገዛዙን ትዛዝ በመቃወም ህዝባዊ ፋኖን እየተቀላቀሉ ይገኛሉ!! ~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~ በሸበል በረንታ ወረዳ የሚገኘው የአገዛዙ ቅጥረኛ ሰራዊት አባል የነበረው የሚሊሻ ተቋም እየፈራረሰ ይገኛል። በሸበል በረንታ የዕድውሃ ከተማ የሚገኘው ሚሊሻ ወደ ትግራይ ክልል ለግዳጅ ትሄዳላቹህ የሚል ትዛዝ መሰጠቱን ተከትሎ  የሚሊሻ አባላቱ ማመጡንና በአገዛዙ ተስፋ በመቁረጡን ተከተትሎ 64ኛ ክ/ጦር እየተቀላቀለ ይገኛል። በዚህም ምክንያት ሀምሌ 29/2018 ዓ.ም ሁለት የሚሊሻ አባላት ከነ ሙሉ ትጥቃቸው ህዝባዊ ፋኖ ተቀላቅለዋል። 1ኛ.ዋለበላይ አወቀ 2ኛ.ደመመው ጌታቸው የተባሉ የሚሊሻ አባላት አገዛዙ ያወጠውን ግዳጅ በመቃወም ከእነ ሙሉ ትጥቃቸው አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር አይበገሬው 64ኛ ክ/ጦር ተቀላቀሉ። አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!!              ሀምሌ 29/2018 ዓ.ም አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ

እውነተኛ አማራነት ከልብ የመነጨ ትህትና፣ ፍፁም አሳምነውነት እና ራስን አሳልፎ ለሰው ልጅ የመኖር ያ መራራ መስዋዕትነት ነው… ​ህይወት በእንባ፣ በቁስል እና በታፈነ ስቃይ መካከል ሆና ብዙ የጎረበ
+4
እውነተኛ አማራነት ከልብ የመነጨ ትህትና፣ ፍፁም አሳምነውነት እና ራስን አሳልፎ ለሰው ልጅ የመኖር ያ መራራ መስዋዕትነት ነው… ​ህይወት በእንባ፣ በቁስል እና በታፈነ ስቃይ መካከል ሆና ብዙ የጎረበጠ እውነት አስተምራኛለች። በየአቅጣጫው ያሉ ሆዳሞች እና ከሃዲዎች አማራዎች ከአረመኔው ብልፅግና በላይ የፈተኑኝ በደቡብ፣ በሰሜን፣ በምዕራብ፣ በምስራቅ እንደ ቀትር እባብ በመርዝ ተሞልተው ቢያሳድዱኝም፣ እውነተኛ አማራነት በባዶ ወሬ ሳይሆን በተግባር በናንተ ህይወት በምትከፍሉት አካላችሁ እና በከንቱ በፈሰሰው ደማችሁ ውስጥ አይቸዋለሁ። ​እውነተኛው የማንነት ህመም፣ ቅንነቱ እና ፍፁም ወንድማማችነት ለካ ያለው እዚያው በበርሃው ቁስላቸውን ደብቀው፣ ረሃብና ጥሙን ችለው ሌት ከቀን ዋጋ በሚከፍሉት እና በረገፉት የቁርጥ ቀን ልጆች ሰራዊት ውስጥ ብቻ ነበር። ​ነገ «አማራ» ብለው ዛሬ በጠላትነት እና በግፍ ሲያሳድዱን የነበሩት እናንተ በገበራችሁት፣ በመሬት ላይ እንደ ቅጠል በረገፈው ውድ አጥንት እና ደም ነው! ያ የከፈላችሁት መራራ እና የከበደ ዋጋ ዛሬ ለእኛ ሳንወድቅ እንድንቆም ብቸኛ መከታችን ይሆናል። ​ውድ የእኔዎቹ፣ ከእናንተ በፊት እኔን ክፉአችሁን አልስማ… ፈጣሪ ይጠብቃችሁ ከቁጥር አይቀንሳችሁ የእኔዎቹ ሰባት ለሰባ ፍፁም አማረነት ያየሁባችሁ!!! Dave Amhara

የአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ሰብሳቢ አርበኛ ዮሃንስ ንጉስ ሙጨ መልካም የሰራ ዘመን ይሁንልህ ወንድማለም ክበርልኝ Dave Amhara

+4
ሐምሌ 28/2018 ዓ.ም አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ 305ኛ ኮር ለተከታታይ ወራት ሲያሰለጥናቸዉ የቆዩ ሰልጣኞችን አስመረቀ!! አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ 305ኛ ኮር ለተከታታይ ወራት ሲያሰለጥናቸዉ የቆዩትን ወጣቶች ሐምሌ 27/11/2018 ዓ.ም የኮርና የክፋለ ጦር ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ አስመርቋል ። በምርቃቱ የተገኙት የኮርና የክፍለ ጦር አመራሮች ስልጠናው ተጀመረ እንጂ የመጨረሻዉ አለመሆኑን የገለጹ ሲሆን በአማራ ህዝብ ላይ እያደረሰዉ ያለዉ ግፍ ገንፍሎ በመፍሰስ ላይ ደርሷል ለህዝባችሁም ልደርሱለት ይገባል  ሲሉ አስገንዝበዋል። ይህን ስልጠና አጠናቃችሁ ለተመረቃችሁ ጀግኖች ልዩ ሚያደርገዉ ሁለት ጉዳዮች መሰረት ነው ያሉት አመራሮቹ:- ✏️አንደኛዉ አንድነቱ በተበሰረ ማግስት መሆኑ፤ ✏️ሁለተኛ ደግሞ የአማራ ፍኖ የትጥቅ ትግል በተቀጣጠለበት 3ኛ ዓመት ላይ መሆኑ ልትኮሩ ይገባል ሲሉ  መልዕክት አስተላልፈዋል። በመጨረሻም  ጀግኖቹ  የአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ተመራቂዎች ለዚች ቀን ለመድረስ ጀግናና ውድ  አርበኞች በየሸንተረሩ ደማቸዉን አፍሰዉ አጥንታቸዉን ከስክሰው  የክብር መስዋትነት ተቀብለው ትግሉን ከዚህ አድርሰዉታል። ስለሆነም ትግል በባህሪዉ ቅብብሎሽ እንደመሆኑ መጠን የሰማዕታትን አደራ ተቀብለን በአደርነት ትግላችንን ዳር እናደርሳለን ብለዋል። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!

ሐምሌ 28/2018 ዓ.ም አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ 305ኛ ኮር ለተከታታይ ወራት ሲያሰለጥናቸዉ የቆዩ ሰልጣኞችን አስመረቀ!! አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ 305ኛ ኮር ለተከታታይ ወራት ሲያሰለጥናቸዉ የቆዩትን ወጣቶች ሐምሌ 27/11/2018 ዓ.ም የኮርና የክፋለ ጦር ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ አስመርቋል ። በምርቃቱ የተገኙት የኮርና የክፍለ ጦር አመራሮች ስልጠናው ተጀመረ እንጂ የመጨረሻዉ አለመሆኑን የገለጹ ሲሆን በአማራ ህዝብ ላይ እያደረሰዉ ያለዉ ግፍ ገንፍሎ በመፍሰስ ላይ ደርሷል ለህዝባችሁም ልደርሱለት ይገባል  ሲሉ አስገንዝበዋል። ይህን ስልጠና አጠናቃችሁ ለተመረቃችሁ ጀግኖች ልዩ ሚያደርገዉ ሁለት ጉዳዮች መሰረት ነው ያሉት አመራሮቹ:- ✏️አንደኛዉ አንድነቱ በተበሰረ ማግስት መሆኑ፤ ✏️ሁለተኛ ደግሞ የአማራ ፍኖ የትጥቅ ትግል በተቀጣጠለበት 3ኛ ዓመት ላይ መሆኑ ልትኮሩ ይገባል ሲሉ  መልዕክት አስተላልፈዋል። በመጨረሻም  ጀግኖቹ  የአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ተመራቂዎች ለዚች ቀን ለመድረስ ጀግናና ውድ  አርበኞች በየሸንተረሩ ደማቸዉን አፍሰዉ አጥንታቸዉን ከስክሰው  የክብር መስዋትነት ተቀብለው ትግሉን ከዚህ አድርሰዉታል። ስለሆነም ትግል በባህሪዉ ቅብብሎሽ እንደመሆኑ መጠን የሰማዕታትን አደራ ተቀብለን በአደርነት ትግላችንን ዳር እናደርሳለን ብለዋል። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!

ለማፈን የተንቀሳቀሰው ጠላት ክፉኛ ተመታ። ሐምሌ 28/2018 ዓ.ም ከስማዳ ተነስተው ወደ ጅብጌ መድሀኒያለም፣ ሰበር ሚካኤል እና ቃጨና አቅጣጫ በመንቀሳቀስ 206ኛ ከፍያለው ደሴ ኮር በጀኔራል ኃይሌ
+3
ለማፈን የተንቀሳቀሰው ጠላት ክፉኛ ተመታ። ሐምሌ 28/2018 ዓ.ም ከስማዳ ተነስተው ወደ ጅብጌ መድሀኒያለም፣ ሰበር ሚካኤል እና ቃጨና አቅጣጫ በመንቀሳቀስ 206ኛ ከፍያለው ደሴ ኮር በጀኔራል ኃይሌ ዘ ውባንተ ክፍለ ጦር ላይ የማፈን ድርጊት ለመፈጸም የሞከረው የጠላት ኃይል በተወሰደበት የተቀናጀ የመልሶ ማጥቃት እርምጃ በጽኑ ተመቷል። ክፍለ ጦሩ ባካሄደው  ስልታዊ የመልሶ ማጥቃት ኦፕሬሽን፣ የጠላትን የማፈን አላማ ማክሸፍ የቻለ ሲሆን በሰውና በቁሳቁስ ላይ ከፍተኛ ኪሳራ በማድረስ የላቀ ድል አስመዝግቧል።ባለፉት ሁለት ቀናት በራስ ጋይንት ቀጠና ጨምሮ በተለያዩ የውጊያ ቀጠናዎች ከፍተኛ ፍልሚያዎች ያካሄደው እዛችን  የጠላትን ስልታዊ እንቅስቃሴዎች በማክሸፍ ከፍተኛ ምት አሳርፎበታል። በጠላት ላይ የደረሰ ቁሳዊ እና ሰባዊ ኪሳራ፦ ✏️15 መከላከያና አድማ ብተና ፖሊስ የተደመሰሰ፤ ✏️27 ቀላልና ከባድ ቁስለኛ፤ ✏️7 የነፍስ ወከፍ ክላሽ ኮቭ ትጥቅ የተማረከ ፤ ✏️123 የብሬን(መትረጊስ)፣የክላሽ ኮቭ ትጥቅ ተተኳሾች በምርኮነት ተገኘ። አንድነት ወታደራዊ አቅምን እና የጦር መሳሪያን አቀናጅቶ  ወደ አንድ ወሳኝ የድል ግብ የመቀየር ትልቁ ወታደራዊ ጥበብ መሆኑን የተረዳው ሰራዊታችን በድል አድራጊነቱ ኤየቀጠለ ይገኛል። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!

እኛ አማራዎች ሀገርን በጽኑ መሠረት ላይ የገነባን ሀገር መሥራች፤ በፍትሕና በዕውቀት የምንመራ ፍርድ አዋቂ፤የት ትውልድን አደራ ሳናጎድል ያቆየን ታሪክ ጠባቂ ነን! ​የራሳችንን መብትና ክብር አሳልፈን የማንሰጥ፤የሰውን መሬትና ሀብት ዓይናችን አፍጥጦ የማንፈልግ፤ በልባችን ውስጥ የወርቅ ያህል የጠራ ንጹሕ እምነት የያዝን ነን። ​ተፈጥሮ በራሷ እጅ ውብ አድርጋ ያበጀችን፤በወኔና በጽናት ጀግና አድርጋ የፈጠረችን፤ በባህላችንና በማንነታችን አንገታችንን ቀና ያደረግን ኩሩ ማኅበረሰብ ነን። ​እኛ ማንነታችን የተከበረ፣ ታሪካችን የጸና አማራ ኢትዮጵያዊ ነን! ብልጦች ነፍሳቸውን አትርፈዋል የአፋብን ጎጃም ጠቅላይ ግዛት ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር አናብስቶች ለብርሃኑ ጁላ ምርኮኛ ያደረጉት አቀባብል ተቸገርን እኮ ጎበዝ። Dave Amhara

የክቡር ሰማዕቱ ብርጋዲየር ጄነራል አሳምነው ፅጌ የስጋ ወንድም ሙሉጌታ ፅጌ በሕመም ምክኒያት ሕይወታቸው አልፏል። የብ/ጄነራሉ የስጋ ወንድም መምህር ሙሉጌታ ፅጌ ባጋጠማቸው ሕመም በሕክምና ሲረዱ ቆይ
+1
የክቡር ሰማዕቱ ብርጋዲየር ጄነራል አሳምነው ፅጌ የስጋ ወንድም ሙሉጌታ ፅጌ በሕመም ምክኒያት ሕይወታቸው አልፏል። የብ/ጄነራሉ የስጋ ወንድም መምህር ሙሉጌታ ፅጌ ባጋጠማቸው ሕመም በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ለትናንት ሐምሌ 27/2018 ዓ/ም አጥቢያ ለሊት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። ይሄንን ተከትሎ እናታቸው እማሆይ የውብሰፈር አሳየ እንዳረፉ ተደርጎ በማህበራዊ ትስስር ገፆች ሲሰራጭ የነበርው መረጃ ስህተት ነው።

የህዝብ እንባ፣ የሰው ህይወት እልቂት እና የባለስልጣናት ቅንጦት የ66 ሚሊዮን ብር እውነተኛው አሳዛኝ ገፅታ! #ይህችም #ትመዝገብ ​የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ ጉድህን ተመልከት፤ የአማራ ህዝብ ሆይ ማን በስሙ እንደሚነግድበትና ማን እንደሚያስጨርሰው ይመዝገብ! ​ዛሬ ሀገራችን ኢትዮጵያ በብዙ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፈተናዎች ውስጥ በምትገኝበት፣ ህዝባችን በከባድ የኑሮ ውድነትና በምግብ እጥረት እያለቀሰ ባለበት በዚህ አስቸጋሪ ወቅት በአንድ በኩል የሰው ህይወት እንደ ቅጠል የሚረግፍበት አሰቃቂ ድርጊት፣ በሌላ በኩል ደግሞ ሰማይን የሚያስቅና ምድርን የሚያስከፋ አሳዛኝ የህዝብ ሀብት ምዝበራ ከክልሉ ገንዘብና ኢኮኖሚ ቢሮ በወጣ የመንግስት ደብዳቤ ይፋ ሆኗል። የአማራን ህዝብ በአረብ ሀገር ድሮን እያስጨረሰ ያለ አርጋ ከበደ ቀንድ አውጣዝ አሰቃቂ እውነታ! ​ከሁሉ በላይ ልብን የሚያደምቀውና የሚሰብረው፣ አረጋ ከበደ የአማራን ህዝብ ንጹሃን እናቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች በአረብ ሀገር ድሮን እያስጨረሰና ደማቸውን እያፈሰሰ ባረፈበት ወቅት፣ በህዝቡ ስቃይ ላይ እየተደሰተ መሆኑ ነው። ​ንጹሃን ዜጎች በየቀኑ በድሮን ጥቃት እየተጨፈጨፉ፣ ቤተሰብ እየተበተነና መላው ክልል በለቅሶና በደም ውስጥ እያለ የህዝቡን ደምና እንባ የረገጠ አመራር ለአንድ ግለሰብ ድሎትና ቅንጦት በሚሊዮኖች የሚቆጠር ብር ሲመድብ ማየት አረመኔያዊነትና አሳዛኝ የህሊና ውድቀት ነው። ​ 66 ሚሊዮን ብር ለአንድ ማረፊያ ቤት እድሳት?! ​ደብዳቤው በግልፅ እንደሚያሳየው፣ አረጋ ከበደ አዲስ አበባ ሲሄድ ለሚያርፍበት ቤት እድሳት የሚሆን 66 ሚሊዮን ብር ከገንዘብና ኢኮኖሚ ቢሮ ወጪ ሆኖ «ህብር ኮንስትራክሽን» ለተባለ ተቋም እንዲከፈል ታዟል። ​በእውነት ይህ ልብን አይሰብርም? ህዝቡ ለመሰረታዊ ህክምናና መድኃኒት አጥቶ፣ ትምህርት ቤቶችና ጤና ጣቢያዎች ተዘግተው፣ እናቶችና ህፃናት በምግብ እጥረት እያለቀሱና በድሮን ጥቃት እየተገደሉ ባሉበት ጨለማ ወቅት ለአንድ ባለስልጣን ጊዜያዊ ማረፊያ ቤት እድሳት ብቻ ይሄን ሁሉ ሚሊዮን ማፍሰስ በህዝብ እንባ ላይ አረመኔያዊ ማፌዝ ነው! ​የመንግስት ሀብትና የህዝብ ግብር ለህዝብ መሰረታዊ አገልግሎቶች ለጤና፣ ለትምህርት እና ለምግብ ዋስትና ሊውል እንጂ ለአንድ ግለሰብ ድሎትና ቅንጦት ማሟያ ሊሆን አይገባም። ​ሌላው የተጋለጠው እውነታ፦ የአባይ ማዶው ህንፃ እና የድልድዩ ፕሮጀክት ቁሳቁስ! ​መዝበራው በዚህ ብቻ አላበቃም፤ በአዲስ አበባው ማረፊያ ቤት ላይ የተመደበው ወጪ ሳያንስ፣ በባህር ዳር ከተማ አባይ ማዶ ላይ የሚገኘው የአረጋ ከበደ ቤት ግንባታ ሌላው አሳዛኝ ምስጢር ይዟል። ​ውስጥ አዋቂው አያሌው መንበር እንደዘገበው ከሆነ፣ የዚህ ህንፃ ግንባታ የተከናወነው ጎጃምን ከጎንደር የሚያገናኘው ስትራቴጂካዊ የድልድይ ፕሮጀክት ከተገዙት ቁሳቁሶች እየተጫነ ነው። የህዝብ መሸጋገሪያና የልማት ፕሮጀክት ንብረት ተወስዶ ለግለሰብ መኖሪያ ቤት መዋል ሀገራችን በምን ያህል አሳዛኝ የመበዝበዝ አደጋ ውስጥ እንዳለች የሚያስረዳ ህሊናን የሚያም እውነታ ነው። ​ ሀገር በዚህ ልክ ሲመዘበር፣ ህዝብ በድሮን ጥቃትና በችግር ሲማቅቅ ማየት እጅግ ልብ ይሰብራል፤ ያሳዝናልም። ​ፈጣሪ ለህዝባችን መፅናናትንና መፍትሔውን ያምጣለት! ሃሳብ ስጡበት ከታች!! #Dave #Amhara